#ርዕስ_አልባ_ግጥም_2 . . በጠብ መንጃ አፈሙዝ የተገዛ ወንበር፣ በትውልድ ደም ላቦት የተገኘ መንበር። . . አንከባሎ ያመጣው እስኪያጠፋው ድረስ፣ ሺ ቅልጥም ቢሰበር የሺ ሰው ደም ቢፈስ። . . ለፌዝ እዘኑ እንጂ ከቶ አትሸበሩ፤ ወገን ገደል ይግባ!! ዝም ብላችሁ ምሩ፣ "ሀገር እግር ትብላ!!" እስኪያቅረን ድረስ ቅዠቱን ደስኩሩ። . . መቼም.... ቀን ያጣመመውን የትውልድ ደባ፣ ሲጎርፈው የኖረ የሻገተ እንባ። በኪነጥበቡ እስኪያለሰልሰው፣ በ"ቢቸግር" ቅኝት ስቀን እናልቅሰው። . . ዘመን ሲያባዝተው ቀን ሲያንቀው አክራሞት፣ ምንም ሆኖ ያልፋል የሰው ልጆች መሞት።!! "........እንላቀስ ጎበዝ........" ዓቢይ ( @abiye12 ) Join & share @sinekal @sinekal @sinekal 467 views15:05