Get Mystery Box with random crypto!

አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ abukelemsismedia — አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
የቴሌግራም ቻናል አርማ abukelemsismedia — አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @abukelemsismedia
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.26K
የሰርጥ መግለጫ

አቡቀለምሲስ ማለት ረአየ ኅቡኣት አበ ራዕይ አበ ትንቢት ማለት ሲሆን የተሰወረውን የተደበቀውን የተከደነውን የሚገልጥ ማለት ነው። መሠራታዊ ዓለማው በሀገረ ስብከታችን ብሎም በመላ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰወሩ ገዳማትን የተደበቁ ሊቃውንትን የተከደኑ ታሪኮችን የተሸሸጉ ቅርሶችን ማውጣት እና የተንሸዋረረ ታሪክ ማስተካከልና የጎበጠውን አዲሱን ትውልድ ማነጽ ነው

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-23 22:39:45 የብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፲፯ኛ ዓመት ሢመተ ጵጵስና ተከበረ።

ሐምሌ ፲፯ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ፣ደብረ ብርሃን)
++++++++++++++++++++++++++++++

የብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፲፯ ዓመት በዓለ ሢመት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቅዐ ጥበብ አባቡ ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ሓላፊዎች እና ሠራተኞች እንድሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተከብሯል።

የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ክቡር መጋቤ ሐዲስ ነቅዐ ጥበብ አባቡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ማርቆስ ጳጳሳትን ሾማ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ከዛሬ 17 ዓመት በፊት ካሰማራቻቸው ብፁዕ አባታችን አንዱ ነበሩ ሲሉ አውስተዋል።

ክቡር ሥራ አስኪያጁ ብፁዕነታቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና ምእመናን በአስተዳዳሪነት በተለያዩ አድባራትና ገዳማት በአስተዳዳሪነት እና በሊቀ ጵጵስና በሐረርና በደቡብ ሀገረ ስብከቶች ያገለገሉ ሲሆን ልዩ ልዩ የዓለም ፈተና ሳይበግራቸው ፈተናዎቹን አልፈው ዛሬም ለሀገረ ስብከታችን ዕድገትና መልካም የሥራ ፍሬ የብፁዕነታቸው አባታዊ የሥራ መመሪያና ጸሎት አቅምና ኃይል ኾኖናል ብለዋል።

በዚሁ የብፁዕነታቸው የእንኳን አደረሰዎት መርሐ-ግብር ላይ የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ሓላፊዎችና የሀገረ ስብከቱ ሠራተኞች ፣ የአድባራት ገዳማት አስተዳዳሪዎች እና የወረዳ ቤተ ክህነት ሠራተኞች ባስተላለፉት መልእክት ብፁዕ አባታችን ለቤተ ክርስቲያን የተፈጠሩና የሚኖሩ ናቸው እኛም ልጆቻቸው የብፁዕነታቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎትና አስተዳደራዊ የሥራ መመሪያ በመቀበል ለሀገረ ሰብከቱ ሁለተናዊ ዕድገትና ውጤት እንተጋለን ብለዋል።

ብፁዕነታቸው በዚኽ የእንኳን አደረሰዎት መርሐ-ግብር ላይ ለተገኙት ልዩ ልዩ ሠራተኞችና እንግዶች ባስተላለፉት ቃለ በረከት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ባሰማራቻቸው ገዳማትና አድባራት እንድሁም በጵጵስና በተመደቡባቸው አህጉረ ስብከቶች ልዩ ልዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች እና የልማት ሥራዎችን እንዳከናወኑ ገልጸው ሀገረ ስብከታችንን ከዚኽ በላቀ ለማሳደግ መትጋት አለብን ብለዋል።

ብፁዕነታቸው እያጋጠመን ያለውን ሀገራዊ ፣ ሃይማኖታዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተና በመቋቋም የሀገራችንን ፣ የሕዝባችንና የቤተ ክርስቲያናችን ተግዳሮቶች ከምንጩ ለማድረቅ የአንዱን ድካምና ክፍተት ሌላው በመሸፈን በፍጹም ሰላማዊና አንድነት ፣ በፍቅርና በመተሳሰብ ለላቀ የልማትና የዕድገት ሥራ መነሳሳት አለብን ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ ከልጅነታቸው ጀምሮ በተለያዩ ጉባኤ ቤት ቅኔ ፣ ድጓ ጾመ ድጓ ፣ አቋቋም ፣ ዝማሬ መዋስዕት ፣ ቅዳሴ፣ መጻሕፍተ ሐዲሳትና ብሉያት በመማር የቤተ ክርስቲያኗን ማዕድ በአግባቡ የተመገቡ ትጉህ ደቀ መዝሙር እንደነበሩ በመርሐ-ግብሩ ላይ ተገልጿል።

ዘገባ በዲ/ን አሰፋ ጌትነት
ፎቶ ሚኪያስ አብዩ
479 viewsedited  19:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 22:43:51 የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕርገት በማስመልከት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የአቡቀለምሲስ ሚዲያ መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ የሰጡት አባታዊ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን
496 viewsedited  19:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 21:07:10
483 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 12:54:46
299 viewsAbukelemsis, 09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 12:54:09 ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ህንጻ ቤተ መቅደስ ጎበኙ።

ሰኔ ፳፱ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ አዲስ አበባ)
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ግዙፍ ህንጻ ቤተ ክርስቲያን ጎብኝተዋል።

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በመ/ፓ/ጠ/ጽ/ቤት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምንጃር ወረዳ ቤተ ክህነት የአረርቲ ህንጻ ቤተ መቅደስ ሲጎበኙ የደብሩ አስተዳዳሪ ገለጻ አድርገውላቸዋል።

ብፁዕነታቸው ምድር ቤቱ 8 መቶ ካሬ ሜትር ወለሉ 2 ሺህ 7መቶ ፣ ፎቁ 6 መቶ 50 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈውንና የአፍሮ አይገባ መስቀል ፣ የኖኅ መርከብና ሰሎሞናዊ ቤተ መቅደስ ቅርጽ ያለውን ዘመናዊ ካቴዲራል ነው የጎበኙት።

የግንባታው ሥራው 70 ፐርሰንት ላይ የሚገኘውን የአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ሕንጻ ቤተ መቅደስ እና የአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ጎብኝተው ለህንጻ አሠሪ ኮሚቴው እና ለካህናቱ የማበረታቻ አባታዊ ትምህርት ሰጥተዋል ።


መረጃው፦የምንጃር ወረዳ ቤተ ክህነት ነው።

ዩቱብ፦

294 viewsAbukelemsis, edited  09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 23:19:08
570 viewsAbukelemsis, 20:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 11:51:10
654 viewsAbukelemsis, 08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 11:50:20 የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ከዲፕሎማ እስከ ሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 5 መቶ 30 ደቀ መዛሙርት አስመረቀ!!


(ሰኔ ፳፭ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ደብረ ብርሃን))
++++++ ++++ ++++++ +++++ +++++ +++

የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ ትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 5 መቶ 30 ደቀ መዛሙርት በዛሬው እለት አስመርቋል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት መምሪያ ሓላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መምሪያ ሓላፊዎች የዩኒቨርስቲው የአስተዳደር ሠራተኞች እና መምህራን የተመራቂ ደቀ መዛሙርት ቤተሰቦች በተገኙበት የምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ተከናውኗል ሲል የዘገባው ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ነው።
559 viewsAbukelemsis, 08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 16:48:10
549 viewsAbukelemsis, 13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ