Get Mystery Box with random crypto!

#ቁርጥራጭ ሀሳቦች በየቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ yetisolomon — #ቁርጥራጭ ሀሳቦች በየቲ
የቴሌግራም ቻናል አርማ yetisolomon — #ቁርጥራጭ ሀሳቦች በየቲ
የሰርጥ አድራሻ: @yetisolomon
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 895
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የተለያዩ ፅሁፎችን ፣የመፅሀፍ ጥቆማዎች ፣ ቁርጥራጭ ሀሳቦች ፣ በንባብና በመፅሀፍት ዙሪያ እንፅፋለን ፣እናጋራለን ፣ የተለያዩ ሀሳቦችን እናሸራሽራለን !

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-02-12 22:15:59 ሊዎ ቴልስቶይ በማስታወሻ ደብተሩ ላይ ይህንን ቁምነገር ጽፏል። ላካፍላችሁ፦

በልጅነቴ ከእናቴ ጋር ዘወትር ትያትር ቤት እንሄድ ነበር። ቤተሰቦቼ ቢጠሯቸው የማይሰሙ ሃብታም ነበሩ። ሞስኮ ውስጥ በክረምት በረዶ ያለማቋረጥ ይወርዳል። ያኔ እናትና ልጅ ትያትር ቤት ውስጥ ነን።

ትያትር ቤቱ የትራጄዲ ተውኔት የሚያሳይ ከሆነ እናቴ ታለቅሳለች። እንባ በአይኖቿ ግጥም ብሎ በጉንጮቿ ያለማቋረጥ ይወርዳል። እኔ በልቤ 'እናቴ ምን አይነት ሩህሩህ ሴት ናት!' ብዬ አስባለሁ።

ተውኔቱ አልቆ ከትያትር ቤት ስንወጣ ሹፌራችንን መኪናው ውስጥ በቅዝቃዜ ተኮራምቶ እናገኘዋለን። እንግዲህ ሹፌራችን መኪናውን ጥሎ መሄድ አይችልም። መቼ ከትያትር ቤቱ እንደምንወጣ አይታወቅም። ሁሌም ዝግጁ እና ንቁ ሆኖ መጠበቅ አለበት። እንደዚያ ተጨብጦ፣ ተኮራምቶ እናቴ ዘወር ብላ እንኳን አታየውም። አንዳንዴ ሹፌራችን በቅዝቃዜ ሞቶ በሌላ ሹፌር የሚተካበት ግዜ ነበር። እናቴ አንድ ዘለላ እንባ እንኳን አታፈስም። በመጨረሻ የእናቴ እንባ የማስመሰልና የሃሰት መሆኑን ተረዳሁ።

Tewodros Shewangizaw
511 views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-12 22:15:18 ዲዮጋን መልከ ጥፉ ነው፤ ፉንጋ ያንስበታል፡፡ ዲዮጋን መልከ ጥፉነቱን ድብን አድርጎ ያውቃል፡፡ ዲዮጋን ፈላስፋ ነው - ህይወትን የሰው እውቀት ማነስ አከበዳት እንጅ፣ በራሷ ቀላል ነች ብሎ ያምናል፤ ያመነውንም ይኖራል፡፡ ጎዳናው ላይ፣ ቦይ ውስጥ እንዳሻው ይተኛል፡፡ ያገኘውን ይበላል፡፡ ቁራጭ ጨርቅ ያሸርጥና ራቁቱን ይኖራል፤ ኃሳቡን ግን ማንም አይጋፈጠውም፡፡ ብዙ አይናገርም፡፡ ከተናገረም በጥቂት ቃላት አሳቢያንን እረፍት የሚነሳ ጠጣር ነው፡፡
እና አንድ ቀን በአቴንስ የተወራላት ቆንጆ (Miss Athena) የዲዮጋንን የፍልስፍና ሊቅነት ሰማች፡፡ ያለበት አፈላልጋ ሄደች፡፡ ዲዮጋን በጀርባው ተንጋሎ፣ ጉልበቱን አመሳቅሎ በጎዳናው ዳርቻ አፈሩ ላይ ተኝቶ ፀሐይ እየሞቀ አገኘችው፡፡ " የተወደድከውና የተከበርኸው ፈላስፋ ሆይ እነሆኝ ወደር ያልተገኘላት ያቴንሷ ውብ አንተን ብዬ መጣሁ" አለችው፡፡ ዲዮጋን ቀናም ብሎ ሳያያት " በአቴና ምድር ወንድ እየተጋፋ ከስርስርሽ እንደሚርመጠመጥ ሰምቻለሁ፡፡ እኔ ዘንድ ምን አመጣሽ?" አለ፡፡
ውቧም እየተሽኮረመመች (አይ አመል!) " ካንተ ልጅ መውለድ እፈልጋለሁ"
" አገሩን የወረረው ወንድ አይደልምን? ምን እኔ ዘንድ አመጣሽ ታዳ?" አለ ዲዮጋን በቸልታ፡፡
" የምወልደው ልጅ አባቱ አንተ እንድትሆን የፈለኩት ያንተን አይነት አእምሮና የእኔን አይነት ውበት እንዲኖረው እና ሙሉ እንዲሆን ስለምፈልግ" አለች በልበ ሙሉነት፡፡
ዲዮጋን እንደተኛ ተንጠራራ ( ሳስበው የተንጠራራ ይመስለኛል!) " በተቃራኒው ልጅሽ የእኔን መልክና ያንችን አእምሮ ይዞ ቢወለድ ምን ያህል አስቸጋሪ ኑሮ እንደሚገጥመውስ አላስብሽምን?" አለና ተነስቶ መቀመጫው የቃመውን አቧራ እያራገፈ ፕሌቶ ወደሚያስተምርበት ጉባኤ ከተማሪዎች ጋር ሊሳለቅበት ጉዞውን ቀጠለ፡፡
እንግዲህ ምን ልል ፈልጌ ነው? አትጣሉ፤ ከተጣላችሁም እውቀት ያለው "ዲዮጋን" ጋር ይሁን ነገራችሁ - ከፀባችሁም እውቀት ታተርፋላችና!
# መውጫ ፦ ውቧ አቴናዊትም በንደት ወደ ንጉሱ ልጅ ሄዳ ወለደች፡፡ ልጇም ፖለቲከኛ ሆነ፡፡ ፈላስፋውም " መሪዎች ፈላስፋ ይሁኑ፤ ወይም ፈላስፎች መሪ ይሁኑ፤ አለዚያ አገር ትጠፋለች" አለ።

Dostoyevsky
452 views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-08 20:07:27

385 views17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-07 16:09:20 { ስለ ፌመንዝም ምን አስባለኹ ?}

' ፌመንዝም' በተለይ ላደጉት አገራት ለሴቶች እኩልነት ከፍተኛ ሚና እንዳበረከተ የማይካድ ሀቅ ነው። መምረጥ መመረጥ ቀርቶ በሞተሰማሩበት ሙያ በፆታቸው ምክንያት ብቻ እኩል ክፍያ አለማግኘትን ጭምሮ በርካታ ፖለቲካዊና ሰብአዊ መብቶቻቸውን ከመነጠቅም አውጥቶአቸዋል ።

አሁንስ ? በግል እይታዬ 'ፌመንዝም 'እንደማንኛውም የመብት ጥያቄ ከእኩልነት ወደ በላይነት ፣ ከመብት ጥያቄ ወደ ጥላቻ እየተሸጋገረ እንዳለ ይታየኛል ።

ይህንንም ለማረጋገጥ እርቀት ሳንሄድ እዚሁ 'ሶሻል ሚዲያ' ላይ ትዳርን ፣የፍቅር ግንኙነትን ፣ወንድነት እንደ አንዳች አውሬ የሚያሳዩ ከትዳር ይልቅ 'ሲንግል ማምነትን' የሚመርጡ ሴቶች መበራከት ማስተዋል ይቻላል ።



ታዲያስ ምን ይሻላል ? እንደኔ እንደኔማ የሴት፣የህፃን ፣የጥቁር ፣ የእንትን ብሄረሰብ ፣ የእገሌ ሀይማኖት የሚባሉ ንጥል መብቶች ይልቅ( የሰው ልጅ መብት )የሚባል ለማንኛውንም ሰው እኩልነት የሚዘረጋበት መርህ ቢቀድም ብዬ እመኛለኹ።

#ቁርጥራጭሐሳቦችየቲ
468 views13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-02 17:50:08 https://www.facebook.com/groups/1019338701980123/?ref=share


ከንባብ ባሻገር ጤናችንንም ለመጠበቅ ጤናማ የህይወት ዘይቤ እንዲኖረን ብንማማርስ?
479 views14:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-02 17:47:50 በንባብ እራሳችንን ከማጎልበት ባሻገር ለአካላችን ለ ጤናችንም መጨነቅ አለብን ። ጤናማ የህይወት ዘይቤን እንከተል ተቀልቀሉን
445 viewsedited  14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 21:59:57 ይህን ቻናል ጎብኙትስቲ
481 views18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 21:59:26 #Brand #Clothes #Watches #Cosmotics
https://t.me/ephodfashion
417 views18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-28 13:00:26
498 views10:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-28 13:00:22 {ትላንት የጠየቃችሁኝን ጥያቄ እኔ ደሞ Tewodros Shewangizaw ጠይቄው ይህን መልስ ሰጥቶኛል ። ጥያቄያችሁ በቂ ምላሽ እንዳገኘ ተስፋ አደርጋለሁ }

ጥያቄ፦ ቴዲ " የአገራችን ደራሲዎች ለምን ደሃ ሆኑ ? በድርሰታቸውስ ውስጥ ለምን ድህነት ይገለፃል ?".አንተ ምን ትላለህ?

አጭሩ መልስ፦ ድርሰት ወፍራም እንጀራ አያበላም።

ረዥሙ መልስ፦ አብዛኛዎቹ ቀደምት የኢትዮጵያ ደራሲዎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣኖች፣ ሚኒስትሮች ወዘተ ነበሩ። ከበደ ሚካኤል በሃይለስላሴ ዘመነ መንግስት የትምህርት ሚኒስትር ነበሩ። በአሉ ግርማ የደርግ ማስታወቂያ ሚኒስትር ዋና ፀሀፊ ነበር። መኮንን እንዳልካቸው ሚኒስትር ነበሩ። ልጃቸው እንዳልካቸው መኮንን የሚኒስትር ልጅ፣ ራሳቸውም በስማቸው በተሰየመው የእንዳልካቸው ካቢኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ነበሩ። ሀዲስ አለማየሁ በተባበሩት መንግስታት፣ በእንግሊዝ እና እስራኤል የኢትዮጵያ አምባሳደር ነበሩ።

አፈወርቅ ገብረየሱስ ራሱ እንደ ሚኒስትር ሊቆጠሩ የሚችሉ፣ በሁለት ሃገሮች ጉዳይ ላይ በማማከር እጃቸውን ያስገቡ ሰው ነበሩ። ብላቴን ጌታ ህሩይ ወልደሥላሴ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣንና ባህላዊ አለባበሳቸው በራሱ ግዝፈትና በሚመለከታቸው ሰው ላይ ጫና የሚያሳድር፣ ከላይ ካባ ከውስጥ ቀጭን ኩታ የማይለያቸው ነበሩ። ሀዲስ አለማየሁ በባለቤታቸው ክበበ―ፀሐይ ለተሰየመው ወላጅ ለሌላቸው ልጆች ማሳደጊያ እንዲሆን 3000 ካሬ ሜትር ቤታቸውን የሰጡ ነበሩ።

ይህንን ሁሉ የዘበዘብኩት ያለ ምክንያት አይደለም። እነዚህ ሁሉም ከላይ የተጠቀሱት ደራሲዎች በመንግስት ከፍተኛው መዋቅር ውስጥ ሆነው ወፍራም እንጀራ የሚያበላ ዋና ስራ ነበራቸው። ድርሰት ዝንባሌያቸው እንጂ እንጀራ መጋገሪያቸው አልነበረም። ኑሯቸውም የተድላና የድሎት ነው። የገንዘብ ጉዳይ የሚያስጨንቃቸው ሰዎች አልነበሩም። ለመፃፍ የሚሆን ግዜ ካጡ እንጂ የመፃህፍቶቻቸው መሸጥ አለመሸጥ የሚያስጨንቃቸው አልነበሩም። ገበታቸው ሙሉ ቤታቸው ምቹ ነበር። በአጭሩ ድርሰት መተዳደሪያቸው አልነበረም።

ድርሰት መተዳደሪያቸው የነበሩ ደራሲዎችስ?? ለዚህ አብይ ምሳሌ የሚሆነን ጋሽ ስብሐት ነው። ስብሐት እንኳን ሞልቶ ተርፎት የድሎት ኑሮ ሊኖር ይቅርና ከወር ወር የሚደርሰው በመከራ ነው። ይህንን ቅልብጭ አድርጎ የሚያሳይ አጭር ታሪክ ልንገራችሁ፦

ተስፋዬ ገብረአብ ቀሽት የነበረውን እፎይታ መፅሄት በሚያዘጋጅበት ግዜ ስብሀት ገብረእግዚአብሔርን፣ ደምሴ ፅጌን፣ የሺጥላ ኮከብን ወዘተ ወዘተ አምደኛ አደረጋቸው። እነዚህ ጋዜጠኛዎችና ደራሲዎች በችሎታቸው የተመሰገኑ ሲሆኑ ከያሉበት በባትሪ ፈልጎ ያሰባሰባቸው ተስፋዬ ራሱ ነው። ታዲያ አንድ ቀን ጋሽ ስብሐት አለቃው ተስፋዬ ገብረአብ ጋር ይመጣና እንዲህ ይለዋል፦

"ያለፈውን ወር ደሞዝ ስለወሰድኩ ልጠይቅህ አልችልም። የሚቀጥለውን ወር ደሞዜንም ልጠይቅህ አልችልም። እሱንም ወስጄዋለሁ። ስለዚህ ለምን ታታሪ ሰራተኛ ብለህ አትሸልመኝም"

የተስፋዬ ገብረአብ ሳቅ ጆሮ አደንቋሪ እንደነበር አይጠረጠርም። ይህንን ታሪክ ለምን ለመንገር ፈለግኩ? በደራሲነት ችሎታ ስብሐትን የሚገዳደር እግር እስኪነቃ ቢፈለግ አይገኝም። ድርሰት የቁስ ሃብታም የሚያደርግ ቢሆን ኖሮ ስብሐት ቱጃር ይሆን ነበር።

ወደ መሰረታዊው ጉዳይ እንምጣ። እንደ ሃገር ማህበረሰባችን ለሃሳብ፣ ለጥበብ የሚሰጠው ቦታ የወረደ ነው። የማንበብ ባህል ደካማ ነው። ለ100 ሚሊየን ህዝብ አስር ሺህ ኮፒ መፃህፍት ተሽጦ ካለቀ እንደ ተአምር ይወራል። አንባቢ እንደ እብድ፣ ደራሲ እንደ ስራፈት የሚታይበት ሃገር ነው። የኢኮኖሚ ድህነት አለ፣ የአስተሳሰብ ድህነት አለ። የህትመት ዋጋ ውድ ነው። ወረቀት ይቀረጥበታል። መንግስት ደራሲዎችንና የንባብ ባህልን አያበረታታም። የደራሲዎች ሽልማት አያዘጋጅም። ቤተመፃህፍት በብዛት የሉም። የመፅሀፍት መደብሮች ጥቂት ናቸው። የነበሩትም እየተዘጉ ካፌና ምግብ ቤት ይከፈትባቸዋል። ከአእምሮው ይልቅ ለሆዱ የሚጨነቅ ማህበረሰብ እና ትውልድ ነው ያለን። ችግሩ ስር የሰደደና ዘርፈ ብዙ ነው። ታዲያ ደራሲዎች በየት በኩል ድሃ አይሁኑ?! በእርግጥ ድርሰት የንግድ መስክ አይደለም። ይሁን እንጂ ለሙሉግዜ ደራሲ ብቸኛ መተዳደሪያው ነው። ደራሲ እንደ ሁላችንም ሰው ነው። ይበላል፣ ይጠጣል፣ ይለብሳል። ለዚህ ደግሞ ገንዘብ ያስፈልጋል። ማጠቃለያው ድርሰት እዚህ ሃገር እንኳን ሙሉ፣ ግማሽ እንጀራ አያበላም ነው!

(ምስሉ ተረት ሰፈር ይገኝ የነበረው የጋሽ ስብሐት ቤት ነው። ይሄ ምስል የኢትዮጵያ ደራሲዎች ድህነትን ጠቅልሎ የሚገልፅ አንድ ፎቶ ነው)
448 views10:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ