Get Mystery Box with random crypto!

የትላንቱ የጎረቤት ሶማሊያ ፓርላማ ውሎ ምን ይመስል ነበር ? • 229 ድጋፍ • 7 ተቃውሞ • 1 | Zena Tube

የትላንቱ የጎረቤት ሶማሊያ ፓርላማ ውሎ ምን ይመስል ነበር ?

• 229 ድጋፍ
• 7 ተቃውሞ
• 1 ድምፀ ተአቅቦ

በትላንትናው ዕለት የጎረቤታችን ሶማሊያ ፓርላማ የሀገሪቱ ጠ/ሚ ባቀረቡት የካቤኔ አባላት ላይ ድምፅ ለመስጠት ተሰብስቦ ነበር።

በዚህም ጠ/ሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ ያቀረቡትን የካቢኔ አባላት በ229 ድጋፍ፣ በ7 ተቃውሞ ፣ በ1 ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በካቢኔያቸው ያካተቷቸው የቀድሞ የአልሸባብ የሽብር ቡድን ምክትል መሪ የነበሩት ሙክታር ሮቦው የሶማሊያ የሀይማኖት ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።

በሌላ በኩል ፤ የቀድሞው የአልሸባብ ሰው በካቢኔ ውስጥ መካተታቸው አሜሪካን እንዳላስደሰታት በአንድንድ የሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን ቢነገርም አሜሪካ በካቢኔው ደስተኛ እንደሆነች በመግለፅ ለፕሬዜዳንት ሼክ ሀሰን ሙሀሙድና ጠ/ሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ እንኳን ደስ አላችሁ ስትል ሶማሊያ በሚገኘው ኤምባሲ በኩል አሳስውቃለች።

አሜሪካ ፤ ለሶማሊያ የምታደርገውን ድጋፎች አጠናክራ እንደምትቀጥልበትም ገልፃለች።

ሀገሪቱ በሶማሊያ የሚኒቀሳቀሰው " አልሸባብ "ን ለመዋጋት ሰፊ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ ሀገራት በቀዳሚነት ስሟ የሚነሳ ሲሆን በኢኮኖሚያዊና ሰብዓዊ ድጋፍ በኩልም በሚሊዮን ዶላሮችን ለሶማሊያ ድጋፍ ታደርጋለች።