Get Mystery Box with random crypto!

የሺዋስ መኳንንት Yeshiwas Mekuanint

የቴሌግራም ቻናል አርማ yeshiwas1 — የሺዋስ መኳንንት Yeshiwas Mekuanint
የቴሌግራም ቻናል አርማ yeshiwas1 — የሺዋስ መኳንንት Yeshiwas Mekuanint
የሰርጥ አድራሻ: @yeshiwas1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 417
የሰርጥ መግለጫ

ትምህርታዊ ጽሑፎችና እንደአስፈላጊነቱ ማስታወቂያዎች ይለጠፉበታል።

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-27 11:20:14
My second SOUL, just at the age of three years.
135 viewsYeshiwas, 08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 20:16:39
በኢትዮፋጎስ የመጽሐፍ ማእከል አሳታሚነት የታተመው ሃይማኖት አበው በይዘትም በአቀራረብም ልዩ ሆኖ ገበያ ላይ ውሏል።

አዘጋጅ፦ ሊቀ ሊቃውንት አባ ሳሙኤል /በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ቤተ ጉባኤ የጉባኤ ቤቱ መምህር/
አከፋፋይ:- ኢትዮፋጎስ የመጽሐፍ ማእከል
አድራሻ:- 4ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ሕንጻ በሚገኘው ማከፋፈያችን ወይም
0111261146 ላይ በመደወል መውሰድ ትችላላችሁ።
165 viewsYeshiwas, 17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 17:57:47 ከየትኛው ቀን ላይ ነን?

ሶሎሞን ሰኞ ዕለት ተወለደ፤
ማክሰኞ ከረሰተነ (ክርስቲያን ሆነ)፤
ረቡዕ ጋብቻ መሰረተ፤
ሐሙስ ዕለት ታመመና አመሻሹ ላይ ሆስፒታል ገባ፤
ዓርብ ዕለት ሕመሙ ጠናበትና ሌሊት ለቅዳሜ አጥቢያ ሞተ፤
ቅዳሜ እረፋዱ ላይ ተቀበረ።

እኛሳ ደግሞ የትኛው ቀን ላይ ነን? ሰው በዚህ ምድር ላይ የሚኖረው ስድስት ቀናትን ያህል ብቻ ነው። ሰባተኛዋ ቀን የዕረፍት ቀን ናት፤ እርሷም የመንግስተሰማያት ምሳሌ ነች። ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ያሉት ቀናት በዚህ ዓለም ላይ ያለውን ሕይወታችንን የሚወክሉ ሲሆን ሰባተኛዋ ዕለት ዕለተ ሰንበት ደግሞ ከሞት ባሻገር የምንኖረውን ሕይወት ትወክላለች። በስድስቱ ቀናት ውስጥ ዕረፍት እንደሌለ ሁሉ ሰውም በዚህ ምድር ላይ ያለውን እድሜውን አጠናቅቆ እስኪሄድ ድረስ ምንም እረፍት የለውም። ከቀናት ሁሉ ዕለተ ሰንበት እንድትበልጥ ወይም ስድስቱ ቀናት ተጠራቅመው ከዕለተ ሰንበት ጋር ሊወዳደሩ እንደማይችሉ ሁሉ በመንግስተ ሰማያት የምንኖረው የወዲያኛው ዓለም ሕይወታችንም አሁን ከምንኖረው ሕይወት ጋር ሲወዳደር ብልጫውን ስንኳንስ መናገር ማሰብ እንኳን አይቻልም።
ቅዱሳት መፃሕፍት በዚች ምድርና በገነት መካከል ያለውን ልዪነት "ገነትሰ ልዕልት ይእቲ እምዛቲ ምድር መጠነ ምሥራቅ እምዕራብ" /የገነት ልዕልና ከዚህ ምድር ጋር ሲነፃፀር ምሥራቅ ከምዕራብ የሚርቀውን ያህል ነው/ በማለት ሲገልጡ፣ ስለኢየሩሳሌም ሰማያዊትን ግን "ዐይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን ትመስላለች" ከማለት ውጭ ምንም አላሉም። ለሰው ልጅ የመጨረሻውና አንደበት ሊረዳው የማይችለው ታላቁ ደስታ /incomprehensible pleasure/ መንግስተ ሰማያትን ማየት ነው። ከፀሐይ በታች አዲስ ነገር የለምና በዚህ ምድር ላይ ምንም surprise የለም።
በዚህ ምድር ላይ በአፀደ ሥጋ ከምንኖረው ከሰባት ቢሊየን በላይ ሰዎች ውስጥ በአሁኗ ሰዓት ከስድስቱ ቀናት ውስጥ በአንዷ የምንገኝ ነን፤
፩ኛ. ሰኞ ላይ ያሉ አሉ እነርሱም በሥጋ ልደት ወደ ዚህ ምድር ከመጡ በኋላ ማክሰኞ ላይ ያልደረሱ ኢጥሙቃን ናቸው።
፪ኛ. ማክሰኞ ላይ ያሉ አሉ፤ እነርሱም እየቀደሱ እያስቀደሱ እየቆረቡም ክርስትናን በተግባር የሚኖሩ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው። እነዚህ ሰዎች ማክሰኞ ላይ ሆነው ማለት ክርስትናቸው ላይ ፀንተው ቆመው ስለሌሎች ቀናት ረስተው ማለት በዚህ ምድር ላይ ስላላቸውና ስለሚኖራቸው ሕይወት ሳይጨነቁ ከቀናት ሁሉ ለምትበልጠው ለእሁድ ብለው ማለት ለሚበልጠው ለሰማዪ ሕይወታቸው የሚሠሩ ናቸው።
፫ኛ. ረቡዕ ላይ ያሉ አሉ፤ እነዚህ ደግሞ ክርስትናውን ትተው ለትዳር ብቻ ወይም ለመብል ብቻ ወይም ደግሞ ለሌላ ለዚህ ዓለም ትርኪ ምርኪ ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ ዓለም ቅርጥፍጥፍ አድርጋ የበላቻቸው ሰዎች ናቸው።
፬ኛ. ሐሙስ ላይ ያሉ አሉ፤ እነዚህም የታመሙ ግን ደግሞ ህመማቸውን ችለውና ውጠው የሚውተረተሩ፣ መታመማቸውንም ሰው ያላወቀላቸው ምስኪኖች ናቸው /መታመሙን ሰው ያልተረዳለት ስንት በሽተኛ አለ መሰላችሁ/።
፭ኛ. ዓርብ ላይ ያሉ አሉ፤ እነርሱም በጠና ታመው በአልጋ ቁራኛ በደዌ ዳኛ የተያዙና በሞትና በሕይወት መካከል ያሉ ናቸው።
፮ኛ. ቅዳሜ ላይ የምናገኛቸው ደግሞ ሞተው በመቀበር ላይ ያሉ ናቸው።
እኛስ የትኛው ቀን ላይ ነን? ገና እንደተወለድን ምንም መኖር ያልጀመርን ሰኞ ላይ ነን? ወይስ ክርስትናው ውስጥ ማክሰኞ ላይ ነን?
ዓለም የዋጠችን የዕለተ ረቡዕ ሰዎች ነን ወይስ የዕለተ ሐሙስ ታማሚዎች?
አልጋ ላይ ያለን የዓርብ ዕለት ሰዎች ነን ወይስ ተስፋ ቆርጠን ሞተን በመቀበር ላይ ያለን የቅዳሜ ሰዎች?
በድጋሜ የትኛው ቀን ላይ ነን?
155 viewsYeshiwas, 14:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 08:36:39
An infant with gunshot wound on his abdomen, and another one chained with hand cuffs and ready for shooting. It is currently happening in the land of origins, Ethiopia. NO DOUBT, IT IS CRUELTY AT ITS BEST.

ግን ምን ዓይነት ትምህርት ብንማር ነው እንዲህ ለመሆን የበቃነው?
እንዴትስ ብንጨክን ነው 'ስምህ ማን ነው?' ተብሎ ቢጠየቅ ስሙን እንኳን አቀላጥፎ መናገር የማይችልን እምቦቅቅላ ሕፃን እንዲህ በጭንቀት የምናርበተብተው?
በየት በየት በኩል ተጉዘን ነው እዚህ የደረስነው?

እግዚኦ!!!!!!!!
135 viewsYeshiwas, 05:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 18:00:21
ዕንባ የደም አረቂ ነው ይባላል። ተንተክትኮ ተንተክትኮ ኩልል ብሎ የሚወርድ የፈላ ደም ነው።
134 viewsYeshiwas, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 22:32:07
"አሁንስ ተስፋየ ማን ነው?" ያለ ማን ነበር?
ግን ምን ብናደርግ ነው የሚሻለን? አሁን እነዚህ እናቶች ያለቀሱባት መሬት ቢዘሩባት ልታበቅል፣ ቢወልዱባትስ ልታሳድግ ትችላለች?
የሩዋንዳ ቱትሲዎችስ በሁቱዎች ከዚህ በላይ ምን ደረሰባቸው? የእኛ ሁቱዎች ግን መቼ ይሆን በቃችሁ የሚሉን?
ኤዲያ!!! ሐሳቤ ሁሉ ጥያቄ ብቻ ሆነብኝ፤ ማን ይመልስልኛልና ነው እንዲህ የሚያስቀባጥረኝ...

"አሁንስ ተስፋዬ ማን ነው?"
ዝም ብዬ ሙሾየን ባወርድስ? ለምን ብለው ይጠይቁኝ ይሆን? ለምን መርጠህ አለቀስህ ይሉኝ ይሆን?
"በሕዝቤ ሴት ልጅ ስብራት እኔ ወድቄ ተሰብሬአለሁ፤ ጠቁሬማለሁ፤ ራስ ማዞርም ይዞኛል፤ ምጥ እንደያዛትም ሴት በመከራው እጨነቃለሁ" /ኤር 8፥21/።
"... ስለሕዝቤ ሴት ልጅ ሰዎች ሌሊትና ቀን አለቅስ ዘንድ ለራሴ ውኃን፣ ለዐይኔም የዕንባን ምንጭ ማን በሰጠኝ? /ኤር 9፥1/።
"ስለወገኔ ሴት ልጅ ቅጥቃጤ ከዐይኔ የውኃ ጎርፍ ፈሰሰ" /ሰቆ ኤር 3፥48/።
152 viewsYeshiwas, 19:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 16:28:13 በሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ
_______
ከላይ ሲሆኑ አይከብድም
_____
ዛሬ አንድ ጉዞ ነበረኝ። ጉዞው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው። የሚሸኘኝ ሰው ወደ መሳፈሪያ ስፍራ እየወሰደኝ ሳለ እባክህ ትኬቱን እናስቀይረውና ጉዞህን ሌላ ቀን እናድርገው አለኝ። ለምን? ስለው አታየውም አየሩ ጥሩ አደለም አለኝ።
ሳየው የቆየሁትን ሰማይ ደግሜ አየሁት፤ እውነትም ሰማዩ በጭጋግ ተሸፍኗል። ፀሐይ ወደ ምድር መድረስ ተስኗት ከጥቁሩ ደመና ጋር ትታገላለች። ሰማይና ምድር መካከላቸው በገባው ጥቁር ደመና ምክንያት መተያየት አቁመዋል።
ቀና ብየ ደግሜ አየሁት፤ ያስጨንቃል። ፊቱን የዞረ ሰማይ በቆፈን የተወረረ ምድር። ምድር ሰማዩ ፊቱን ካላበራላት ጨለማ ናት።
ለካ ብርሃናችን ከሰማይ ነው። ምድር አይኗን የምትገልጥበት ምንም የላትም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
"የፈራ ይመለስ" የሚለው ስብከት ትዝ አለኝ። ነገር ግን መቅረት ስለማልችል እሄዳለሁ ብየ ጉዞየን ጀመርሁ። መሬቱን ለቀን ወደ ላይ አቀናን። አውሮፕላኑ ጥቁሩን ደመና አልፎ የተፈቀደለትን ከፍታ እስከሚይዝ ድረስ ያስፈራል። ከተሞች ከዐይናችን ተሰወሩ። አሁን በሰማይና በምድር መካከል ነን። ፍርሃቴ እየቀነሰ ሲመጣ ይሰማኛል። ምክንያቱም ጥቁሩን ደመና እያለፍነው ነው። ከደመናው በላይ ፀሐይ አለ። ብርዱ ያለ ከታች ነው። ከላይ ግን ሙቀት ነው። ጨለማው ያለ ከመሬት ነው ከላይ ግን ብርሃን ነው። ኔትዎርክ ኖሮ መነጋገር የሚፈቀድ ቢሆን ያንን የሸኝን ሰው ችግሩ ያለ ከታች በመኖራችን እንጅ ከላይ መልካም የሆነ ዓለም መኖሩን እነግረው ነበር። ነገር ግን ከታችኛው ዓለም ጋር መገናኘት አይቻልም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከደመናው በላይ መልካም የሆነ ዓለም ካለ ከሰማዩ በላይ እንዴት ያለ መልካም ሀገር ይኖር ይሆን? ወደ ሰማያዊው ከተማ የገቡ ሰዎች ለአንድ ቀን ከኛ ጋር መገናኘት ቢፈቀድላቸው ምን ይሉን ይሆን?
የላይኛውን ዓለም በእምነት መመልከት ላልቻሉ ሰዎች በዚህ መኖር መልካም ይመስላቸዋል። በክርስትና መንገድ ላይ የጀመሩትን የቅድስና ጉዞ አቋርጠው የተመለሱ ብዙዎች ናቸው። ምክንያቱም የጋረዳቸውን ደመና አልፈው መሄድ ስላልቻሉ ነው። ጭጋጉን እስክናልፍ የክርስትና ፈተናው ከባድ ቢሆንም በቅዱስ ወንጌል የተፈቀደላቸውን የሕይወት ከፍታ ይዘው ለሚጓዙ ክርስቲያኖች ግን መንገዱ አስቸጋሪ አይደለም። ፈተናው ያለ ስንወጣና ስንወርድ ብቻ ነው። ያስፈራል። ያስጨንቃል። ከላይ ስንሆን ግን የሚመራን ታላቅ ብርሃን አለ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አሁን ወደ ምድር ተመልሰናል። ምድርን ያጨለማት ደመና እዚህም አለ።
ያው መመላለስ ነው።
አንድ ጊዜ ወደ ላይ አንድ ጊዜ ወደ ምድር።

Taken from Yohannis Temesgen post
157 viewsYeshiwas, 13:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 06:56:01 https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=7808713089170668&id=100000961646191
161 viewsYeshiwas, 03:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 15:11:50
የአጋንንት አለቃ ሳጥናኤል የሰው ልጆችን ሁል ጊዜ ወደ ኀጢአት እንደ ሚመራና ወደ ሲዖል መርቶ እንደሚያስገባ የሚያምን ሁሉ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ደግሞ በተቃራኒው ውሉደ አዳምን በፅድቅ መንገድ እየመራ ወደ ገነት እንደሚያስገባ ማመን አለበት። እንደዚያ ካልሆነ ግን ክፉ ክፉውን ማመንና ደግ ደጉን መካድ ይሆንበታል።
194 viewsYeshiwas, 12:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 10:55:50
ጾሙን ባለመብላት እና ባለመጠጣት ብቻ ሳይሆን እንደእኛ እድሉን ማግኘት ላልቻሉ ነፍሳቸው ቃለ እግዚአብሔርን ተርባና ታርዛ ድረሱልን እያሉ ዘወትር የሚጮኹትን ወገኖቻችንን ቃለ እግዚአብሔርን እየመገብን እንጹመው።
345 viewsYeshiwas, edited  07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ