Get Mystery Box with random crypto!

Zekarias tadesse official🪕

የቴሌግራም ቻናል አርማ zeeanointed — Zekarias tadesse official🪕 Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zeeanointed — Zekarias tadesse official🪕
የሰርጥ አድራሻ: @zeeanointed
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 425
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የወንድም ዘካሪያስ ታደሰ ኦፊሺያል ገፅ ነው። ገፁን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
በፌስቡክ_https://www.facebook.com/tade555/?referrer=whatsapp
በዩቲዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCn24otLyc8A2Ogo3WVe0aKg

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-28 22:50:38
#የእግዚአብሔር_ሰው_ማን_ነው
በመጋቢ ታምራት ኃይሌ



358 views19:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 07:56:54
#ለማን_ይሆን_ቦታ_የሰጠነው?

“ለመታዘዝ ባሪያዎች እንድትሆኑ ራሳችሁን ለምታቀርቡለት፥ ለእርሱ ለምትታዘዙለት ባሪያዎች እንደ ሆናችሁ አታውቁምን? ወይም ለሞት የኃጢአት ባሪያዎች ወይም ለጽድቅ የመታዘዝ ባሪያዎች ናችሁ።”
— ሮሜ 6፥16
https://t.me/zeeanointed
422 viewsedited  04:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 13:57:05
#ሰው እንዲያያችሁ ከፈለጋችሁ "ፊታችሁን አሳምሩ" #እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት ከፈለጋችሁ ግን "ልባችሁን አሳምሩ"።

If you want someone to see you, "beautify your face," but if you want to please God, "beautify your heart."
https://t.me/zeeanointed

“እግዚአብሔር ግን ሳሙኤልን፦ ፊቱን የቁመቱንም ዘለግታ አትይ፤ ሰው እንዲያይ እግዚአብሔር አያይምና ናቅሁት፤ ሰው ፊትን ያያል፥ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል አለው።”
— 1ኛ ሳሙኤል 16፥7
https://t.me/zeeanointed
521 viewsedited  10:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 20:35:38 #አገልጋይና_ገንዘብ

እውነተኛ አገልጋይ ለመሆን እስከፈለጋችሁ ድረስ የገንዘብን ጉዳይ
ማስተካከል ይጠበቅባችኋል። ኢየሱስም ‹‹አንድ ባሪያ ለሁለት ጌቶች ማገልገል
አይችልም... ስለሆነም ለእግዚአብሔር እና ለገንዘብ በአንድ ጊዜ መገዛት አትችሉም›› ብሏል።
ስለሆነም አገልግሎት እና ለገንዘብ መራወጣችሁ(መንገብገባችሁም)በልዩ ሁኔታ ተለይተው ሊቀመጡ ይገባቸዋል።

እግዚአብሔር የእናንተ ሙሉ ጊዜን እንጂ ትርፍ ሰዓታችሁን ብቻም ከእናንተ አይጠብቅም::

ገንዘብ ደግሞ በህይወታችሁ ውስጥ እግዚአብሔር እንድትተዉ ያደርጋችኋል።

ብዙ ሰዎችም እግዚአብሔርን ከማገልገል ወደ ኋላ የሚቀሩት ለቁሳዊ ነገሮች ባሪያ መሆን ሲጀምሩ ነው።

እነዚህ ሰዎች <<በመጀመሪያ የገንዘብ ችግሬን ከቀረፍኩኝ በኋላ እግዚአብሔርን ማገልገል እጀምራለሁኝ›› ሲሉም ይሰማሉ፡፡ ይሄ ግን ፍፁም ስህተት የሆነ ነገር እና ለዘለዓለም ፀፀት ውስጥ የሚከታቸው ነገር ነው (ከተፀፀቱ ማለቴ ነው)።

ይሄ የገንዘብ ነገርም በጣም ፈታኝ መሆኑን ለማንሳትም ሲል...
ኢየሱስ በምድር ላይ በሚያስተምርበት ጊዜ ላይ ስለ ሲኦል እና ገነት ከማውራት (ከማስተማር) ይልቅ ስለ ገንዘብ ነው ብዙ የተናገረው ‹‹ምድራዊውን ሀብታችሁን በደንብ መቆጣጠር ካልቻላችሁ እንዴትስ ነው እውነተኛው
የስማያዊ ሀብታችሁን መቆጣጠር እንደምትችሉ የምትታመኑት›› ይላል።

ልብ አድርጉ እራሳችሁን ለክርስቶስ ስታስገዙ ገንዘብ የእናንተ አገልጋይ ይሆናል።
ነገር ግን ገንዘብን አገልጋይ ከሆናችሁ የገንዘብ ባሪያ ትሆናላችሁ።

“ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል፤ ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም።” ( ማቴ- 6፥24)

ይሄ ነው እውነቱ!
እስቲ ለጥቂት ደቂቃ ራሳችንን እንመርምረው

ቃሉ ነው የሚናገረን


https://youtube.com/c/ZekariasTadesseOfficial
478 views17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 20:35:34
117 views17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 09:43:19 እንደ ክርስቲያን ለመኖር ካልወሰንን የክርስትና ምልክቶች ያሉባቸው ነገሮች ባናንጠለጥል መልካም ነው፡፡
ከጌታ ጋር ያለኝን ግንኙነት የሚገለፀው በምለጥፋቸው ጥቅሶች፣ በማንጠለጥላቸው መስቀሎች ወይም ቤተክርስትያን መሄዴ አይደለም፡፡ በቃሌም የሽመደድኳቸው ጥቅሶች ፣ያሉኝ የክርስትያን መፅሐፎች፣ ካሴቶች እና ሲዲዎችም አይደሉም::
#የክርስትናዬ ማስረጃ መሆን የሚችለው በፍቅር የማፈራው ፍሬ ነው፡፡

የሚያጋጥማችሁን ሁሉ በተረጋጋ መንፈስ መጋፈጥ እንድትችሉ መጸለይ እንዳለባችሁ እመክራችኋለሁ፡፡ የሚያበሳጩ ነገሮች እንደሚያጋጥሙን የታወቀ ነው። ነገር ግን አስቀድመን ተዘጋጅተን ከሆነ በእርጋታ የመጋፈጥን ብቃት እናገኛለን፡፡

ሁልጊዜ ስሜታችንን በመቆጣጠር ተረጋግቶ መኖር እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ነገሮች እንዳቀዱት አልሄዱ ሲላቸው ቱግ ሲሉ እናያለን።
አንዱ መልካም ተፅዕኖ እንዲኖረን ከሚያደርጉን መንገዶች ውስጥ ነገሮችን
በተረጋጋ መንፈስ መወጣት መቻል አንዱ እንደሆነ አምናለሁ፡፡

መፅሐፍ ቅዱስ ከሁሉም ሰው ጋር በትዕግስት እንድኖር እና ቁጡዎች እንዳንሆን ያስተምረናል (1ተሰ 5፡ 14 ) በሰዎች ዘንድ ከሚኖረን ጥሩ ምስክርነት በተጨማሪ ለራሳችንም ጥሩ ነው፡፡
አብዝተን ታጋሽ በሆን ቁጥር ጭንቀትን እየቀነስን እንመጣለን፡፡
እግዚአብሔር ሰዎች እንዲድኑ ስለሚፈልግ በአስደናቂ ሁኔታ ይታገሰናል( 2ኛ ጴጥ 3፡4) መፅሐፍ ቅዱስ ከሁሉም ሰው ጋር በትዕግስት እንድኖር እና ቁጡዎች እንዳንሆን ያስተምረናል (1ተሰ 5፡ 14 ይመልከቱ)
በሰዎች ዘንድ ከሚኖረን ጥሩ ምስክርነት በተጨማሪ ለራሳችንም ጥሩ ነው።

በድርጊታችን ሰዎችን ሁሌም እናስተምራለን፡፡ ትምህርት ሁሌም በቃል ብቻ የሚደረግ አይደለም፡፡
ሁላችንም በሌሎች ላይ ተፅዕኖ ስላለን በምን መልኩ ተፅዕኖአችንን እንደምናሳርፍ መጠንቀቅ ይገባናል።
የኢየሱስን መስቀል አንገቴ ላይ አንጠልጥዬ የህዝብ አገልግሎት በሚሰጡ ሰዎች ላይ ብበሳጭ እና ፍቅርን ባላሳይ ለእኔም ሆነ ለጌታ የሚጠቅመው ነገር የለም።

እውነቱን ለመናገር ባለፈው አስር ዓመት ሰዎች ሲያደርጉት ያየሁትን ሳስበው ያቅለሸልሸኛል፡፡
በ1ኛ ቆሮ 13 ጳውሎስ ስለ ፍቅር በፃፈው የፍቅር ዋነኛውና መጀመሪያው መገለጫ ትዕግስት ነው። ጳውሎስ ሲፅፍ ፍቅር ይታገሳል ይላል። ፍቅር ታጋሽ ነው ነገሮች እኛ ባቀድናቸው መንገድ አልሄዱ ባሉን ወቅት እንኳን ፍቅር አይለወጥም።

አሜን!
እግዚአብሔር ታጋሾች ያድርገን።
መልካም ቀን

https://youtube.com/c/ZekariasTadesseOfficial
490 views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 12:28:23
#ሳይግባቡ ይጋባሉ ሲግባቡ ይፋታሉ ገበናቸውን መተያያት ሲጀምሩ የእርሱም የእርሷም ጉድ መውጣት ይጀምራል
#ከሰው ምክር ተነስተህ የጀመርከው ጋብቻ በሰው ምክር ይፈርሳል፡፡

#የሰው ምክር ያግዛል እንጂ የእግዚአብሔርን ቃል አይተካም በሰው ልምድና ልማድ ተመስርተህ ጋብቻን ማስቀጠል አትችልም፡፡
የሰው ልምድ ለእራሱ ሰርቶ ይሆናል ለአንተ ግን ላይሰራ ይችላል::
#ሁሉን አትውሰድ የእግዚአብሔር ቃል አይደለምና የሌሎች ሰዎች ልምድ ሙሉ በሙሉ እንደ ትክክለኛ ነገር መውሰድ የለብህም ልምድ መጥፎ ሆኖ አይደለም ከእግዚአብሔር ቃል ማስበለጥ ግን የለብህም
#በእግዚአብሔር ቃል ቤትህን ስራው
ከጠቢቡ ሰለሞን ጥቅስ ተነስተህ ብቻ ቤትህን መስራት ካሰብክ እርሱ እራሱ ስለ ጋብቻ ያለው ቢሰራለት 700 ሚስቶች ባላገባ ነበር ጥቅሱ ለእርሱም....

#አሁን ካሉ የጋብቻ አስተማሪዎችም የሚጠቅምህን ውሰድ ሁሉ አይጠቅምህም ቤት ውስጥ ያለው የኑሮ ዐይነት እንደ አሻራችን ልዩ ልዩ ነው
#የአንዱ ከአንዱ ይለያያል አንደ መላክ ተደርጎ የተሳለባችሁ ቤት ሌላ ሆኖ ሲገጥማችሁ እንዳትደናገሩ
#ትዳር መነሻው ፍቅርና የአላማ መግባባት መሆን አለበት፡፡
#ፍቅርም በዕውቀትና በጥበብ መያዝ አለበት

#ትዳርን ከጥቅም ፡ ከግዜያዊ ፍላጎትና በሌሎች ሰዎች ግፊት የገባችሁበት ቤት ከሆነ ጥቅሙን ስታገኙት ትዳሩን ትጠሉታላችሁ
ቤት ውስጥ የሚያቆያቹና ትዳርን የሚያሰነብተው ገንዘብና መልክ አይደለም፡፡

1 ፍቅር
2 የተሰራ ስብዕና
3 የአላማ አድነት

ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም!!!
አገልጋይ ገዛኸኝ አሰፋ
የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ።
399 views09:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 08:38:55
ከመሬት ተነሥቶ የሚጠላህን ሰው
ከሰማይ ተነስተህ ውደደው

ማንነትን ከማወቅ የሚመነጭ ፍቅር ይህ ነው።
አባ እንዲያው ወደኸናልና ተመሥገን።ሌላውንም እንዲያው እንወዳለን
#እግዚአብሔር #በክርስቶስ #ወዶናል!! ሰዉን መዉደድ ያለብን ሰዉ ስለሆነ ብቻ መሆን አለበት እንዲሁ መሆን አለበት በቃ ጌታ ያስተማረን ይሄንኑ ነዉ !!!"

https://t.me/zeeanointed
“እግዚአብሔርንም በመምሰል የወንድማማችን መዋደድ፥ በወንድማማችም መዋደድ ፍቅርን ጨምሩ።”
(2ኛ ጴጥ 1፥7)
https://t.me/zeeanointed
ሊንኩን በመጫን ቤተሰብ እንሁን
514 viewsedited  05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 08:58:22 https://www.facebook.com/2488061571420496/posts/pfbid02veaBkF7j3X9K7qgYZvEBSuuyGrx348uaZdN9rbuk4tiWGEdPpATtdducUQU91ciVl/?sfnsn=mo&mibextid=LYJLKDz
548 views05:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ