Get Mystery Box with random crypto!

(ABC) Amhara Broadcasting Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ ab_corporation — (ABC) Amhara Broadcasting Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ab_corporation — (ABC) Amhara Broadcasting Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @ab_corporation
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 225
የሰርጥ መግለጫ

ለእውነተኛ እና ፈጣን መረጃዎች አሁኑን ይቀላቀሉ
########################
@ABC_Broadcasting
We are here to deliver updated News, Exclusive programs, Interviews, Entertainment and more Reliable and Updated Information about Amhara Region And Ethiopia people

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-29 05:44:12
የመኖሪያ ቤት ሽልማት ለባለ እድለኞች ከአማራ ባንክ፡፡
ሰላም ፍቅር ጤና እንዲሆንላቹ እየተመኘን የባንኩ ቦርድ ሊቀመንበር አቶ መላኩ ፋንታ ሀገራዊ ለዉጡን ተከትሎ ሀገራዊ ኢኮኖሚዉን ለማሳደግ የተከፈተ ባንኩ ሲሆን በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ አስተዋጽዎ ለማድረግ የተጀመረ ባንክ ነዉ ብለዋል። በዚህም ባንካችን ስራ በመጀመሩ ምክንያት ለመላው ኢትዮጵያውያን መልካም ስጦታ ይዘን ቀርበናል እናም እድለኛ ለሆኑ 3 የአዲስ አበባ ወይም ከአዲስ አበባ ውጪ ለሚኖሩ ነዋሪዎች የመኖርያ ቤት አፓርታማ ልንሸልምዎ ዝግጅታችንን ጨርሰናል፡፡
1ኛ እጣ ባለ 3 መኝታ ከነሙሉ እቃው፡፡
2ኛ እጣ ባለ 2 መኝታ ከነሙሉ እቃው፡፡
3ኛ እጣ ባለ 1 መኝታ ከነሙሉ እቃው፡፡
ቀጥሎ ላሉ 100 እድለኞች የ1000 ብር ያልተገደበ የኢንተርኔት አገልግሎት ሽልማት ይኖረዋል፡፡ ይህ እጣ የሚቆየው እስከ ሰኔ 30 ሲሆን ሰኔ 30 ላይ በኮምፒዩተር እጣ አወጣጥ ዘዴ በመታገዝ እድለኞችን ሰኔ 30 ላይ በዚ ቻናል ላይ ይፋ የምናደርግ ይሆናል፡፡
ከእናንተ ሚጠበቀው ቻናላችንን መቀላቀል እንዲሁም ደግሞ ለዘመድ አዝማድዎ ለወዳጅዎ ለግሩፖች እድላቸውን እንዲሞክሩ ቢያንስ ለ60 ሰዎች ሼር በማረግ እንዲቀላቀሉ መጋበዝ ብቻ ነው፡፡ ከ 60 ሰው በላይ መጋበዝ እድልዎን ያሰፋል፡፡

መልካም እድል ከ አማራ ባንክ፡፡

@Amharabankb
@Amharabankb
@Amharabankb
50 views02:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 16:11:24
በባሕር ዳር ከተማ ውስጥ የሽብር ጥቃት ለመፈፀም የተንቀሳቀሱ አካላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።
የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር መሰረት ደባልቄ በሰጡት መግለጫ÷ "በሀገሪቱና በክልሉ ሕግ ለማስከበር እየተንቀሳቀስን እንገኛለን" ብለዋል፡፡
ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ምሽት ኅብረተሰቡን ለማሸበር ያለመ ወንጀል ለመፈፀም የፈለጉ ቀሪ ኀይሎች በባሕርዳር ከተማ በአራት ቦታዎች ላይ ቦንብ እንዳፈነዱ ገልጸዋል።
ፖሊስ ከሕዝብ ጋር በመቀናጀት ባደረገው ክትትልም ወዲያውኑ 6 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር አውሏል ነው ያሉት።
የተጠርጣሪዎች ቤት በሚፈተሽበት ወቅትም 2 ቦንብ፣ 3 ብሬን መሳሪያ እና 3 ሺህ 700 ጥይት፣ አንድ ስናይፐርና 500 ጥይት እንዲሁም በቀጣይ ተመሳሳይ የሽብር ወንጀል ለመፈፀም የያዙትን እቅድና መመሪያ ፖሊስ መያዙን ኮማንደር መሰረት ተናግረዋል።
በዚሁ ምሽት ከዚሁ ሽብር ጋር ግንኙነት ያላቸው 14 ተባባሪ አካላት በቁጥጥር ስር ውለው የክልልና የፌዴራል የፀጥታ አካላት ምርመራ እያደረጉ ይገኛሉ ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል።በባሕር ዳር ከተማ ውስጥ የሽብር ጥቃት ለመፈፀም የተንቀሳቀሱ አካላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

በዚሁ ምሽት ከዚሁ ሽብር ጋር ግንኙነት ያላቸው 14 ተባባሪ አካላት በቁጥጥር ስር ውለው የክልልና የፌዴራል የፀጥታ አካላት ምርመራ እያደረጉ ይገኛሉ ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል። https://t.me/JournalistNetsanetGetachew
54 views13:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 17:26:27
#USA https://t.me/JournalistNetsanetGetachew
79 views14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 17:26:27
ኢራን በምዕራብ ወለጋ በጅምላ የተጨፈጨፉበትን ጥቃት አወገዘች። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ሰኢድ ካቲብዛበህ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል። https://t.me/JournalistNetsanetGetachew
72 views14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 17:26:27 “ቤተሰቦቻችን አልቀው እኛ አለን”

“እኔስ አንድ ወንድምና የወንድም እህት አጣሁ። ሙሉ ቤተሰቡን ያጣ ዘመዴ አለ። 21 ቤተሰብ የሞተበትም ሰው አለ እኮ። ልጆቹን፣ የልጅ ልጆቹን ያጣም አለ” ብሏል ከማል።

እሱ የሚኖርበት አካባቢ አቅራቢያ ባሉ ሦስት ጎጦች “250 ሰው እንደተቀበረ” እና ገና አስክሬናቸው ተፈልጎ የሚቀበሩ ሰዎች ስላሉ፣ የሟቾችን አጠቃላይ ቁጥር አሁን ላይ ለመናገር እንደሚከብድ ገልጿል።

“ቤተሰቦቻችን አልቀው እኛ አለን፣ ግማሹ ትላንት ተቀበረ። ግማሹ ዛሬ ይሰበሰባል። ትላንት ‘ይህን ሁሉ ሰው መቅበር አንችልም’ ብለው የተመለሱ አሉ” ሲል ከማል አክሏል።

ዛሬ ተጨማሪ የሰው ኃይል ለቀብር እንደሄደ ጠቅሶ “ምን ያህል ሰው እንደሞተ በዚህ መረዳት ይቻላል” ብሏል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጥቃቱን በተመለከተ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ዝርዝር ነገር ባያሰፍሩም፣ በተለያዩ ክልሎች ውስጥ የሚፈጸሙ እንዲህ ያሉ ጥቃቶችን መንግሥታቸው እንደማይታገስ ገልጸዋል።

መንግሥት ሸኔ ብሎ የሚጠራው እና እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት የሚለው ቡድን ታጣቂዎች በርካታ ሰላማዊ ሰዎች መግደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እና የኦሮሚያ ክልል አመልክተዋል።

ከማል ጥቃቱ በሚፈጸምበት ወቅት ወደ እርሻ ሄዶ እንደነበርና ጥቃቱ መፈጸሙን እንደሰሙ ወደ መንደራቸው ሲመለሱ ሴቶችና ሕጻናት በብዛት ተገድለው እንደደረሱ ተናግሯል።

“ወረዳውን ‘ኧረ እባካችሁ እርዱን፣ ኧረ የመንግሥት ያለህ’ ብለን ስንደውልለት የሚረዳን ጠፋ። ኋላ ላይ በ11 ሰዓት ለይምሰል የሚረዳን መጣ። የተጠቃው አማራ ብቻ ነው። ብሔር ለይተው ‘እዚህ ምን ተደርጋላችሁ? በቃ ውጡ!’ ነው ያሉን። እዚህ ካደራችሁ መልሰን መጥተን እንጨፈጭፋችኋላን ብለውናል። የሦስት ቀን ሕጻን ሳይቀር ተጨፍጭፎብናል።”

ጥቃቱ እሱ የሚኖርበት መንደር ጋር ሲጀመር፣ ቤቶች ሲቃጠሉ ከሩቁ ተመልክቶ ወደ ቤቱ አቅራቢያ እንደሄደም እንዲህ ተናግሯል።

“እየገሰገስን ስንመጣ መንደሩ ተከቧል። እኛንም በጥይት አባረሩን። ቤት ውስጥ የነበሩ ሴቶችና ሕጻናት አለቁ። አርሶ አደሩን እያባረሩ በጥይት ገደሉ። ሸንኮራ ማሳ ውስጥ ተደብቀው ሲያለቅሱ የነበሩ ሕጻናት ሳይቀሩ ተገድለዋል።”

የነዋሪዎች ንብረት እንደተዘረፈና ከእንግዲህ በኋላም ለደኅንነታቸው እንደሚሰጉም ከማል ተናግሯል።

“የቁም ከብት ቀርቶ ዶሮ የቀረው የለም። ተዘርፏል። የሞተው ሞቷል ለእኛ ለቀረው መፍትሄ እንዲሰጠን ነው የምንፈልገው። መንግሥት ካለ፣ ሕግ ካለ ከዚህ ያስወጣንና ወደ አገራችን ይመልሰን። እስካሁን ያዘነልን፣ ስህተት ነው ያለንም የመንግሥት አካል የለም” ብሏል።

ምዕራብ ኦሮሚያን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ውስጥ እንደሚንቀሳቀስ የሚነገርለት ታጣቂ ቡድኑ ቶሌ ቀበሌ ውስጥ በሚገኙ መንደሮች “ሲቪል ሰዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት በሰው ሕይወት፣ በአካል እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት” ደርሷል ሲል ኢሰመኮ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

የኦሮሚያ ክልል መንግሥትም በምዕራብ ወለጋ ዞን፣ ጊምቢ ወረዳ፣ ቶሌ ቀበሌ ውስጥ በአሸባሪነት የተፈረጀው ታጣቂ ቡድኑ ጥቃት መፈጸሙን አረጋግጦ፣ በዚህም ጥቃት በንጹሃን ሰዎች እና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ባወጣው መግለጫ ላይ አመልክቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ "በንጹሃን ዜጎች ላይ በሕገ ወጥ እና በኢ-መደበኛ ኃይሎች የሚደርስ ጥቃት እና መተዳደሪያን ማውደም ተቀባይነት የለውም” በማለት፣ “በቤኒንሻንጉል እና በኦሮሚያ ክልሎች፣ ዋና ዓላማቸው ኅብረተሰቡን ማሸበር በሆነ አካላት የተፈጸመው የሰው ልጆችን ሕይወት የሚቀጥፍ ዘግናኝ ድርጊት የምንታገሰው አይደለም” ብለዋል።

በጊምቢ ለሰዓታት ከተፈጸመው ጥቃት የተረፉ የዐይን እማኞች ምስክርነት

መረጃው የbbc ነው
https://t.me/JournalistNetsanetGetachew
67 views14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 22:15:46
#የተለያዩ

በነገው እለት ወደ ስራ የሚገባው የአማራ ባንክ የተሰኘው የንግድ ተቋም በጣም በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች እንደሚጋሩት ከአማራ ህዝብ ወይም ከክልሉ ህዝብ ጋር ግንኙነት እንዳለው አብዝተው ይገለጻሉ።

ነገሩ ግን ወዲህ ነው ተቋሙ የተመሰረተው የክልል ስም ይዞ ነው እንጂ የክልሉ ሀብት ሁኖ አይደለም ይልቁንም የክልሉ ህዝብ ሀብት የሆነው አብቁተ የተሰኘው ተቋም ማሳደግ ሲገባ የግለሰቦች የሀብት ምንጭ የሆነውን የአማራ ባንክ እንደ ህዝብ ባንክ ማስተዋወቅ ተገቢ አይመስለኝም።

ባንኩን የመሰረቱት ደግሞ የመንግስት ተቋማት ሀላፊዎች ናቸው ታዲያ ይህን የንግድ ተቋም ወደፊት በአማራ ክልል የተለየ እንክብካቤ ሊደረግ እና የንግድ ስርዓቱን የሚውክ ህገወጥ ተግባር በሀላፊዎች የፈፀሙ ይሆናል የሚል ስጋት አለ።

አንድ የህዝብ ተቋም የህዝብ ነው ለማለት በተቋሙ የሚገኙ ትርፋች ለህዝብ አገልግሎት የሚሆኑ ትምህርት ቤት የጤና ተቋማት የሚገነባበት እና የህዝብ ተወካዮች የሚመሩት ወይም ተጠሪ የሆነ ነው በዚህ መሰረት የአማራ ባንክ ይህዝብ ሳይሆን የንግድ ተቋም ነው።

https://t.me/JournalistNetsanetGetachew
94 views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 16:18:25
አዋሽ ባንክ አንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት የሚያስገኝ የሥራ ፈጠራ ውድድር ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።

የሥራ እድል ፈጠራን የሚያበረታታውና "ታታሪዎቹ" የተሰኘው ውድድሩ፤ አንድ ሺህ ተወዳዳሪዎችን እንደሚያሳትፍ ይጠበቃል።

አዳዲስ እና ችግር ፈቺ የሆኑ የሥራ ሀሳቦች ያላችሁ አመልካቾች በውድድሩ መሳተፍ ትችላላችሁ።

የማመልከቻ ቅጹ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት አማራጭ ሊንኮች ይገኛሉ፦

ለአማርኛ
https://formfaca.de/sm/ibm6Nojej

ለአፋን ኦሮሞ
https://formfaca.de/sm/WZwSVKhOY

ለእንግሊዝኛ
https://formfaca.de/sm/WFbP8sJNG

በተጨማሪም በየትኛውም የአዋሽ ባንክ ቅርንጫፍ በመቅረብና የተዘጋጀውን ፎርም በመሙላት ማመልከት ይቻላል ተብሏል።

የማመልከቻ ጊዜ
ከግንቦት 24 እስከ ሰኔ 15/2014 ዓ.ም
https://t.me/EthiopianEducationalTelevision
116 views13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 16:58:56
#ሄሎ_ኢትዮጵያ - ለቅዳሜ
#ጥያቄ
ልብሽ ከወደደኝ በዪኝ ወድካለው፤
ያው እድለኛ ነሽ መውደድ መታደል ነው።
:
:
ካልወደድሺኝ ደሞ ውስጥሽ አያመንታ፤
ፍቅር በፍቅር እንጂ ሲሆን በይሉኝታ ፤
ፍሬ መች ያፈራል የማታ የማታ።
እኔን አይወክልም!! https://t.me/JournalistNetsanetGetachew
96 views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 08:54:52
የሰዎች የመንቀሳቀስ መብት የተረሳበት ዝግጅቶች መበራከት

አሁን አሁን በኢትዮጵያ የተለያዩ ዝግጅቶች ለመዘጋጀት በማለት በርከት ህዝብ ለመንቀሳቀስ የሚጠቀምባቸውን መንገዶች የለም ቅድመ ንግግር ውይም ለህዝብ ከሳምንት ወይም ከ3 ቀናት በፊት ሳያሳውቅ መንገዳችን መዝጋት ማለፍ ክልክል ነው ማለት እየተለመደ እና ህብረተሰብን ደግሞ ለማጉላላት እየዳረገ ይገኛል።

በተላይ መንግስት ወደ ስልጣን በመጣበት ወቅት ህብረተሰብ ላይ የምንዘነጋው መንገድ የለም ቢል ቅኑ እየሆነ ያለው ግን በተቃራኒ ሁኗል በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመስቀል በዓል መክበሪያ በሆነው መስቀል አደባባይ ያለ እረፍት የተለያዩ ዝግጅቶች መንግስት በማዘጋጀት የመዲናዋን የእለት ከእለት እንቅስቃሴ ችግር ውስጥ እያስገባ ይገኛል።

በተላይ በዚህ የመንገድ መስተጓጐል መክንያት የተቸገሩ ሰዎች የሚነሱት ሀሳቦች በሚዲያ አልተነገረም ለምን በእረፍት ቀን እሁድ አያደርግም ወይም ህዝብን በሚያስቸግር መልኩ ለምን በአዳራሽ አይደርጉም የሚል ሀሳቦችን ያሰማሉ።

የመፍትሔ ሀሳብ መንግስት እንደነዚህ ትልቅ መንግሥታዊ ስነስርዓት በሚካሄድበት ወቅት ለህብረተሰቡ ተለዋጭ አማራጭ ማመቻቸት እንዲሁም ጉዳዩን በአዳራሽ ውስጥ መከወን ተገቢ ነው።

መረሳት የሌለበት ደግሞ አንድ የህዝብ መንገድ ከመዝጋት በፊት በህግ የተቀመጠውን ለህብረተሰቡ ቀድሙ ማሳወቅ እንዲሁም ከአካባቢው የህዝብ እንደራሴዎች ጋር ውይይት ማድረግ መዘንጋት የለበትም።

https://t.me/JournalistNetsanetGetachew
99 views05:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 23:25:46
#መዲናችን_መፀዳጃ_ቤት_ሆነች

አሁን አሁን በከተማችን ህዝብ በሚበዛባቸው የከተማዋ እንብርት ስፍራዎች እንደ መገናኛ ሜክሲኮ አደባባይ እና ሌሎች ሰዎች የሚበዙባቸው አካባቢዎች ላይ እንደ መደበኛ ነገር በመሀል አደባባይ ላይ በፕላስቲክ ላይ ሽንት መሽናት እና መሽናት እየተለመደ ነው።

በተላይ እንዚህ የፕላስቲክ ሽንት መሽኛ ስፍራዎች አካባቢ ላይ ያለው አስከፊ ሽታ በአካባቢው ለሚንቀሳቀሱ ማህበረሰብ ከፍተኛ የጤና ችግር ሁኗል ነገር ግን በአካባቢው ያሉ የደንብ አስከባሪዎችም በዝምታ ያለፉት ጉዳይ ሁኗል።

መንግስት ህዝብ እና ተቋማት አካባቢያቸውን ከቆሻሻ ንፁህ እንዲደርጉ እና አረንጓዴ አካባቢ እንዲፈጥሩ ጥሪ በሚደረግበት በዚህ ወቅት እንደዚህ ለትውልድ መልካም አርያ የማይሆን ለከተማ ውበትና ለጤና ችግር የሆነ የመንገድ ዳር የሽንት መሽናት ማሸናት ተግባር ሀይ ሌባል ይገባዋል።

ነገሩ ግን ትኩረት ሳያገኝ ከቆየ ይህ መጥፎ ልምድ እየተበራከተ በመሆደ የሀገራችን የጋራ ከተማ የሆነችውን አዲስአበባ መፀዳጃ ቤት እየሆነች ትመጣለች የሚል ስጋት አለኝ በአካባቢው መጥፋ ሽታ ማሽተት የተለመደ ይሆናል ይህም እንደ ጉንፋ፣ያሉ በሽታዎች በየ ቀኑ የምንጋለጥ እንሆናለን።

የመፍትሔ ሀሳብ በተላይ መንግስት በየ አካባቢው የሰራቸውን የመፀዳጃ ቤት አገልግሎት የሚሰጡ ስፍራዎች በአግባቡ እና ተገቢ በሆነ የክፍያ መርህ ለታለመው አላማ እንዲሰራ ማድረግ በተጨማሪም የከተማ መፀዳጃ ቤት እጥረትን በአግባቡ ጥናት በማድረግ ተጨማሪ ግንቦት ማድረግ እና በዚህ ህጋዊ ባልሆነ ስራ ላይ ጤናቸውን ችግር ላይ የጣሉ ወጣቶችን ወደ ስራ በማስገባት ችግሩን መፍታት ተገቢ ነው።

በመጨረሻም መልክት እባካችሁ በተቻለ መጠን ከመፀዳጃ ቤት ውጭ ባለመፀዳዳት አካባቢያችንን በጋራ ከበሽታ እንጠብቅ!!

@JournalistNetsanetGetachew
101 views20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ