2022-07-12 20:34:47
እግዚአብሔር ህዝቡን ጎበኘ ---------------------------------------------------
ሉቃስ 7፥16“ሁሉንም ፍርሃት ያዛቸውና፦ ታላቅ ነቢይ በእኛ መካከል ተነሥቶአል፥ ደግሞ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን ጐበኘ እያሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።”
---------------------------------------------------
የሥላሴ አማኒያን ኢየሱስ አምላክ ነው ለማለት ይህን ጥቅስ ማረጋገጫ አድርገው ይጠቅሱታል፣ ምክንያቱም እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደጎበኘ ስለሚናገር ነው።
ነገር ግን ክፍሉ በጭራሽ እንደዛ አያመለክትም አውዱ ላይ ሰዎቹ ኢየሱስን “
ታላቅ ነቢይ
በእኛ መካከል ተነሥቶአል ” ብለው መናገራቸው ነብይ አድርጎ የሚያስነሳ ሌላ አካል እንዳለና ኢየሱስ አምላክ ነው ብለው እንደማያምኑ መረዳት እንችላለን።
"እግዚአብሔር ሕዝቡን ጐበኘ " የሚባለው እግዚአብሔር በሰዎች በኩል ሲሰራ፣ ቃሉን ሲያስተላልፍ
እግዚአብሔር ህዝቡን ጎበኘ ተብሎ ይነገራል ይህ አገላለፅ ድሮም የነበረ ነው
ለምሳሌ ፡ አሮን እግዚአብሔር ለሙሴ የነገረውን ቃል ለህዝቡ ተናግሮ ተአምራቱንም ሲያደርግ
እግዚአብሔር የእስራኤል ልጆችን ጎበኘ ተብሏል ፡፡
ዘጸአት 4፡30-31¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁰ አሮንም እግዚአብሔር ለሙሴ የነገረውን ቃል ሁሉ ተናገረ፥ ተአምራቱንም በሕዝቡ ፊት አደረገ።
³¹ ሕዝቡም አመኑ፤
እግዚአብሔርም የእስራኤልን ልጆች እንደ ጐበኘ ጭንቀታቸውንም እንዳየ በሰሙ ጊዜ፥ አጐነበሱ ሰገዱም።
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
በኢየሱስ ጊዜ አምላክ ህዝቡን ጎበኘ የተባለው ተዓምር የሚያደርግ ነብይ ኢየሱስን በመላኩ ነው ፡፡ የኢየሱስ ነብይነት በርካታ ቦታዎች ላይ ተዘርዝሯል፡፡ (ማርቆስ 6:4 , ሉቃስ 7:14 , ማቴዎስ 21:11, ማቴዎስ 13:57 ..)
አብዱልከሪም
------------------------------------------
ለተጨማሪ ትምህርቶች ይቀላቀሉ
https://t.me/Abdulkerimcomparative
1.8K views17:34