* ይህ የረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ታላቅ ምክር ነው።* *አንድ ሰው ወደ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ጋ መጣና "ለዱንያም ሆነ ለአኼራ *የሚጠቅም ንግግር ለመጠየቅ መጣው" አላቸው ።* *እሳቸውም ደግሞ "የመጣልህን ጠይቅ"* *አሉት።* * "ከሰው ሁሉ አዋቂ ለመሆን እፈልጋለው?"* *እሳቸውም "አላህን ፍራ" አሉት* * "ከሰው ሁሉ ሀብታመ* *ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው።* *"ባለህ ነገር ተብቃቅተ አላህን አመስግን" አሉት* * "ትክክለኛ ፈራጅ እና ታማኝ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል* *"ለራስህ የምትወደውን* *ለሰዎች ውደድ"* *አሉት።* * "ከሰው ሁሉ ብርቱ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል* *"በአላህ ተወከል"አሉት* * "በአላህ ዘንድ ብቸኛ ተመራጭ ለመሆን* *እፈልጋለው" ሲላቸው?* *"ዚክር አብዛ" አሉት።* * "ከሰው ሁሉ በላጭ* *ለመሆን እና ጥሩ ሰው ለመሆን* *እፈልጋለው?" ሲል* *"ለሰው ጠቃሚ ሁን" አሉት።* * "የተከበረና ቸር ሰው* *ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው* *"ችግርህን ለፍጡር አትንገር" አሉት።* * "ረሱል እና አላህ እንዲወዱኝ *እፈልጋለው?" ሲል* *"አንተም እነሱ የወደዱትን* *ውደድ" አሉት::* * "ከወንጀል የጠራው ሁኜ አላህንመገናኘት እፈልጋለው" ሲል* *"ጀናባህን በደንብ ታጥበ* *እስቲግፋር አብዛ ማልቀስ* *መተናነስ መታመም* *አለብህ" አሉት።* * "ከበጎ ሰሪወች ለመሆን እፈልጋለው"* ሲላቸውም* *"አላህን ልክ እንደምታየው ሁነክ ተገዛው" አሉት።* * "ኢማኔ እንዲ ሞላ* *እፈልጋለው" ሲል* *"ፀባይህን አሳምር" አሉት።* * "እርዝቄ እንዲሰፋ እፈልጋለው" ሲል* *"ተዋዱዕ አዘውትር" አሉት።* * "ዱዓዬ ሙስተጃብ እንዲሆንልኝ እፈልጋለው?" ሲላቸው* *"ሀራም አትብላ" አሉት::* * "አላህን ከሚታዘዙ ሰዎች ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል* *"ግዴታዎችህን ፈፅም" አሉት።* * "በአላህ ዘንድ ትልቁ ሀሠና ወይም ደግ ሥራ የቱ ነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው* *"መልካም ፀባይ መተናነስ እና *በበላ ላይ ሰብር ማድረግ ነው" አሉት።* * "በአላህ ዘንድ የትኛው ስርዓት ነው መጥፎ ሥራ?" ሲል ሲጠይቃቸው* *"መጥፎ ፀባይና ፍላጎትን መከተል ናቸው" አሉት* * "በዱንያም ሆነ በአኼራ የአላህን ቁጣ የሚያበርድ ምንድነው" ሲል ጠየቃቸው? *"ድብቅ ሰደቃ እና ዘርን መቀጠል ናቸው" አሉት።* * "የቂያማ ቀን በአላህ ኑር ለመሰብሰብ* *እፈልጋለው?" ሲል* *"ሰውን አትበድል" አሉት* * "የቂያማ እለት አላህ* *እንዲያዝንልኝ እፈልጋለው?"* *"ለአላህ ባርያዎች እዘን" አሉት።* * "የቂያማ ቀን የጀሀነም እሳት የሚያጠፋው ምንድነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው* *"በችግር ላይ ወይም በሙሲባ ላይ ትህግስት መሰድረግ ነው" አሉት።* * "የቂያማ እለት ነውሬ* *እንዲሸፈንልኝ እፈልጋለው?" ሲል* *"የወንድምህን አይብ ሸፍን" አሉት።* * "የቂያማ ቀን ከአላህ ቁጣ ሰላም ለመሆን* *እፈልጋለው?" ሲል* *"በአንድም ፍጡር አትቆጣ" አሉት።* *አሏህ ሱብሃን ወተአላህ ባወቅነው በስማነው የምንስራ ያድርገን ኣሚን!** @yenebiywedaj @yenebiywedaj @yenebiywedaj 250 viewsيا رسول, edited 12:04