Get Mystery Box with random crypto!

Addis Ababa Technical Vocational Training and Technology Development Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ aatvtdbureau — Addis Ababa Technical Vocational Training and Technology Development Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ aatvtdbureau — Addis Ababa Technical Vocational Training and Technology Development Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @aatvtdbureau
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄዎ
251913288028

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-25 15:54:40
የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ በክረምት የበጎ ፍቃድ መርሀ-ግብር ያስገነባቸውን የአቅመ-ደካማ ቤቶች አጠናቅቆ ለባለቤቶቹ አስረከበ፡፡

ነሀሴ 19 ቀን 2014 ዓ.ም

ኮሌጁ በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ውስጥ ከሚገኙ የአቅመ ደካማ ቤቶች መሀከል የሁለት አረጋውያን ቤቶችን በመለየት ሙሉ በሙሉ አፍርሶ በመገንባት ነው በዛሬው እለት ያስረከበው፡፡

ቤቶቹ የተገነቡት በኮሌጁ አሰልጣኞች ሙሉ የጉልበት እና የሙያ ተሳትፎ መሆኑ የተለየ እንደሚያደርገው የኮሌጁ ዋና ዲን ወ/ሮ ጌጤነሽ ዘራብዛ ገልጸዋል፡፡

በቤቶቹ ርክክብ መርሀ-ግብር ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ቴክኒክ ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወ/ሪት ፀዳለ ተክሉ በዚህ የቤት ግንባታ ሂደት ጉልበታቸውንና ሙያቸውን በነፃ ያበረከቱ የኮሌጁ አሰልጣኞችን አመስግነዋል፡፡ 

ወ/ሪት ፀዳለ የቤቶቹን ቁልፍ ለባለቤቶቹ ካስረከቡ በኋላ ባስተላለፉት መልዕክት ቢሮው በስሩ የሚገኙ ኮሌጆችን በማስተባበር የሚያከናውናቸውን ማህበረሰብ አቀፍ ተግባራት አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ቴክኒክ፣ ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዘንድሮ የክረምት በጎ ፍቃድ መርሀ-ግብር በስሩ የሚገኙ ኮሌጆችን በማስተባበር በከተማ ደረጃ 40 የአቅመ ደካማ ቤቶችን በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡
315 viewsmirmir haile, 12:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 15:03:10
ጎፋ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ምቹ የስልጠና እና የስራ  አካባቢ በመፍጠር ሂደት አበረታች ለውጦችን ማስመዝገቡን ገለፀ

ነሐሴ ፤ 19 ቀን 2014 ዓ.ም

ጎፋ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ምቹ የስልጠና እና የስራ አካባቢ በመፍጠር ሂደት አበረታች ለውጦችን ማስመዝገቡን ገልጿል፡፡

ኮሌጁ በስልጠና ሂደት የሚስተዋሉ የግብአት አጠቃቀም እና የምርት ብክነት ሊቀንስ በሚችል መልኩ የካይዘን ፍልስፍና ተግባራዊ በማድረግ አመርቂ  ውጤት መመዝገቡን የኮሌጁ  የተቋማት አቅም ግንባታ ምክትል ዲን አቶ ጎሳዬ አለሙ ተናግረዋል፡፡

ስለ ካይዘን ፍልስፍና የኮሌጁን ማህበረሰብ አቅም በማሳደግ ወደ ተግባር መገባቱን የሚናገሩት አቶ ጎሳዬ አሁን ላይ ከ5ቱ "ማ" ዎች የመጨረሻ  የሚባለው ማላመድ ደረጃ ላይ መድረሱን ገልፀዋል፡፡

ለዚህም በየስራ ክፍሉ የካይዘን ትግበራ ሂደቱን የሚከታተል "ከልቡ" የተሰኘ ኮሚቴ አይነተኛ ሚና እንደተጫወተ ይነገራል፡፡

ኮሌጁ የካይዘን ፍልስፍናን በሚገባ በመረዳት ወደ ተግባር በመግባቱ ምቹ የስልጠና እና የስራ አካባቢ መፍጠር ተችሏል  እንዲሁም የንብረት አያያዝና አጠቃቀም ማሻሻል ችሏል፡፡

በአሁኑ ወቅት ኮሌጁ ስታንዳርዱን የጠበቀ ወርክሾፖች ባለቤት ከመሆኑም በላይ በካይዘን ፍልስፍና በከተማዋ ካሉ ተቋማት ግንባር ቀደም በመሆን ልምዱን ለሌሎች  ተቋማት በማጋራት ላይ ይገኛል፡፡

በቀጣይም በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሁም በምስራቅ  አፍሪካ ደረጃ  ዕውቅና ለማግኘት እንቅስቃሴ መጀመሩን የተቋማት አቅም ግንባታ ምክትል ዲን አቶ ጎሳዬ አለሙ ጠቁመዋል፡፡
431 viewsmirmir haile, 12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ