Get Mystery Box with random crypto!

በብሂለ አበው ኩኑ ውሉደ ብርሃን

የቴሌግራም ቻናል አርማ yetwahedolijoch — በብሂለ አበው ኩኑ ውሉደ ብርሃን
የቴሌግራም ቻናል አርማ yetwahedolijoch — በብሂለ አበው ኩኑ ውሉደ ብርሃን
የሰርጥ አድራሻ: @yetwahedolijoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 917
የሰርጥ መግለጫ

<<አንተስ ለእግዚአብሔር ስገድ አለኝ የዚህን መፅሐፍ የትንቢት ቃል አትሰውር ዘመኑ ደርሷልና ፤ እንግዲህስ የበደለውን ይበድሉታል። ያሳደፈውን ያሳድፉታል ጻድቁም ይጽደቅ። ንፁሑም ንፅሑ ይሁን። እነሆ ፈጥኘ እመጣለሁ። ለእያንዳንዱም እንደስራው ከፍየ ብድሩን እከፍለው ዘንድ የምሰጠው ዋጋ ከኔ ጋር ነው (ራዕ ፳፩ ቁ ፰-፲፪ ፤ ኢሳ ፵ ቁ ፲)>>
መልዕክት ካለዎት @TemhrtTewahedoBot

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-11 21:42:35
ጋብቻችሁ የአብርሃምና የሣራ ይሁንላችሁ መልካም ጋብቻ
312 views 卩卂卩丨ㄥㄥㄖ几 , 18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-11 21:42:10
እንኳን ደስ አላቹ ትዳራችሁን እማምላክ ትባርክላችሁ
300 views 卩卂卩丨ㄥㄥㄖ几 , 18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 01:01:36
536 views 卩卂卩丨ㄥㄥㄖ几 , 22:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-09 14:22:09 ልደታ ለማርያም

ድንግል ሆይ ! ያንቺ መወለድ በእውነት ድንቅ ነው ! በዘር በሩካቤ ፣ በሕግ በሥርዓት ተወለድሽ ። ወላጆችሽ እግዚአብሔርን ይፈሩ ነበርና ከእግዚአብሔር ለምነው አገኙሽ ። የእግዚአብሔር እንድትሆኚ ፣ ለእግዚአብሔር ሊሰጡሽ አንቺን መውለድ ተመኙ ። የእግዚአብሔር እናት እንደምትሆኚ ፣ ፈጣሪን እንደምትወልጂ ያውቁ ይሆን ? እንበለ ዘርዐ ብእሲ እንደምትወልጂ ተገንዝበው ይሆን ?

ከገቦ አዳም ሔዋን ተገኘች ፣ አንቺ ግን ከኢያቄምና ከሐና ተወለድሽ ። ሔዋን አቤልና ቃየን የሚባሉ ደግና ክፉ ልጆች ወለደች ። አንቺ ግን ኃጥአንን በቸርነቱ የሚያጸድቀውን ወለድሽ ። ቤተ መቅደስ ሳለሽ ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱሽ ። የፊተኛው መቅደስ ክብር ሲያበቃ ያንቺ ክብር ግን ላያልፍ ይኖራል ። የሚጠሉሽ ሊያጠፉሽ አልቻሉም ። ኑሮሽ ብዙ ስጋት ፣ ስለ ልጅሽ ብዙ ጭንቀት ነበረው ። ያለ ወንድ ዘር ስንጸንሺ ጭንቀት ነበረ ። በልጅሽ ምክንያት የቤተ ልሔም ሕፃናት ሲያልቁ ነፍስሽ ተጠብባ ነበር ። የግብጽን በረሃ ልጅሽን ታቅፈሽ ስታቋርጪ ፣ አገር አልባ ሁነሽ በምድረ አሕዛብ ስትቀመጪ ፣ በልጅሽ ብዙዎች ሲሰናከሉ ፣ ደቀ መዛሙርቱ ሲከዱት ፣ ዓለም ተባብሮ ሲሰቅለው አንቺ በዚህ ሁሉ ውስጥ መስቀልን ተሸክመሽ ታለቅሺ ነበር ። እኛ የአምላክ ተከታይ ሁነን ለምን ጎደለብን እንላለን ። አንቺ ግን የአምላክ እናት ወላዲተ አምላክ ሁነሽ ሁሉን ስታጪ አልተከፋሽም ። አሳብሽ ለአንድ ቀን ምድራዊ አይደለምና ። እኛ ድንግል በሥጋ ብንሆን እንመኛለን ። አንቺ የደናግል መመኪያ ግን ፣ ድንግል በሥጋ ፣ ድንግል በሕሊና ነሽ ። ደናግል ደረቅ ዛፍ ነን እንዳይሉ ድንግል የሆንሽው አንቺ አምላክን ወለድሽ ። ከሐዋርያት ይልቅ የሰበክሽ ፣ ከሰማዕታት ይልቅ መከራ የተቀበልሽ ድንግል ሆይ ፣ ያንቺ ልደት የተባረከች ናት ።

ለእኛ ለምንወድሽ በረከትሽ ይድረሰን !

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን

ግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም.
684 views 卩卂卩丨ㄥㄥㄖ几 , 11:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-09 10:53:12
የልደትሽ ቀን ልደታችን ነዉ። እንኳን አደረሳችሁ
481 views Ⓕⓘⓢⓔⓗⓐ , 07:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 21:33:53 ዳግማይትንሳኤ ማለት ዳግም መነሳት (ሁለተኛ መነሳት)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በስምንተኛው ቀን በዕለተ እሁድ ደቀ መዛረሙርቱ አይሁድን ፈርተው በተሰበሰቡበት ዝግ ቤቶ "ሰላም ለእናንተ ይሁን "ብሎ ዳግም ስለ ተገለጠ #ዳግማይ\ትንሳኤ ተብሏል ።
ሁለተኛለምንተገለጠ?

ለሐዋርያው ቶማስ ትንሳኤውን ለማሳመን

የጌታችን ትንሳኤ ቶማስ ስለ ተጠራጠረ ጌታችን ቶማስ በተገኘበት ዝግ ቤት ተገልጦ ለቶማስ ና ወደኔ የተቸነከረውን እጄና ጉኔን ዳስስ ብሎታል

ቶማስም የተቸነከረው እጁን አይቶ የተወጋውን ጉኑ በእጁ ዳስሶ የጌታችን ትንሳኤ አምኗል ።ሃገረ ስብከቱም በሕንድ ስለ ነበረ ተጋድሎውም የፈጸመው እንዲሁም ሰማዕትነት የተቀበለው በሕንድ ነው ።ያቺ የጌታችንን ጎን የነካች (የዳሰሰች)እጅ ሳትበሰብስ ከታቦት ጋር በመንበሩ ላይ ተቀምጣለች ።እስካሁን ድረስ የሕንድ ሊቀ ጳጳስ ሲሾም በዛች እጅ ተመርጦና ተባርኮ እንደሚሾም አንዳንድ ሊቃውንት ይናገራሉ

ሰንበትን ሊያጸናልን

የአይሁድ ሰንበት፣እግዚአብሔር 22 ፍጥረታትን ፈጥሮ ያረፈባትና እረፉባት ብሎ ያዘዘን ሰንበት ቀዳም(ቅዳሜ)ናት ።በሐዲስ ኪዳንም ጌታችን የተጸነሰባት ፣ከሙታን መካከል የተነሳባት፣አንዲሁም ደግሞ ለማጽናት ሁለተኛ የተገለጠባት(ዳግማይ ትንሳኤ)፣መንፈስ ቅዱስ የወረደባትና ሐዋርያት ከመጀመርያዋቹ ክርስቲያኖች ጋር በኅብረት ሆነው መንፈሳዊ ስራዋች የሚሰሩባት ቀን ዕለተ እሁድ ነበረች ።ቤተ ክርስቲያናችን ለቅዳሜ ቀዳሚት ሰንበት ለእሁድ ደግሞ ሰንበተ ክርስቲያን እያለች ለሁለቱም ቀናት እኩል ታከብራቸዋለች ።ጌታችንም ይቺ ቀን እረፍትነቷን ለማጽናት ሁለተኛ የተገለጠባት ቀን ናት ።እረፍት ስንልም ስራችንን ትተን ቁጭ ብለን (ተኝተን)የምናሳልፈው ማለት አይደለም ።እንደውም ከማንም ቀን በላይ አብዝተን መንፈሳዊ ስራዎች የምንሰራባቸው ቀናት ናቸው እንጂ

ምትሐት አለመሆኑ ለማስረዳት

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምትሐት እንዳልሆነና ቀድሞ የተዋሃደው ስጋና መለኮት ፣ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑ ለማስረዳት ለሁለተኛ ጊዜ ተገልጦላቸዋል ።በዝግ ቤት መግባቱ ደግሞ መለኮት እንዳልተለየውና ስጋ ብቻው እንዳልሆነ ለማስረዳት ነው ።
"ብጹዓን እለ እንዘ ኢይሬእዩ የአምኑ"
(ዮሐ20:29)

የተሣተውን ፤ የተረሳው፤ የተገደፈውን፤ የነጠፈውን በቀና መንፈስ አቃንታቹ አንብቡት
ስለ ማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን
664 views 卩卂卩丨ㄥㄥㄖ几 , edited  18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-26 22:26:03 ማዕዶት!

☞ለፈውስ የሚዳርግ በሽታ? ወይስ ለበሽታ የሚዳርግ ፈውስ?

በ Ethio Beteseb Media



527 views▂▃▄▅▆▇█▓▒░𝕤𝕚𝕪𝕦░▒▓█▇▆▅▄▃▂, 19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 21:11:42 ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡-

#ሰኞ- ማዕዶት ይባላል፡-
ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን

#ማክሰኞ- ቶማስ ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29

#ረቡዕ- አልአዛር ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን

#ሐሙስ- አዳም ሐሙስ ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን

#አርብ- ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና

#ቅዳሜ- ቅዱሳት አንስት ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል

#እሁድ- ዳግም ትንሳኤ ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል

@yetwahedolijoch
448 views 卩卂卩丨ㄥㄥㄖ几 , edited  18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 12:27:09 #መልካም_ፋሲካ

- "ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ"

የትንሣኤ መዝሙር
405 views▂▃▄▅▆▇█▓▒░𝕤𝕚𝕪𝕦░▒▓█▇▆▅▄▃▂, edited  09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 10:51:04 "ክርስቶስ ተንስዓ እሙታን"
"በዓቢይ ሀይል ወስልጣን"
"አሠሮ ለሠይጣን "
"አግዐዞ ለአዳም
"ሠላም "
"እምይእዜሠ "
"ኮነ"
"ፍሠሀ ወሠላም"

እንኳን ለጌታችን ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል እና እንኳን =ከሲኦል ወደ =ገነት ተሸጋገርን ተሸጋገራችሁ ከዘመነ ፍዳ ወደ ዘመነ ፍስሐ በሰላም አደረሳችሁ። የክርስቶስን ሞት ድል አድርጎ መነሳት ስናስብ በዛውም የእኛንም የትንሳኤ ዘመን እናነሳለን።ያኔ በሲኦል ቀንበር ስር ሆነን ለ5500 ዘመን ስንቀጣ የነበረ ቢሆንም ክርስቶስ በቀራንዮ አደባባይ ላይ እርቃኑን ስለሰው ልጅ መዳን ብሎ ተሰቅሎ በአዲስ መቃብር ተቀብሮ በነፍስ ወደጥልቁ በመውረድ ነፍሳትን ወደ ገነት አሸጋግሯል። ታድያ ዛሬም እኛ ለወራት ሥጋችንን በፆም በፀሎት በስግደት ስንቀጣው ቆይተን ዛሬ ላይ ከትንሳኤው እለት ደርሰናል እና ለዚህ ያደረሰን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። ነገር ግን ማስተዋል ያለብን ያኔ ከሲኦል ቀንበር ወደገነት እግዚአብሔር አምላክ ሲያሸጋግረን ትንሳኤው እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት እና እለት እለት ከእርሱ ጋር የምንኖርበት ነበር።ታድያ ዛሬ ላይም እኛ ትንሳኤውን የምንጨፍርበት ከልክ በላይ በልተን የምንጠግብበት ዝሙት የምንፈፅምበት ከደጁ የምንርቅበት ሳይሆን እንደቀድሞው ትንሳኤ ከእርሱ ጋር በይበልጥ የምንኖርበት ነው።ስለዚህ ሁሉንም ነገር በልክ እና በአግባብ እንድናረገው ወንድማዊ ምክሬን እነሆ።

ሞታችንን ወስዶ ህይወትን ለሠጠን ለጌታችን ትንሣኤ እንኳን አደረሳቹ ፣ አደረሰን።

መልካም የትንሣኤ ዘመን ይሁንላችሁ ፣ ይሁንልን
የአመት ሰው ይበለን
መልካም በዓል
❖ የድንግል ማሪያም ጥበቃ ምልጃዋ አይለያቹ
​✞ @DenglMaryam21 ✞
500 views▂▃▄▅▆▇█▓▒░𝕤𝕚𝕪𝕦░▒▓█▇▆▅▄▃▂, 07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ