Get Mystery Box with random crypto!

حيات سحبا የምርጦች ትውልድ ታሪክ

የቴሌግራም ቻናል አርማ yemrtoche_twlede — حيات سحبا የምርጦች ትውልድ ታሪክ ح
የቴሌግራም ቻናል አርማ yemrtoche_twlede — حيات سحبا የምርጦች ትውልድ ታሪክ
የሰርጥ አድራሻ: @yemrtoche_twlede
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131
የሰርጥ መግለጫ

«ያ አላህ! ባልሰራበት እንኳ ወደ በጎ ነገር
ያመላከተ ሰው የሚያገኘውን አጅር አታሳጣኝ፡፡»
.
.
.
.
.
ማሳሰቢያ:- Leave Channel ከማለቶ በፊት
ያለተመቾት ነገር ካለ ያሳውቁን
@yemrtoche_twledebot

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-09-06 18:27:28 በአማርኛ ቋንቋ የሸሪዓ እውቀትን መማር ለሚትፈልጉ ሁሉ ።

የሸሪዓ እውቀትን ለመማር የተመኙና ያለሙ ነገር ግን ምኞታቸውንና ህልማቸውን ለማሳካት የተተሳናችው ውድ ወንድሞችና እህቶች።

ይከታተሉ! በአፍርካ አካዳሚ ድረ ገጽ እጅግ በጣም የላቀና በአይነቱ ልዩ የሆነ የሸሪዓ ትምህርት ኢንዲሁም ብቃታቸው የተመሰከሩላቸውና በሞያቸው ልዩ በሆኑ ኡለማዎች የተዘጋጀ ሲሆን አሳታፊነቱ ልዩ ያደርገዋል ።

እናም ይህ ሁሉ በነጻ እና በኤሌክትሮኒክ መንገድ ከቤትዎ መማር እንድትችል ዘንድ ቀርቦ ይገኛል።

ለአካዳሚው ምዝገባ የሚጀምሪው፡ በ6/9/2021 EC.

የሚዝገባው ቀን በአካዳሚ ቴሌግራም(telegram) ቻናል ላይ ይፋ ይደረጋል: https://t.me/Ethioafricaacademy

ስለ አካዳሚው የበለጠ ለማወቅ ድረ ገጻችንን ይጎበኙ: https://africaacademy.com/
b
@yemrtoche_twlede
106 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, 15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-31 21:23:41 ╔═══════════════╗
ኡሙ ሐኪም
╚═══════════════╝

በኢስላም ታሪክ ውስጥ ሴቶች በተፈለጉበት ቦታና ጊዜ ከመገኘት ወደኋላ ብለው አያውቁም። በብዙ ክስተቶች ጠንካራ አሻራቸውን አሳርፈዋል። ከሁሉም ድል በስተጀርባ ከወንዶች እኩል ስማቸውን ከትበዋል። በወሳኝ ፍልሚያዎች ተሳትፈዋል። ከወንዶች ያላነሰ ሚናን ተጫውተዋል።

ድፍረት እና ጀግነትን ከሚያስደስት ግርማ ሞገስ ጋር የተላበሰችን እንስት ላስተዋውቃችሁ የእጆቼ ጣቶች የስልኬን ፊደላት መነካካት ይዘዋል።

ኡሙ ሀኪም ቢንት አል-ሀሪስ ትባላለች። ሙጃሂድ፣ ታጋሽ እና ጨዋ ስለመሆኗ የቅርብ ጓደኞቿ ይመሰክራሉ። በህይወት ዘመኗ ሶስት ባሎችን አግብታለች። በሠርጓ ምሽት ሰባት የመስቀል ጦረኞችን ብቻዋን ተፋልማ የገደለች፣ ጀግንነትን በተግባር የኖረች የኢስላም ፈርጥ ናት።

ከመስለሟ በፊት በእስልምና ጥላቻ መታወሯ ሐቅን እንዳትመለከት አድርጓታል። ረሱልን ገድሎ ኢስላምን ለማጥፋት በተደረገው የኡሁድ ዘመቻ ግንባር ቀደም ተሳታፊ ነበረች። የእምነት አጋሮቿን በማበረታታትና በማጠንከር ላይ ተሳትፋለች። ከመካ መከፈት በኋላ እናቷ እና አባቷ እስልምናን ተቀብለው ለነቢ ﷺ ቃል ኪዳናቸውን ሲሰጡ እሷም በይፋ እስልምናን ተቀበለች።

ወደ ነቢም ﷺ ዘንድ በመሄድ ባሏ ሙስሊም ሆኖ ከተመለሰ ደህንነቱ ተጠብቆ ይቅር እንዲባልላት ጠየቀች። ባሏ ኢክሪማ ይሰኛል። ረሱልም ﷺ ለደህንነቱ ዋስትናን ሰጡት። ይህንን የሰማው ባልም ወደ መካ በመምጣት እስልምናን መቀበሉን አወጀ።

ኡሙ ሀኪም የየርሙክ ዘመቻ ወቅት ከመስመሩ በስተጀርባ ቆስለው የወደቁትን ሙጃሂዶች በማከም፣ ከትግሉ ወደ ኋላ ያፈገፉትን በመመለስ እየታገለች ባሏን ኢክሪማን አጣች። በጦርነቱ ተሰዋ። ወደ ደረቷ አስጠግታ አቅፋ ተሰናበተችው። ኢዳዋን እንደጨረሰች የዚድ ኢብኑ አቢ ሱፍያን እና ኻሊድ ኢብኑ ሰዒድ የጋብቻን ጥያቄን አቀረቡላት።

ኻሊድ ኢብኑ ሰዒድን መረጠች። እሱን ለማግባትም ተስማማች። በሙስሊሞች እና በሮማውያኑ የመስቀል ጦረኞች መካከል ሻምን የማቅናት ዘመቻዎች እየተካሄዱ ነበር።
የሰርጉ ድግስ በ“መርጅ አስ-ሰፈር” በወንዙ አቅራቢያ በሚገኝ ድልድይ ሥር ተፈፀመ። የኋላ ኋላ የ“ኡም ሀኪም” ድልድይ ተብሎ በተሰየመው ቦታ ላይ ድግሱ ተበላ። ሙሽሮቹ በተዘጋጀላቸው ድንኳን ውስጥ አረፉ። ጋብቻው አንድ ለሊትን በቅጡ ሳያስቆጥር ሮሞች ዘመቻቸውን አጠናክረው ለሊቱን ተገን በማድረግ ጥቃት ሰነዘሩ። ሙሽራው በአላህ መንገድ ፀንቶ በጀግንነት እየተፋለመ ከጌታው ጋር ተገናኘ።

ኡም ሀኪም ባሏ በሮማውያን እጅ ሸሂድ መሆኑን ባወቀች ጊዜ ያገባችበትን የድንኳን ዓምድ ሰብራ መቀነቷን አስራ ሮማውያንን ለመዋጋት ወጣች። በወንዙ ዳርቻ ከጠላት ጦር ጋር ፊት ለፊት ተገናኘች። ጥንካሬ ወኔና ጀግንነት በተሞላበት መንፈስ እየተፋለመች ሰባቱን ከመሬት ዘርራ ልብሳቸውን በደማቸው ነክራ ድልን ተጎናፀፈች።
እናት ትምህርት ቤት ናት በሚገባ ካዘጋጀሀት ትውልድን ትቀይራለህ!

ሰብስክራይብ ያድርጉ

ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ #yemrtoche_twlede
98 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, 18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-27 21:12:42 በዚህ ሽባ እግሬ ጀነትን መርገጥ እፈልጋለሁ !
(أريد أن أطأ بعرجتي الجنة)


(..ዐምር ኢብኑል ጀሙህ የኢማኑን ለዛ አጣጣመ ። በሽርክ ያሳለፋት እያንዳንዷ ደቂቃ ትቆጨው ጀመር። መላ እሱነቱን ለአዱሱ እምነት አስረከበ። አካሉን፣ መንፈሱን፣ገንዘቡን ፣ ልጆቹን ኢስላምን ለማገልገል ተግባር አዋለ። አላህንና ረሱልን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ለማርካት።

ብዙም ሳይቆይ የኡሁድ ዘመቻ ተከሰተ። ሦስቱ ልጆቹ የአላህን ጠላቶች ለመፋለም ዝግጅት ላይ ናቸው። ሸሂድ ለመሆን፤ አላህ ዘንድ ለመወደድ ለስኬት ለመብቃት ጎግተዋል። ውስጣዊ ስሜቱን ቀሰቀሱበት።

በረሱል (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አመራር ስር ኡሁድ የፍልሚያ መስክ ለመገኘት ቆረጠ።
ልጆቹ ግን ተቃወሙት። አባታቸው ሽማግሌ ነው። እድሜው በጣም ገፍቷል። አንድ እግሩም ሽባ ነው። አላህ ጂሀድን ግዴታ አላደረገበትም። ስለዚህ ባይዘምት ይመረጣል። በአቋማቸው ፀኑ። " አባታችን ሆይ ! አላህ ባንተ ላይ ጂሀድን ግዴታ አላደረገብህም፤ ለምን ራስህን ታስጨንቃለህ?"
ዐምር በልጆቹ ውሳኔ በጣም ተቆጣ። ከረሱል (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዘንድ በመሄድ ስሞታውን ተናገረ። " የአላህ ነብይ ሆይ! እነኝህ ልጆቼ ከዚህ በጎ ነገር ሊያቅቡኝ ይሻሉ። ሽባ ነህና ጂሀድ አትሄድም ይሉኛል። በአላህ ይሁንብኝ በዚህች በሽባ እግሬ ጀነትን መርገጥ እፈልጋለሁ።" አላቸው።
" ይዝመት፤ ምናልባትም አላህ ሰማእት የመሆንን ታላቅ እድል ይሰጠው ይሆናል። " አሉ መልዕክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ለልጆቹ። ልጆቹ የረሱልን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ትእዛዝ አከበሩ።

የኡሁድ ዘመቻ ወቅት ደርሷል። ዐምር ኢብኑል ጀሙህ ባለቤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ተሰናበተ። ከዚያም ወደ ቂብላ በመዞር ፊቱን ወደ ሰማይ አቅንቶ " አላህ ሆይ! ሸሂድ የመሆንን እድል ለግሰኝ! ወደ ቤተሰቦቼ ከነሕይወቴ እንዳትመልሰኝ" ሲል ዱዓ አደረገ። በሦስቱ ልጆቹና በበርካታ የአንሷር ተዋጊዎች ተከቦ ወደ ዘመቻ ሄደ።

ጦርነቱ ተጋግሟል። ሰዎች ከረሱል (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ጎን እየራቁ ነው። ዐምር ኢብኑል ጀሙህ ከረሱል (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ጎን ቆሟል። በደህና እግሩ እየዘለለ ይፋለማል።" ጀነትን ለመጎናጸፍ በእጅጉ ጎግቻለሁ" ይላል። ከበስተጀርባው ልጁ ኸልላድ ነበር። ዐምርና ልጁ ነቢዩ ሙሐመድን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከጥቃት በፅናት ይከላከላሉ። ዐመር የሚችለውን ሁሉ ካደረገ በኋላ ተመቶ ወደቀ። ሸሂድ ለመሆንም በቃ። ብዙም ሳይቆይ ልጁም ተከተለው አባትና ልጅ የክብር ሞት ለመሞት ታደሉ።

ጦርነቱ ተጠናቋል ። የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የኡሑድ ሸሂዶችን ለመቅበር ተዘጋጅተዋል " ከነደማቸውና ቁስላቸው ተዎቸው ። እኔ መስካርያቸው ነኝ። በአላህ መንገድ ላይ የሚቆስል ሙስሊም የቂያማ ቀን ደሙ የሚፈስ ሆኖ ይመጣል። የደሙ ቀለም አበባ ይመስላል። ሽታውም እንደሚስክ ይሸታል" አሉ ። ...)

رضي الله عن الصحابة وألحقنا بركبهم!
#ሀያቱ አል ሶሃባ
@yemrtoche_twlede
116 viewsAb Ab, 18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-01 19:32:41 ╭─┅┅┅┅┅┅┅┅┅┅┅─╮
ስለ ሶስቱ ሰዎች ምን አሳወቃችሁ?!
╰─┅┅┅┅┅┅┅┅┅┅┅─╯

እ.ኤ.አ. በ1839 የእንግሊዝ ጦር በፋርስ፣ በኹራሳን፣ በፓሽቱኒስታን፣ በቢንጃብ እና በሲንድ አዋሳኝ ድንበር መካከል የምትገኘውን "ባሎቺስታን" ከተማን ተቆጣጠሩ፡፡
በዚህ መሐል ከባሎቺስታን ተራሮች ከከፍተኛው ጫፍ ላይ የእንግሊዝ የመስቀል ወረራ ኃይል በሙስሊሞች ላይ እየፈፀመ ያለውን ኢ-ሰብዓዊ ተግባር በመቃወም ወታደሮቹን ዒላማ ያደረገ የጂሃድ ትግል እንቅስቃሴ ተጀመረ።
ከተራራው ጫፍ የጀግንነት ተግባር ይፈፀሙ ጀመር። እጅግ አስደናቂ ተጋድሎ የሚያደርጉት ሙጃሂዶች የእንግሊዝን ጦረኞች በቀኝ በግራ ይረፈርፏቸው ያዙ። ከ83 በላይ አነጣጥሮ ተኳሽ ወታደሮችን በሞት ነጠቁ።
በተራራው አናት ላይ የተደራጁ ሰራዊቶች ይኖራሉ ብለው በመገመታቸው የእንግሊዝ ወታደሮች የወቅቱን ዘመናዊ መሳርያ ሸክፈው እጅግ ብዛት ያለውን ኃይላቸውን አጠናክረው በተራራው ዙሪያ ሰበሰቡ። የተራቀቁ የጦር መሣሪያዎችን ይዘዋል። ከወዲህ ከወዲያ ጦራቸውን ያንደቀድቁት ጀመር። ኮሽ ባለ ቁጥር በሙሉ ኃይላቸው ከግራም ከቀኝም ተኩሱን ያጧጡፉታል። ሆኖም ግን መቆጣጠር አልቻሉም።
በዚህ ሁኔታ አራት አመታቶች ተቆጠሩ። የሙጃሂዶቹ ብዛት እስካሁንም ግምት እንጂ ትክክለኛ ቁጥራቸው አልታወቀም። ከእነርሱ የሞተም ሆነ የተማረከ አንድም የለም። ለ4 ዓመታት!
የእንግሊዝ ኃይል ከተራራው አናት ላይ ባሉ ሙጃሂዶች ተገፍቶ የበዙ ወታደሮቹን በመነጠቁ ተራራውን ከሚያዋስኑ መንደሮች ጋር ሰላማዊ ድርድር ማድረግ ጀምሯል። በነዋሪው ላይ የጫኑትን ግብሮችም አንስተዋል።
የምግብ አቅርቦቶች፣ የጥይትና በጦር መሳሪያዎች ለሙጃሂዶቹ እንዳይደርሳቸው በተራራው ላይ ሙሉ በሙሉ ከበባ አደረጉ።
ሙጃሂዶቹ የምግብ ቁሳቁሶችና የጥይት ቀለሀዎች ስላለቀባቸው በረሀብ ከመሞት እጃቸውን ለመስጠት ወሰኑ። መስቀላዊያኑ በጭራሽ ያልጠበቁትን ነገር በመመልከታቸው ተገረሙ፡፡
እነሱ እንዳሰቡት እጅግ በርካታ የሙጃሂድን ስብስብ በተራራው ላይ አላገኙም። .... ሶስት ጀግና ሙጃሂዶች ብቻ ነበሩ። ... ለአራት ዓመታት ከተራራው አናት በሺዎች ከሚቆጠሩ የጠላት ሰራዊት ጋር ሲዋጉ የተራራውን ከፍታና አስቸጋሪውን የመሬት አቀማመጥ ተቋቁመው ብሎም ብቃታቸውን ተጠቅመው የጠላትን ጦር ከማርገፍም በላይ ለአመታት ፍርሀትና ድንጋጤን ፈጥረው ያንቀጠቀጡ ሶስት ጀግና ሙጃሂዶች፡፡
የእንግሊዝ የመስቀል ወረራ ኃይል የሶስቱን ጀግኖች ስም ይፋ አደረጉ
"ካላ ኻን"
"ጋላምብ ኻን"
"ረሂም አሊ" ይሰኛሉ።
ፍርዱ ከመፈጸሙ ከቀናት በፊት እጆቻቸውና እግሮቻቸው ተጠፍሮ የምትመለከቱትን ፎቶግራፎችን ተነሱ። እ.አ.አ. በ1891 የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው ተሰቅለው ተገደሉ፡፡

አላህ ምህረቱን ያጎናፅፋቸው ተበለሁሙላሁ ፊ ሹሀዳእ፡፡
═════════════════
ምንጭ:
كتاب: كانوا رجال
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ በእናንተ ሰበብ አንድ ሰው ወደ መልካም ነገር ቢመራ እኩል አጅርን ይጎናፀፋል
@yemrtoche_twlede
124 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, 16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-19 22:45:16
#eid።።።።።

ሰማይ ድምፅህን ልጣታው አይገባም። ስትለምን መላኢኮች ድምፅህን የሚያውቁት ባሪያ ሁን።
"ጌታዬ ሆይ… " ስትል… "ታዋቂ ድምፅ ከታዋቂው ባሪያ" ይላሉ። ልብ በል! በዱዓህ ታዋቂ የምትሆነው አላህ ዘንድ ነው።
ያ.....አ.....ላ.....ህ በለው!!!

ጌታችሁንም ምሕረትን ለምኑት፡፡ ከዚያም ወደርሱ ተመለሱ፡፡ ጌታዬ አዛኝ ወዳድ ነውና (አላቸው)

#ሰሉ #አለ #ነቢ....( اللهم صل وسلم على نبينا محمد )

⇘⚘#አትዘን لا تحۡـــــزن⚘
@yemrtoche_twlede
113 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, edited  19:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-18 22:28:42 የነገን ሰኞ ዙልሂጃ 9 (አረፋ) ፆምን መፆም እንዳንዘነጋ!
ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ‹‹የአረፋን እለት የፆመ ሰው ያለፈውን የአንድ አመትና
የሚመጣውን የአንድ አመት ወንጀሉን ያስምርለታል ብየ እከጅላለሁ›› ማለታቸው
ተዘግቧል። (ሙስሊም)
የነገዋ ቀን በዱኒያ ላይ ካሉ ቀናቶች ሁሉ በላጭ ቀን ናት፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ከፍተኛ
ቁጥር ያለውን ሙስሊም ከጀሃነም እሳት ነጅ የሚልበት ቀን ነው፡፡ በዚህች
በተቀደሰች ቀን አላህ የወፈቃቸው በአረፋ ተራራ ላይ ቆመው አላህን ሲማፀኑ
ይውላሉ፡፡ ከሃጅ ስነ ስርአት ውጪ ያለው በቢሊዬን የሚቆጠር ሙስሊም ደግሞ
ቀኑን በታላቅ ኢባዳ፣ በፆም፣ በዚከር፣በዱዓ፣በሰደቃ ባጠቀቃላይ በመልካም
ስራዎች ተጠድሞ ያሳልፈዋል፡፡
ይህ ውድ ቀን ሁላችንም ልንጠቀምበት ይገባል፡፡ ለወንጀላችን ምህረት
የምንጠይቅበት፣ ከእሳት ነጅ እንዲያወጣን አልቅሰን የምንማፀንበት ፣ ሃገራችንን
እና አለማችንን ሰላም እንዲያደርግልን የምንለምንበት፣ ላስጨነቀን ሁሉ ነገር
መፍትሄ ለማግኘት አላህን የምንማጸንበት ቀን ነው፡፡
ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) " በላጩና ምርጡ ዱዓ በዐረፋ ቀን ውስጥ የተደረገ ዱዓእ ነው"
ብለዋል ፡፡ (ቲርሚዚ እንደዘገቡት)
እራሳችንንም ሆነ ቤተሰቦቻችንን እንዲሁም አጠገባችን ያሉ ሙስሊሞችን
የነገዋን የአረፋ ቀን በፆም እና በኢባዳ እንዲያሳልፉት እናስታውሳቸው
እናበረታታቸውም!
የነገን የአረፋ ቀን ፆመን ከእሳት ነጅ ከሚባሉት፣ወንጀላቸው ከሚማርላቸው እና
በዱኒያም ሆነ በአኼራ ስኬታማ ከሚሆኑት አላህ ያድርገን!!
@yemrtoche_twlede
270 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, 19:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-17 23:08:37 ╔───────◎◎───────╗
ቢላል ኢብኑ ረባህ
╚───────◎◎───────╝

"አቡበክር ልዑላችን ነው። የኛን ልዑልም ነፃ አውጥቶልናል" የሚለውን የሙገሳ ቃል ሲሰማ ግንባሩን ደፋ፣ ዐይኑን ገርበብ በማድረግ "እኔ ትናንት ባርያ የነበርኩ የሐባሻ ሰው ነኝ" ይላል።
በየትኛውም ቦታ የሚገኙ ሙስሊሞች የኢስላሙን ሙአዚን ቢላል ኢብኑ ረባሕን ያውቁታል። ስሙን፣ ዝናውን እና ሚናውን በሚገባ ያወሱታል።
ሕፃናትን ቢላል ማን ነው ብለህ ብትጠይቅ የረሱል ﷺ "ሙአዚን" ነው ይሉሀል። አሳዳሪው በጋለ ድንጋይ ላይ አስተኝቶ ሲያሰቃየው ወደ ጥንት እምነቱ ከመመለስ ይልቅ "አሐድ... አሐድ... በማለት ፅናቱን የገለፀ ብርቱ ሰው ነበር የሚል ምላሽን ታገኛለህ።
ቢላል ኢስላምን ከመቀበሉ በፊት በሕዝቡ ዘንድ ከእንስሳ ተለይቶ የማይታይ የተናቀ ባርያ ነበር። ኢስላምን ባይቀበል ኖሮ የአሳዳሪውን ግመል ከመጠበቅ ሌላ የህይወት ሚና የሌለው፣ እንኳን ከሞተ በኋላ በሕይወት ዘመኑም አስታዋሽ አልባ ሰው ሆኖ በቀረ።
የመካ ሰዎች በትኩስ ወሬነት የሚነጋገሩት ሙሐመድ ﷺ ነብይ ነኝ ብሎ የመነሳቱ ጉዳይ በቢላል ጆሮ ደረሰ። አሳዳሪውና እንግዶቹ በዚሁ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ሲወያዩ ሰማ። በተለይ ኡመያ ኢብኑል ኸልፍ ተንኮል የተሞላበት ውይይትና ምክክር ከጓደኞቹናና ከቁረይሾችች ጋር ሲነጋገር አዳመጠ።
የቢላል ጆሮ ተሰብሳቢዎቹ ከሚናገሩት የጥላቻ ንግግር ውስጥ ረሱል ﷺ ስለተነሱበት አላማና ምን እያሉ እንደሚያስተምሩ ቀነጨበ። አዲስ የመጣው ዲን ለመላው የሰው ዘር ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ያለመ መሆኑን ሰማ።
በእስልምና በእጅጉ ተማረከ። የኢማን ብርሀን በልቡ ላይ ፈነጠቀ። እምነቱን ይፋ ማድረግ እንዳለበትም ወሰነ። ወደ ረሱል ﷺ በመሄድ ለኢስላም እጁን መስጠቱን ይፋ አደረገ። የቢላል መስለም በመካ ምድር ተሰማ። የበኒ ጀምህ መሪዎች በቁጣ ተወጣጠሩ። በተለይ አሳዳሪው የኢስላም ጠላት ኡመያ ኢብን ኸለፍ ሀበሻዊ ባሪያው መስለሙ እንደታላቅ ነውርና ንቀት ቆጠረው። "ይህ ኮብላይ ባሪያ በመስለሙ ፀሀይ ተመልሳ የምትጠልቅ አይመስለኝም" ሲል ቁጭቱን ገለፀ።
እርቃኑን በትኩስና አሸዋማ መሬት ላይ እንዲተኛ ተደርጎ ቋጥኝ ድንጋይ ደረቱ ላይ ተጫነ። በጠራራ ፀሐይ ሰውነቱ እየተገረፈ "ላት" እና "ዑዛ" የተሰኙ ጣዖታትን እንዲያወሳ ያለ መታከት ይጠይቁታል። መልሱ ግን "አሐድ.... አሐድ" ነበር። "እኛ የምንለውን ደግመህ በል" በማለት ይገርፉታል። በምፀታዊ ቃልም "እናንተ የምትሉትን ለመናገር ምላሴ አትችልም" ይላቸዋል። "ላት" እና "ዑዛ" ጌታዎች ናቸው ካልክ እንተውሀለን በእርግጥ አንተን ማሰቃየት ደክሞናል" ጭንቅላቱን በመነቅነቅ "አሐድ...አሐድ" የሚል ምላሽ ከመስጠት ባሻገር እጅ አልሰጠም ነበር።
አቡበከር ቢላል በሚሰቃይበት ቦታ ደረሱ። "አንድ ሰው አምላኬ አላህ ነው! በማለቱ ብቻ ልትገድሉት ትሻላችሁን?" ሲሉም ጠየቁ። ወደ ኡመያ በመዞር "ቢላልን ከገዛህበት ዋጋ ጨምሬ እከፍልሀለው" ሽጥልኝ አሉት።
ኡመያ በቢላል ተስፋ ስለቆረጠ ገንዘብ ቢያገኝበት የተሻለ መሆኑ ተሰማው። አቡበከር ቢላልን ከገዙት በኋላ ነፃነቱን አወጁ። ቢላልን ተረክበው ሊሄዱ ሲነሱ ኡመያ እንዲህ በማለት ተሳለቀ፦ "በላትና ዑዛ እምላለሁ በአንድ ወቄት ወርቅ ካልሆነ አልገዛህም ብትለኝ እንኳ እሸጥልህ ነበር" አቡበክርም፦ "በጌታዬ አላህ ይሁንብኝ! በመቶ ወቄት ወርቅ ካልሆነ አልሸጥልህም ብትለኝ እንኳ የጠየቅከውን እከፍልህ ነበር" አሉት።
በርካታ የቁረይሽ ሹማምንት በበድር ጦርነት ተሳታፊ ለመሆን በሙሉ ልብ ተነስተዋል። ቢላል ላይ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ሲፈፅም የነበረው ኡመያ ኢብኑል ኸለፍ ግን ከመካ ለመውጣት ባለመፈለጉ ምክንያት ፈጥሮ ለመቅረት አስቧል። ዑቅባ ኢብኑ አቢ ሙዓይጥ ኡመያ ጦርነቱን ላለመሳተፍ ዘዴ እየዘየደ መሆኑን ሲሰማ ሴቶች ጭስ የሚሞቁበትን ሸክላ በመውሰድ ወዳጆቹ በተሰበሰቡበት "የዐሊይ አባት ሆይ! አንተ ሴት ነህና በዚህ ሸክላ ጪስ ሙቅበት" አለው።
ኡመያ የኃፍረት ማቅ መላበሱ ስለተሰማው "አንተንም ሆነ ይዘህ የመጣኸውን ነገር ዑዛ ያጥፋችሁ" በማለት ብስጭቱን ከገለፀ በኋላ ወደ ጦር ሜዳ ለመዝመት ዝግጅቱን ጀመረ።
ውጊያው ተጀመረ። ሙስሊሞች "አላሁ አክበር... አሐድ... አሐድ..." ሲሉ ይሰማል። ኡመያ ይህን ቃል በሚገባ ያስታውሰዋል። ትናንት የቢላል የጣር ድምፅ ነበር። አሁን ደግሞ የአዲሱ ትውልድ መፈክር ሁኗል። ልቡ ተሸበረ። ሠይፍ ከሠይፍ ተፋተገ። አንገት ተቀላ። ከዚህም ከዚያም የጣር ድምፅ ተሰማ። ጦርነቱ ሊገባደድ ተቃረበ። የሙስሊሞች የኃይል ሚዛን ደፍቷል። ቁጥራቸው አነስተኛ ቢሆንም ግዙፉን የቁረይሽ ጦር ድል ለመንሳት ተቃርበዋል። ቢላል ኡመያን በግላጭ አገኘው። በተጠማ ሠይፉ "አሐድ... አሐድ... " የሚል መፈክሩን እያሰማ የኡመያን አንገት ቆረጠው።
ቀናት ቀናትን ወልደው አመታት አለፉ። መካ በድል ተከፈተች። ሙስሊሞች መካን አጥለቀለቋት። እውነት... ፈካ... ሐሰት ተነነ። ሰዎች ለድንጋይና ለታቦት መገዛታቸው አከተመ።
ቢላል ከረሱል ጎን ቆሟል። ከካዕባ ጣራ ላይ በመውጣት የ"አዛን" ጥሪን እንዲያሰማ አዘዙት። በታላቁ ቦታ በተከበረው ቀን ሐበሻው ቢላል በካዕባ አናት ላይ በመውጣት "አዛን" አሰማ። በሺህ የሚቆጠሩ ሙስሊሞች እርሱን በመከተል የአላህን መልእክት ደጋግመው አስተጋቡ።
ቢላል ከረሱል ﷺ ጎን ሳይነጠል ኑሮውን መግፋቱን ቀጠለ። እርሳቸው በተገኙበት ዘመቻ ሁሉ ዘምቷል። ሁሌም ለሶላት "አዛን" ያደርጋል። ከጨለማ ወደ ብርሀን፣ ከባርነት ወደ ነፃነት ያወጣውን ታላቅ ዲን አርማ ያስተጋባል።
አንድ ለራሱና ለወንድሙ ሚስት ለማጨት ወደ ሴቶቹ አባት ቤት አመራ። "እኔ ቢላል እባላለሁ ይህ ደግሞ ወንድሜ ነው። ሀበሻዊ ባሪያዎች ነን...በተሳሳተ እምነት ላይም ነበርን። አላህ መራን። ነፃ አወጣን። ልጆቻችሁን ከዳራችሁልን አልሀምዱሊላህ እንላለን። ከከለከላችሁን ደግሞ አሁ አክበር እንላለን" በመተናነስ ጠየቀ። ጥያቄው ተቀባይነት አጊኝቶ ሀላ ቢንት አውፍን አገባ።
ከረሱል ﷺ ህልፈት በኋላ አዛን ማድረጉን አቁሞ በጂሃድ መስክ ላይ ተሰማራ። ዑመር ኢብኑል ኸጣብ ለጉብኝት ሻም በገቡበት ወቅት የሻም ነዋሪዎች ለአንድ ጊዜም እንኳ ቢሆን ቢላል አዛን ያሰማቸው ዘንድ ዑመር ግፊት እንዲያደርጉ ጠየቁ። ቢላል በልመና ተስማማ። አዛን አሰማ። "አሽሃዱ አንነ ሙሐመደን ረሱሉላህ" የሚለውን ሐረግ ጮኾ ለማሰማት ሳግ ያዘው። ዕንባ ተናነቀው። የረሱል ﷺ ትዝታ በአዕምሮው ተቀርፆ ትንፋሽ አሳጠረው። እርሱና በረሱል ﷺ ዘመን የነበሩ ሰሐቦች በእንባ ተራጩ። በተለይ ዑመር እንባቸውን ለረጅም ጊዜ መግታት አልቻሉም።

አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸው

╔───────◎───────╗
ምንጭ:
كتاب: رجال حول الرسول
╚───────◎───────╝
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ በእናንተ ሰበብ አንድ ሰው ወደ መልካም ነገር ቢመራ እኩል አጅርን ይጎናፀፋሉ
@yemrtoche_twlede
112 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, 20:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-16 18:00:17 ╔═══════════════╗
የአላህ አንበሳ የሸሂዶች ቁንጮ
╚═══════════════╝

አለም በእንቅልፍ ሰመመን ተውጣለች። ሁሉም የህልም አለም ውስጥ ይዳክራል። በቁሙ የተኛም ሞልቷል። ግን አንድ ሰው እንቅልፍ የለውም። ትንሽ ተኝቶ ብዙ ይቆማል። ትንሽ ስቆ ብዙ ያለቅሳል። የተጣለበት ኃላፊነት በእጅጉ የገዘፈ ቢሆንም ይህንን ኃላፊነት ለመወጣት ደፋ ቀና ይላል። ይህ ሰው ነቢዩ ሙሐመድ ነበሩ። ሁሉም ባመጡት መልዕክት አኩርፏቸዋል። ሁሉም በጠላትነት ፈርጇቸዋል። ዳዕዋ የሚያደርጉት በድብቅ ነው። ብዙ ሰው አይንህን ለአፈር እያላቸው ነው።
አንድሰው ግን ለነቢ ክብር ነበረው። በእሳቸው ለማመን ቢፈልግም ባህልና ወግ ወጥሮ ይዞታል። ነቢ ያመጡት ግን እውነት መሆኑን ያውቃል። እሳቸውንም ይወዳል።ይህ ሰው ሐምዛ ኢብን አብዱልሙጠሊብ ይባላል። የነቢዩ አጎት፣ የጡት ወንድማቸው፣ አብሮ አደጋቸው፣ የቅርብ ጓደኛቸው ሐምዛ!!
ሐምዛና ነቢዩ አብረው አድገው አፈር ፈጭተው ውሀ ተራጭተው አድገዋል። በእድሜም ተቀራራቢ ናቸው። ይዋደዳሉ።
ሐምዛ ጭንቅላቱ በሐሳብ ተወጥሯል። ህሊናው እረፍት ነስቶታል። ይህ የሙሐመድ ሐይማኖት እውነት ይመስላል። እያለ ማሰብ ከያዘ ሰነባብቷል።
ሐምዛ ጭንቅላቱ በሐሳብ እየተናወጠ ቀናቶች ተቆጠሩ። ሳምንታት ነጎዱና ወራትን ወለዱ። ቁረይሾችም በነቢዩና በተከታዮቻቸው ላይ እርምጃ መውሰድ ጀመሩ። ዳዕዋውን ለማኮላሸት ሌት ተቀን መስራትን ተያያዙት። ሐምዛ ከጡንቻው የፈረጠመ ቢሆንም አዕምሮው ግን ሐቅን ለመፈለግ አልቦዘነም። እስከ መቼ በውሸት ጌታ ህይዎቴን እገፋለሁ እያለ ያሰላስል ጀመር።
እንድት ሴት፦ "አንተ የዑመር አባት ሆይ ዛሬ በሙሐመድ ላይ የተሰራውን ብታይ ታዝን ነበር" አለችው።
ሐምዛ አንገቱን ደፍቶ አቀረቀረ ሠይፉን አነገበ። ውስጡ በንዴት ነበልባል መቃጠል ይዟል። እሳት ጎርሶ ነቢዩን ሰደቡ ወደ ተባሉት ሰዎች ገሰገሰ። አቡጀህል በቁረይሸ ጣዖታውያን ተከቦ ስለ ሙሐመድ ሲዶልት አገኙት። የሐምዛ አይን ያስፈራ ነበር። ሠይፉን መዘዘ። ከአቡጀህል አናት ላይ አሳረፈው። አቡጀህል ተፈነከተ። የደም ማዕበል ፈሰሰው። ተዘርሮ ወደቀ። በዙሪያው የነበሩት በድንጋጤ ሸሹ።
"እኔ ከዛሬ ጀምሬ ሙሐመድ ይዞት በመጣው እምነት አምኛለሁ። አቅሙን የተማመነ፣ በጉልበቱ፣ በጦር ብቃቱ የሚኮራ ካለ ይሄው ሙሐመድ ላይ የፈፀማችሁትን እኔ ላይ ትፈፅሙት ዘንድ ፊታችሁ ቆሜያለሁ" አለና መንጎራደድ ጀመረ።
መስለሙን የሰሙት ቁረይሾች ተስፋ መቁረጥ ከበባቸው። አደጋ እንደተጋረጠባቸው ተገነዘቡ። የሐምዛ ፈርጣማ ጡንቻ ለቁረይሾች አስጊ ሆነባው። ሁሉም እምነቱን በደበቀበት ወቅት ሐምዛ በልበ ጀግንነተ መስለሙን አውጆላቸው ሠይፉን አንግቦ ወደ ቤቱ ተጓዘ።
ሐምዛ ከጀግንነቱ በተጨማሪ የሰከነ ስሜት፤ ብሩህ አዕምሮ ያለውና አርቆ አሳቢ ነበር። በእርሱ መስለም አላህ እስልምናን ግርማ ሞገስ አላበሰው። ጠላት ገና ሲመለከተው የሚያርበደብደውን ጡንቻውን ለኢስላምና ለሙስሊሞች ጋሻ መከታ በመሆን ያገለግልበት ጀመር። ቁረይሾችም የኃይል እርምጃ መውሰድ እንዳለባቸው ወሰኑ። ለፍልሚያ ዝግጅቱን አጧጧፉት።
ሙስሊሞች ለመጀመሪያ ጊዜ በቁረይሾች ላይ ጥቃት ሲፈፅሙ መሪያቸው ሐምዛ ነበር። ነቢዩም ለመጀመሪያ ጊዜ የኢስሊምን ባንዲራ ያስያዙት ለእርሱ ሆነ። በበድር ዘመቻ ላይ ሐምዛ ታሪክ ሰራ። ብዙ የኩፍር አቀንቃኞች አንገታቸው የሠይፍ ሰለባ ሆነ። ቁረይሾች በሐዘን ተሞሉ። ሞራላቸው ተንኮታኮተ። ወኔያቸው በኖ ጠፋ። ኩራታቸው ተገረሰሰ። ሐብት ንብረታቸው ወደመ። ብዙ ሹማምንቶች የበድር አፈር ቀማሽ ሆኑ። እነ አቡጀህል፣ እነ ኡትባ፣ እነ ኡመያ በድር ላይ አንገታቸው ከተበጠሱት ሰዎች መካከል ነበሩ።
ቁረይሾች በበድር የደረሰባቸውን የሐፍረት ማቅ ለማካካስ ብዙ ጥረት ላይ ናቸው። ከፍተኛ ዝግጅት አደረጉ። በዚህ ጦርነት ሁለት ሰዎችን ከገደልን ሌላው ቀላል ነው አሉ።ሁሉም ተዋጊ እነዚህን ሰዎች ያነጣጥር ሲሉ አሳሰቡ። ለመገደል ከተፈለጉት ሁለት ሰዎች ነቢዩና ሐምዛ ነበሩ።
ሐምዛን የሚገድል ሰው ተመረጠ። አንድ ሐበሻዊ ጦር ወርውሮ የማይስት ወህሽይ የሚባል ባሪያ። ጦሩን አንግቦ ሐሞዛን ብቻ እንዲከታተል ተነገረው። ሐምዛንም ከገደለ ከባርነት ነፃ እንደሚወጣ ቃል ተገባለት። የኢስላም ጠላቶች ሁሌም ኢንቨስት ያደርጋሉ። ወህሽይ ሐምዛን ከገደለ ብዙ ወርቆች በእጁ ይገባሉ። ወህሺይ በሰጦታ ልቡ ማሏል። ኢላማውን ሐሞዛ ላይ ብቻ አነጣጠረ።
ጦርነቱ ተጀምሯል። ሐምዛ በሚያስፈራ ግርማ ሞገስ የጦር ልብሳቸውን ለብሰዋል። በጦሩ ማዕከል ውስጥ ሰይፋቸው ከተሰነዘረ አይስቱም። አንገት ይቀነጥሳሉ። በርካታ ሙሽሪኮች በሐምዛ ሰይፍ አንገታቸውን አጡ። ሙስሊሞች የበላይነቱን ተቆጣጥረዋል። ሙሽሪኮች አሁንም ድል የጠማቸው ይመስላሉ። ጦርነቱ በሙስሊሞች አሸናፊነት ለመደምደም የቀረው ጥቂት ወቅት ነበር። በመጨረሻው ሰዓት ሙስሊሞች ስህተት ፈፀሙ። ጦርነቱ ያበቃ መስሏቸው የአላህ መልእክተኛ አትልቀቁ ያሏቸውን ቦታ ለቀው ምርኮ ለመካፈል ከተራራው ላይ ወረዱ። መሳሪያቸውን ፈቱ።
ድንገት የሙስሊሞች ጦር በካፊሮች እጅ ከፍተኛ ጥቃት ደረሰበት። የሚይዙትን የሚጨብጡት ጠፋባቸው። ብትንትናቸው ወጣ። ይህንን የሙስሊሞች መበታተን ያስተዋሉት ሐሞዛ ኃይላቸውን አሟጠው የተጠጋቸውን ሁሉ ከቀኝም ከግራም እየቀነጠሱ ያጋድሙት ጀመር። ወደ ሐምዛ የቀረበ ሰው ሁሉ አናቱ በሰይፍ ተፈጥፍጦ መሞት ብቻ ነበር እጣ ፋንታው።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ ወህሺይ ጦሩን ሰበቀ። ከሐምዛ እምብርት ላይ አነጣጠረ። ወረወረው። ጦሩ በሐምዛ ደረት በኩል ተሰካ። ሐምዛ ተሸነፉ።
ያ የአላህና የመልዕክተኛው አንበሳ በአንድ ሐበሻ በተሰነዘረባቸው ጥቃት ወደቁ። አይናቸው መገለጥ ተሳናት። እጃቸው ሰለለ። እስትንፋሳቸው አቆመች። ላይመለሱ
ወደ ጀነት ከነፉ። ረድየላሁ አንሁ
በየዘመኑ ስለኢስላም ጥለው የሚዋደቁ መኖራቸው የአላህ ሱና ነው ዛሬም ድረስ የሐምዛን መንገድ የተከተሉ አያሌ ሙጃሂዶች አልፈዋል።

═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ በእናንተ ሰበብ አንድ ሰው ወደ መልካም ነገር ቢመራ እኩል አጅርን ይጎናፀፋሉ

@yemrtoche_twlede
103 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-16 09:56:56 ሰው አንድን ሰው ሲወድ መቼም ቢሆን እንዲለየው አይፈልግም ህይወቴም ሞቴም ከሱ ጋር ያድርገው ሲል ይሳላል ከሱ ጋር መቀስቀስ ይመኛል፡፡ ድንገት የተለየው እንደሆን ሀዘን ይበዛል አብሮት ቢሆን በሃሴት ስሜት ጣሪያ ይነካል፡፡ በርግጥ ከሚወዱት ጋር መሆን ምነኛ ያስደስታል ያ አሏህ!

«ሰውባን» ሰሃባ ነው ምርጥ የነብዩ (ﷺ) ወዳጅና አገልጋያቸው ነው፡፡ የአሏህ መልዕክተኛም (ﷺ) ብዙን ጊዜ ከጎናቸው አይለዩትም ነበር፡፡

አንድ ቀን ግን ነብዩ (ﷺ) በጠዋት ወጡ እስከ ማታም ድረስ ሳይመለሱ ቆዩ፡፡ ወደ ቤት ሲመለሱ ትልቁ ሠውባን እንደ ህፃን ልጅ ቁጭ ብሎ ሲያለቅስ አገኙት፡፡

ነብዩም (ﷺ) ጠየቁት፦ «ምን አስለቀሰክ ሰውባን ሆይ!?»

ሰውባንም፦ «ብቻዬን ትተውኝ ጠፉ እኮ አንቱ የአሏህ ነብይ»

ረሱልም (ﷺ)፦ «ይህ ነው የሚያስለቅስህ»

ሰውባን፦ «አይደለም አንቱ የአሏህ መልዕክተኛ! ሙሉውን ቀንና ሌሊት ብቻዬን ትተውኝ ሲጠፉ ብቸኝነት ተሰማኝ ጀነት ብገባም እንኳን ደረጃዬ ከታችኛው እንደሚሆን አውቃለው እርሶ የአሏህ መልዕክተኛ ኖት እና በጀነት ዉስጥ ደረጃዎት ትልቅ ነው፡፡ በጀነት ከርሶ መለያየቴ አሳሰበኝና ስጋት ገብቶኝ አለቀስኩኝ» አላቸው።

የልብ አካሚው የአሏህ ነብይ (ﷺ) የሰውባንን ስጋት እንዲህ በማለት አቀለሉለት፦ «ሰውባን ሆይ! አንድ ሰው ከወደደው ጋር እንደሚቀሰቀስ አላወክም እንዴ» ብለው አረጋጉት።

አሏህ (ﷻ) እውነተኛ የረሱል (ﷺ) ወዳጅ ያድርገን።

@yemrtoche_twlede
108 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, 06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-15 14:02:02
87 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, 11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ