Get Mystery Box with random crypto!

ACTS REVIVAL

የቴሌግራም ቻናል አርማ acts_revival — ACTS REVIVAL A
የቴሌግራም ቻናል አርማ acts_revival — ACTS REVIVAL
የሰርጥ አድራሻ: @acts_revival
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 243
የሰርጥ መግለጫ

መንፈስን ተሞልተን ኢየሱስን እንገልጣለን

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-10-19 20:50:31 ስለ ኃይል ሌሎችም እንዲጋሩ ለጥቂት ጊዜ Bioዋቹን
ባለክ ገብ ግብር ትከፍላለህ
ባለክ ኃይል ደግሞ ተአምራት ታደርጋለህ

በማለት ፃፉ
586 views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-17 21:31:47 የኃይልን ምስጢር ማወቅ
*Part-2

ማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 17 ላይ ኢየሱስ የምጥል በሽታ ያለበትን ልጅ ስፈዉሰዉ የልጅየዉ አባት መጀመሪያ ልጁን ያመጣው ደቀመዛሙርቱ ጋር ነበር ግን ደግሞ ደቀመዛሙርቱ አጋንንቱን ማውጣት ባልቻሉ ጊዜ ወደ ክርስቶስ እንዳመጣው ይናገራል ፨
ማቴዎስ 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁹ ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ብቻቸውን ወደ ኢየሱስ ቀረቡና፦ እኛ ልናወጣው ያልቻልን ስለ ምን ነው? አሉት።
²⁰ ኢየሱስም፦ ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፦ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።
²¹ ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።

እዚህ ጋር ልብ እንዲትሉልኝ ምፈልገዉ እነርሱ ሁለት ነገር ነበር የጎደላቸው የመጀመሪያው የእምነት ማነስ ስሆን ሁለተኛው ግን ኃይል ነበር ፨
ክርስቶስም “ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም ስላቸው የአጋንንቱን ግብዝነት ወይም የአጋንንቱን ከባድነት እያወራቸዉ አልነበረም ይልቁኑ ኃይል እንዳልነበራቸው እንጂ ለዚህም ነበር ክርስቶስ ስናገር በጸሎት እና በጾም ካልሆነ ባስተቀር አይወጣም ያለው ይህ ጸሎትና ጾም ኃይልን ማግኛ መንገድ ስለሆነ ።
በመጨረሻ የኃይልን ምስጢር ማወቅ በምለው ሀሳብ ዋናው ነጥቡ ( መልዕክቱ ) :-

ባለክ ገብ ግብር ትከፍላለህ ባለክ ኃይል ደግሞ ተአምራት ታደርጋለህ ::::::

#Join_Share

@Acts_Revival
@Acts_Revival
1.3K views18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-16 21:42:03 የኃይልን ምስጢር ማወቅ
Part-1

"Paying your tax in your income"
ይህ ማለት ካለክ ገብ አንጻር ግብርን ትከፍላላህ ማለት ነዉ ፨
ምሳሌውን ያነሳውበት ምክንያት ዛሬ የኃይልን ምስጢር በጥቂቱ ልነግራችሁ ፈልጌ ነዉ ፨ ኃይል ማለት ምን ማለት ነዉ ??
ኃይል ማለት አብዝተን የእግዚአብሔር ክብር ( መንፈስ ቅዱስን ) ከመፈለግ ብዛት የምመጣ ነገር ነዉ :
አሁን እኔ ወይም እናንተ እና Apostle Tamirat Tarekegn ያለን ኃይል እኩል አይደለም : እርሱ አብዝቶ የእግዚአብሔር ክብር ( መንፈስ ቅዱስን ) ስለፈለገ ( ስለተጠማ ) በእርሱ ዘንድ ኃይል አለ ፨
ስለዚህም ሽባዉን ይተረትራል ፣ አጋንንትን ያወጣል ...
ለዚህም ነበር "Paying your Tax in your income" ያልኩት :- ባለክ ገብ ልክ ግብርን ትከፍላለህ
ባለክ ኃይል ደሞ ተአምራት ታደርጋለህ
The same as ከመሬት ተነስተህ ክርስቲያን ስለሆንክ ብቻ የሆነ አጋንንትን "በኢየሱስ ስም ለቀሀዉ/ሀት ሂድ" ብትለው መልሶ ይስቅብሀል እንጂ ፍንክቺ አይልም

*Part-2 እሁድ ይ ጥላል
@Acts_Revival
@Acts_Revival
4.3K views18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-14 12:10:52
ሐዋርያት 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵⁴ ይህንም በሰሙ ጊዜ በልባቸው በጣም ተቈጡ ጥርሳቸውንም አፋጩበት።
⁵⁵ መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፦
⁵⁶ እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ።
@Acts_Revival
2.7K views09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-05 21:55:52 ካልሰጠሀኝ የመንፈስ ቅዱስ እሳቱን ፤
ካልወረደ ክብርህ አንደ በዓለ ኀምሳኛዉ ቀኑ ፤
እኔስ አለቅህም ካልሆንኩ አንደ ሐዋርያቱ፨
#Revivall
@Acts_Revival
459 views18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-29 15:01:59 ጥቂት የሪቫይቫል ከዋክብቶች ስለሪቫይቫል የጻለዩት ጸሎት
======================
ጆን ኖክስ የእስኮትላድ የተሃድሶ መሪ ሲጸልይ፦እግዚአብሔር ሆይ እስኮትላንድን ስጠኝ ወይንም ግደለኝ ይል ነበር። በጣም ይጸልይ ስለነበር ፊቱ እጅግ ስለሚያስፈራ፦የአገሩ የእስኮትላድ ንግስት ሜሪ ስለእርሱ ስትናገር እኔ ከእግሊዝ ጦር ሠራዊት ይልቅ የሚያስፈራኝ የጆን ኖክስን ፊት ማየት ነው ትል ነበር ይባላል።እንዲሁም ሔብራይትስ በሚባል ሪቫይቫል የነበሩ ወንድሞች ልክ እንደ ጆን ኖክስ ጌታ ሆይ የማትጠቀመን ከሆነ ግደለን እያሉ ይጸልዩ ነበር።

ሴይንት (st)ፓትሪክ በእግዚአብሔር ጽኑ አማኝ የሚል ቅጽል ስም የወጣለት ሰው፦ሲጸልይ የሞቱ ከብቶችና ዛፎች ሳይቀር ተመልሰው ሕያዋን ይሆኑ እንደነበርና ሁሌ ሲጸልይ ጌታ ሆይ ነፍሳትን የማትሰጠኝ ከሆነ ምንንም አትስጠኝ ይል ነበር ይባላል።

1904 ከካልፎርኒያ አሜሪካ አሱዛ እስትሪት ሪቫይቫል ይዘው ወደ እንግላንድ የመጡ የእንግላንድ ወጣቶች እጅግ ከባድ ቅዝቃዜ በነበረበት ክረምት በየቀኑ ይጸልዩ ነበር የጸሎታቸውም ዋና ርዕስ ጌታ ሆይ የአንተን እሳት ይዘው በእንግሊዝ መንገዶች ላይ እየሮጡ የሚያሰራጩ ስዎችን እባክህን ስጠን ይሉ ነበርና የናፈቁት የመንፈስ ቅዱስ እሳት አልቀረም ተከሰተ።

የእኔም ጥማት በእትዮጵያ የእግዚአብሔር ክብር በሀይል ስገለጥ ማይት ነው የእትዮጵያ ልጆች በመንፈስ ቅዱስ ተቀጣትጥለው ወንጌልን በገጠርቷና በከትማይቷ እትዮጵያ ከዛሚ አልፎ ለዓለም የወንጌል ሰደድ እሳት ስሰብኩ ማይት ውስጤ ነው።

#ወንጌልን_ባልሰብክ_ወዮልኝ
#ሪቫይቫል_በደጅ_ነው
#God_of_Revival
#we_need_revival

#Revival #Revival #Revival




@Acts_Revival
@Acts_Revival
3.7K views12:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-20 17:23:40 #መንፈስቅዱስ

መንፈስ ቅዱስ -የሪቫይቫል ምንጭ ባለቤትና ኃይል
“እግዚአብሔር ይላል ፡- በመጨረሻው ቀን እንዱህ ይሆናል ፤ ሥጋ በሇበሰ ሁለ ሊይ
ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤”-የሐዋ 2፡17
አማኝ በክርስቶስ ኢየሱስ ሲያምን ሕያው የሚያደርገውንና ለዘላለምም በሕይወት
እንድኖር የሚያስችለውን የሥላሴን ሶስተኛው አካል (ደረጃን አያመለክትም)
ክቡሩና አስደናቂው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ስጦታ ሆኖ ይሰጠዋል ፡፡ ይኸው
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከአማኙ የግል ሕይወት መዳንና መለወጥ ባለፈ
በቅድሳን ሕብረት (በቤተክርስቲያን) ውስጥ ጥበብንና ኃይልን በመግለጥ
ቤተክርስቲያንን በትውልድ መካከል የታመነ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ምስክር አድርጎ ያቆማታል ፡፡
እርሱ መንፈስ ቅዱስ ከዘላለም የነበረ ለዘላለምም የሚኖር ሁለን የፈጠረ እና
ለሙታንም ሕይወትን የሚሰጥ የሥላሴ ሶስተኛ አካል የሆነ የእግዚአብሔር
ሕይወት ነው፡፡ እርሱ ባለበት ሁለ ሕይወት አለ ፡፡ በእርሱ መገኘት ውስጥ ሞትና
ጭንገፋ አይሰራም፡፡ ያስባል፣ ይናገራል፣ ያዳምጣል ፣ ይሸከማል፣፤ያስተምራል ፣
ይመራል ፣ ያስተጥቃል። እግዚአብሔር እርሱ በላከው በኢየሱስ ክርስቶስ
ለሚያምኑ ያዘጋጀው ስጦታ መንፈስ ቅደስ መሆኑ ምን ያህል ፍቅር እና ቸር
መሆኑን ያሳያል፡፡ መንፈስ ቅደስ የጥበብና የማስተዋል መንፈስ ነው፤ የምክር እና
የኃይል መንፈስ ነው፤ የእውነት እና የቅድስና መንፈስ ነው፤ የትንሣኤ እና የክብር መንፈስ ነው…፡፡
ይህ እንዲለ ሆኖ መንፈስ ቅዱስንና ሪቫይቫል ምንድን ነው የሚያገናኛቸው? ጌታኢየሱስ ሐዋሪያቱን ለወንጌል ሥራ ከመላኩ በፊት በሐዋ 24፡49 “ከላይ ኃይልን
እስክትለብሱ ድረስ …” ብሎ በመናገር ያለ መንፈስ ቅደስ ለመንቀሳቀስ እንኳ
እንዲይሞክሩ አስጠንቅቋቸዋል ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ እግዚአብሔር በመጨረሻው
ዘመን ሥጋ በለበሰ ሁለ ከመንፈሱ እንደሚያፈስ እና ምልክቶችና ድንቆች
እንደሚሆኑ ተናግሯል (ኢዩ 2፡ 28-30) ፡፡ ጌታ ኢየሱስም በግልጥ ሲናገር “ያለእኔ
ምንም ልታደርጉ አትችሉመምና” ብሏል (ዮሐ 15፡5) ፡፡ እነዚህ እና ሌሎች
የእግዚአብሔር ቃል ጥቅሶች የሚያስረዱት እግዚአብሔር የሚያደርገውን ነገር ሁሉ
የሚያደርገው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት መሆኑን ነው፡፡
የእግዚአብሔር ስራ ያለ መንፈስ ቅድስ የማይሞከር፣ ጭራሹንም የማይታሰብ
ነው፡፡ ይልቁንም ጉዲዩ ሪቫይቫል ሲሆን መንፈስ ቅዱስ እና መንፈስ ቅዱስ ብቻ
የሪቫይቫሉ ምንጭ፣ ባለቤት እና ኃይል በመሆን ዋነኛ ድርሻውን ይወስዲል፡፡
ቤተክርስቲያን ለመንፈስ ቅዱስ ዕውቅናን መስጠትና በእርሱም ለመመራት እራሷን
ማስገዛት ይጠበቅባታል በመንፈስ ቅዱስ መመራት እና በመፅሃፍ ቅዱስ እውነት
መመራት የሚጋጭበቸው ሰዎች ልኖሩ ይችላሉ ፡፡ መንፈስ ቅዱስ መፅሃፍ
አይደለም፡፡ መፅሃፍ ቅዱስንም ያዘጋጀልን እርሱን እንድተካልን አይደለም ፡፡
ይልቁንም በእርሱ መሪነት እግዚአብሔርንና በክርስቶስ በኩል ያደረገልንን በማወቅከእርሱ ከራሱ ጋር ቀጥተኛ ሕብረት እንዲኖረን እና ከምድር ባልሆነ የእርሱ ኃይል
ወንጌልን በድንቆችና በምልክቶች፣ በፈውስና በተአምራት መስበክ እንዴንችል
ነው፡፡ መንፈስ ቅደስ የሪቫይቫል ምንጭ፣ ባለቤት እና ኃይል ነው፡፡
በብለይ ኪዳን መፃህፍትም ሆነ በአድስ ኪዳን ሲያልፍም በቤተክርስቲያን ታሪክ
ውስጥ ተፅዕኖን ፈጥረው እና የእግዚአብሔርን ክብር ገልጠው ያለፉ የእግዚብሔር
ሰዎች ትልቁ ምስጢራቸው ከዚህ የእግዚአብሔር መንፈስ መንፈስ ቅዱስ ጋር የነበራቸው ጥብቅና ጥልቅ ቁርኝት ነው፡፡ እርሱን ማስተዋል የጀመሩ ጊዜ
ሕይወታቸው ተቀየረ፤ አካሄዳቸውንም ከእርሱ ጋር ባደረጉ ጊዜ ከፍ ሊለ ዓላማ
ሲጠቀምባቸው ታየ፡፡ ሪቫይቫልን የሚያደርገው የእግዚአብሔርንም ክብር ኢየሱስ
ክርስቶስን የሚገለጠው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነው፡፡ ክብር ሁሉ…
ለእርሱና እርሱ ብቻ ይሁን!!!!! ሃሌሉያ!!!!!!!
ይድረስ የእግዚአብሔርን ክብር ለተራቡት please share በማድረግ ተባበሩኝ
@Acts_Revival
@Acts_Revival
@Acts_Revival
2.0K views14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-18 18:44:10 መዝሙሩን የስልካችዉ ጥር አድርጉት የሰማኝ እሱ ይጠቀማል ብቻ ምን አለፋችሁ ጥርያችዉ አድርጉ ፨
#WE_NEED_REVIVAL

@Acts_Revival

ያደረገ ብቻ
1.2K views15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ