ሀገር ስጪኝ... (በላይ በቀለ ወያ) . . ለጠየቅሽኝ እንቆቅልሽ ፣ ሲጠፋብኝ እኔ መልሱ "ሀገር ስጠኝ" የምትዪኝ ፣ መልስ አታውቂም አንቺ ራሱ! ።። ሁሉ ሀገሩን ተከፋፍሎ፣ ክልልሎችን እያጠረ ኬት አምጥቼ ሀገር ልስጥሽ ?፣ ሀገር ማለት "ሰው" ነበረ። ሰውም በዘር ተከፋፍሎ ፣ ሀገር መሆን አቅቶታል ገድሎ ሚኖር ተበራክቶ ፣ ሞቶ ሚያኖር ካገር ጠፍቷል! ።።። ይህን እውነት እያወቅሽው ... "ሀገር ስጠኝ" አትበዪኝ ፣ በእንቆቅልሽ ልትለውጭኝ ክልልና ዘር ነው ያለኝ ፣ እሱን ወስደሽ ሀገር ስጭኝ! ። t.me/yetesebere 234 views16:59