✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ●••••✥••••✥••••✥✞ ✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ● የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤት ማደራጃ ክፍል ጋር በጋራ በመሆን በአዲስ አበባ ውስጥ ካሉ የደብራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣ የሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቃነ መናብርት እንዲሁም የስብከተ ወንጌል ኃላፊዎች ጋር በቀጣዩ ዓመት የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙሪያ ዛሬ ሐምሌ 22/2014 ዓ.ም የጋራ ምክክር አደረገ ። የምክክር መድረኩ የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤት ማደራጃ ዋና ክፍል ኃላፊ መምህር ደምስ አየለ የተመራ ሲሆን :: ስለ ስርዓተ ትምህርቱ ገለጻ እና ውይይት በመምህር በላይነህ መኮንን እና ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው ቀርቧል :: በምክክር ጉባዔው ማጠናቀቂያ ላይም ከየአጥቢያው የመጡ ባለድርሻ አካላት በየአጥቢያችን ላይ ሥርዓተ ትምህርቱን ለማስተግበር ኃላፊነት እንወስዳለን በማለት አጋርነታቸውን ገልጸዋል ። #የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት ✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ●••••✥••••✥••••✥✞ ✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ● 5.0K viewsBereket kebede, 11:50