Get Mystery Box with random crypto!

ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ለ100 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል የሚፈጥር ፕሮጀክት ይፋ አደረገ! ማስተ | Aß Mustefa

ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ለ100 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል የሚፈጥር ፕሮጀክት ይፋ አደረገ!

ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን 20 ሚለየን ብር በጀት የያዘለትንና በ7 ኢንድስትሪ ፓርኮች ውስጥ አንድ መቶ ሺ ወጣቶች የስራ እድል እንዲያገኙ እንዲሁም ሙሉ የመረጃ ሲስተም ለመዘርጋት የሚያስችለውን ስምምነት ከኢትዮጲያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በትላንትናው ዕለት ተፈራርሟል፡፡

በፕሮጀክቱ በኢንዱስትሪ ፓርኮች 100 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ ያሉ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ያሉትን የስራ እድሎች፣ ጥቅሞቹን፣ ለስራው ማሟላት ያለባቸው መስፈርት ምን እንደሆነና ሌሎችም መረጃዎችን የሚያገኙበት ሲስተም በመዘርጋት የመረጃ ችግሩን ለመቅረፍ ያስችላል ተብሏል፡፡

ፋውንዴሽኑ ድጋፍ የሚደርግባቸው ኢንድስትሪ ፓርኮችም በአዳማ፣ ድሬደዋ ፣ባህርዳር፣ ደብረ ብርሀን፣ሀዋሳ፣ መቀሌ እና ኮምቦልቻ የሚገኙት ሲሆኑ በቀጣይ 3 ኢንድስትሪ ፓርኮች ላይም ድጋፍ እንደሚደርግ ኢትዮ ኤፍ ኤም ዘግቧል፡፡

@Ab_Mustefa