አምስት ነገሮችን ከአምስት ነገሮች በፊት ተጠቀሙባቸው ፡፡ ወጣትነትህን ከማርጀትህ በፊት | وَتَوَكَّلْ عَلَى ٱللَّهِ ۚ وَكَفَىٰ بِٱللَّهِ وَكِيلًا🌹🌹
አምስት ነገሮችን ከአምስት ነገሮች በፊት ተጠቀሙባቸው ፡፡
ወጣትነትህን ከማርጀትህ በፊት
ጤንነትህን ከመታመምህ በፊት
ሀብትህን ከመደህየትህ በፊት
ትርፍ ጊዜህን ከመጨናነቅህ በፊት
ህይወትህን ከመሞትህ በፊት
የአሏህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሲናገሩ " ሕዝቦች አምስት ነገሮችን በመውደድ ከአምስት ነገሮቺ ይዘናጋሉ" ካሉ በኀላ ሲዘረዝሯቸው እንዲህ አሉ:
ሕይወትን ያፈቅሩና - ሞትን ይረሳሉ:
ዱንያን ያፈቅሩና -አኼራን ይዘነጋሉ፡
ህንፃ መገንባት ይወዱና - ቀብር መኖሩን ይዘነጋሉ፡
ገንዘብ ይወዱና - ከሒሳብ ( በቂያማ ግዜ መተሳሰቡን ) ይዘነጋሉ ፡
ፋጡራንን ያፈቅሩና - ፈጣሪን ይዘነጋሉ ፡፡
አሏህ ከዚህ ተግባር ይጠብቀን ኣሚን ፡፡