Get Mystery Box with random crypto!

የመንገዱ ሰዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ yemengedusewoch — የመንገዱ ሰዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ yemengedusewoch — የመንገዱ ሰዎች
የሰርጥ አድራሻ: @yemengedusewoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 280
የሰርጥ መግለጫ

“እኛም በክርስቶስ ፍጹም የሚሆን ሰውን ሁሉ እናቀርብ ዘንድ ሰውን ሁሉ እየገሠጽን ሰውንም ሁሉ በጥበብ ሁሉ እያስተማርን የምንሰብከው እርሱ ነው፤”
— ቆላስይስ 1፥28

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-24 01:06:15 "ምጥን የእሁድ ምስባክ"

ርዕስ፦ እንበልጣለን

መሪ ጥቅስ፦ ማቴዎስ6፥26

በጌታ የተወደዳችሁ ቅዱሳን እንደገና ቅዱስ ቃሉን የምንካፈልበትን ዕድል በማግኘታችን እጅግ አድርገን ጌታን እናመሰግናለን። እንበልጣለን በሚል ርዕስ የጀመርነውን መልዕክት  ክፍል ሁለትን እነሆ ብያለሁ።

“ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም በጎተራም አይከቱም፥ የሰማዩ አባታችሁም ይመግባቸዋል፤ እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን?”

በዚህ ክፍል ጌታ ኢየሱስ ስለ ወፎች ሲናገር እግዚአብሔር ወፎችን እንዴት እንደሚመግብ እና አበባዎችን እና ሣሮችን እንዴት እንደሚያለብስ ተናግሯል። እኛ ግን እነዚህ በተፈጥሯዊ ሂደቶች እንደሚከሰቱ እናውቃለን። ይህ የእግዚአብሔርን መግቦት ያንፀባርቃል።

ይህ ማለት እግዚአብሔር በሁሉም ፍጥረቱ ውስጥ ማለት ነው።  ሁሉም ነገር ሙሉ በሙሉ በእግዚአብሔር ላይ የተመሠረተ ነው። ከዚህ ሁሉ በላይ ለሰው ሕይወትን፣ እስትንፋስን እና ሌሎችንም ሁሉ ይሰጣል (ሐዋ17፡25)።

የእኛ ቅፅበታዊ እስትንፋስ እንኳን ሳይቀር ከእግዚአብሔር ፀጋ ውጭ ሊከሰት አይችልም። ስለዚህ ምንም እንኳን ወፎች ምግባቸውን ቢሰበስቡም፤ እግዚአብሔር ግን በማደናቸው ውስጥ ይሳተፋል፤ እግዚአብሔር በአበባዎች በሚበቅሉ እና ሣሩ ቀለሙን በሚያገኝ ውስብስብ ሂደቶች ውስጥ ይሳተፋል። ይህም የሚያስረዳን በዚህ ዓለም ውስጥ ከእግዚአብሔር ውጭ ምንም ነገር እንደማይከሰት ነው። ይህ ሁሉ የሚሆነው አንድ ሰው “እግዚአብሔር አደረገው” (ኢዮብ 1፡21፣ አሞጽ 3፡6፣ ኢሳ 45፡6) እንዲል በሚያስችል መንገድ ነው።

  ወፎቹ እራሳቸውን ለመመገብ
የሚያደርጉት እርምጃ እራሳችንን እና ሌሎችን ለማቅረብ አሁንም የመሥራት ሃላፊነት እንዳለብን ያስታውሰናል። ጳውሎስ መስራት የማይወድ ሰው መብላት እንደሌለበት ተናግሯል (2ኛተሰ. 3፡10)።

በዚህ ውስጥ ልናየው የሚገባን አንድ ትልቅ ነገር አትጨነቁ የሚለውን የክርስቶስ ትእዛዝ ነው። እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ሉዓላዊ እንክብካቤ ስንረዳ የክርስቶስ ትምህርት መተማመንን መፍጠር አለበት።

ብዙውን ጊዜ ከጭንቀት ጋር የምንታገልበት አንዱ ምክንያት እግዚአብሔር ትቶናል ብለን እናስብና በራሳችን መንገድ መሄድ አለብን ብለን ስንወስንና ስንንቀሳቀስ ነው። አንዳንድ ጊዜ ሀሳቦቻችን እና ተግባሮቻችን ያንን ያመለክታሉ ከዚህም የተነሳ ስንኖር እና ስንሠራ ከፍርሃት እና ከጭንቀት የተነሳ ይሆናል ማለት ነው። ጭንቀትን ማሸነፍ ከፈለግን መንገድ እነሆ እግዚአብሔር ለእኛ ባለው የዝግጅት እንክብካቤ ላይ ማተኮር አለብን። ጭንቀትን ለማሸነፍ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ታላቅ ዋጋ ለይተን ማወቅ አለብን። ይኸውም፦
እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን?

  እኛ አማኞች ከሌሎች የፍጥረት ክፍሎች የበለጠ ዋጋ ያለን በምንድን ነው?

  ጌታ ኢየሱስ “የወፍ አባት” እንደማይባል ልብ ሊባል ይገባል። የደቀ መዛሙርቱ አባት ይመግባቸዋል ይላል። ከዚያም ክርስቶስ “እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን?” አላቸው። ወፎች በእግዚአብሔር መልክ አልተፈጠሩም፥ በአምሳሉም የተፈጠሩ አይደሉም (2ኛቆሮ. 3፡18)። የእግዚአብሔር ወንዶችና ሴቶች ልጆች አይደሉም - ከክርስቶስ ጋር አብረው ወራሾች አይደሉም (ሮሜ 8፡17)።

እግዚአብሔር ሰውን የፍጥረቱ አለቃ አደረገው። በአዲስ ልደት በሚሆነው ጥምቀት ከክርስቶስ ጋር አንድ አድርጎናል። እኛ በእርግጥ ከአእዋፍ፣ ከአበቦች እና ከሳር የበለጠ ውድ ነን። እግዚአብሔር የሚያስፈልገንን ሁሉ እንዲኖረን ምን ያህል ያረጋግጥልናል? ፍላጎታችንን አይሰጠንም፤ አንዳንድ ጊዜ የምንጨነቀው ፍላጎታችን ስለጎደለን ነው። እግዚአብሔር የሚያስፈልገንን እንደሚሰጠን ቃል ገብቷል።
               “አምላኬም እንደ ባለ ጠግነቱ መጠን በክብር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ይሞላባችኋል።” (ፊልጵ. 4፡19)።
              ስለዚህ፣ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ታላቅ ዋጋ ስላልተረዳን ብዙ ጭንቀታችን ይከሰታል። ሮሜ 8፡31-32።

እግዚአብሔር አምላክ ልጁን ስለ እኛ ከሰጠ ለእኛ የሚያስፈልገንን ሁሉ የማያቀርብልን እንዴት ነው? እኛ ከፍተኛ ዋጋ ያለን በመሆኑ እግዚአብሔር ሁሉንም ለእኛ ሰጥቶናል።

ማጠቃለያ፦ እኛ አማኞች ከፍጥረት ሁሉ የምንበልጥ መሆናችንን ተገንዝበን ልንመላለስ ይገባናል። ለዚህም ደግሞ ጭንቀትን ሁሉ ለማስወገድ ልናደርጋቸው የሚገቡን ነገሮች፦
-  ጭንቀትን ለማሸነፍ በጊዜያዊ ጉዳዮች ላይ ከማተኮር ይልቅ #ዘላለማዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ማተኮር አለብን፤
-  ጭንቀትን ለማሸነፍ በአባታችን #የአቅርቦት እንክብካቤ ላይ ማተኮር አለብን፤
-  ጭንቀትን ለማሸነፍ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ታላቅ #ዋጋ ለይተን ማወቅ አለብን፤
-  ጭንቀትን ለማሸነፍ #በራሳችን ውጤታማ እንዳልሆንን ማወቅ አለብን፤
-  ጭንቀትን ለማሸነፍ የጌታን #ተስፋዎች መከተል አለብን፤
-  ጭንቀትን ለማሸነፍ ሁል ጊዜ በእግዚአብሔር #ጸጋ ላይ ማተኮር አለብን፤

                      አበቃሁ!
                 
                      መልካም ሳምንት

ዘላለም ተሾመ (ወንጌላዊ)

@yemengedusewoch
@SolenTse
+251941214813
140 viewsSolomon Tsegaye, edited  22:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 01:05:47
131 viewsSolomon Tsegaye, 22:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 05:24:35
ከኃዘን ድባብ ውጡ!

አሁን ላላችሁበት ሁኔታ የእናንተ የትናንትና ምርጫና ውሳኔያች መዋጮ ኖረውም አልኖረውም፣ ሙሉ ሃላፊነቱን ካልወሰዳችሁ፣ በኃዘን ድባብ ውስጥ ስለምትኖሩ ወደ ኋላ ትንሸራተታላችሁ፡፡ “ዛሬን እንደዚህ የሆንኩት ከእገሌ የተነሳ ነው” ብለን ማሰባችን፣ መናገራችንና ሰውን መውቀሳችን ከሃላፊነት አያድነንም፡፡

ዛሬ ላለንበት ሁኔታ ሙሉ ሃላፊነት መውሰድ ስንጀምር ነገ ወደየት አቅጣጫ መሄድ እንዳለብን ጥርት አድርገን ማየት እንጀምራለን፡፡

የትናንትናችንን በመራራነትና በወቃሽነት ስሜት ማሰብ የሚያስከትለው የኃዘን ድባብ የነገውን የማየት አቅማችንን ይጋርደዋል፡፡

ለትናንትናው ስህተት መድሃኒቱ የነገ ራእይ ነው፡፡ የነገን ራእይ ለማየት ደግሞ ዛሬ ላለንበት ሁኔታ ሙሉ ሃላፊነትን በመውሰድ ካለብን ኃዘን መላቀቅ የግድ ነው፡፡

አዲስ ምልከታ፣ አዲስ እቅድ፣ አዲስ ጅማሬ፣ አዲስ ግንኙነት፣ አዲስ ሃሳብ . . . ያዙ! ካለፈው ተማሩ! ያለፈውን ተው! የወደፊት ሕይወታችሁ ያለው ነገ ላይ ስለሆነ ነገን ናፍቁ!

https://t.me/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
94 viewsSolomon Tsegaye, 02:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 07:14:31 "ምጥን የእሁድ ምስባክ"

ርዕስ፦ እንበልጣለን

መሪ ጥቅስ፦ ሮሜ. 8፥37

“በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን።”

በጌታ የተወደዳችሁ ቅዱሳን እንደገና ቅዱስ ቃሉን የምንካፈልበትን ዕድል በማግኘታችን እጀግ አድርገን ጌታን እናመሰግናለን።

ከላይ ያነሳነውን መሪ ጥቅስ ከመመልከታችን በፊት በቁጥር 35 ላይ፣ ጳውሎስ በዚህ ህይወት ውስጥ በአንድ ሰው ላይ ሊደርሱ የሚችሉ በርካታ አስከፊ ነገሮችን ዘርዝሯል። የእርሱ ነጥብ ማንኛቸውም በክርስቶስ ውስጥ ያለነውን ለእኛ ካለው ፍቅር ሊለዩን እንደማይችሉ ነበር። በክርስቶስ እንዳንሆን ወይም ክርስቶስ እንዳይወደን የሚከለክል ወይም ክርስቶስ ከእንግዲህ እንደማይወደን የሚያረጋግጥ አስከፊ ነገር በእኛ ላይ ሊደርስ አይችልም።

በዚህ ቁጥር ውስጥ አጽንዖት ሰጥተን ልንመለከታቸው የሚገቡን ሦስት አሳቦችን እንይ፦

1.  በዚህ ሁሉ ግን፦

ይህም ማለት በችግር፣ በመከራ፣ በረሃብ . . . በመጋለጥ፣ ዛቻ ወይም ዓመፅ “በወደደን [በክርስቶስ] ከአሸናፊዎች እንበልጣለን” ሲል ጽፏል። ይህ መግለጫ ያልተለመደ፣ እጅግ የላቀ ድል፣ ቀጣይነት ባለው ሁኔታ፡ ለዘላለም በድል መጨመር የሚለውን ሃሳብ ይይዛል።

ከእነዚህ ችግሮች መካከል አንዳቸውም በእኛ ላይ አይደርሱም ወይም በዚህ ሕይወት ውስጥ ልናስወግዳቸው እንችላለን ማለት አይደለም፣ በግልጽ አይደለም፣ በዚህ ምንባብ አውድ ላይ በመመስረት። ከዚህም በላይ፣ ብዙዎቹ በጳውሎስ ላይ እንደደረሱ ልብ ማለት ያስፈልጋል (2ኛ ቆሮንቶስ 11፡23–29)።

2.  በወደደን በእርሱ፦

ክርስቶስ እኛን የወደደበት መውደድ ነፍሱን እስከ መስጠት ድረስ መሆኑን የእግዚአብሔር ቃል ይነግረናል፤

“ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም።” ዮሐ.15፥13

የመጨረሻው የፍቅር ተግባር ራስን በፈቃደኝነት መስጠት ነው። ክርስቶስ ለኃጢአተኛ ሰዎች እንዲህ ያለ መስዋዕት ማድረጉ ከቃላት በላይ ነው (ዮሐንስ 10፡17–18፤ ሮሜ 5፡7–8)።

የመብለጣችን ምክንያት ኢየሱስ መሆኑን ማስታውስ ያስፈልጋል።

3.  ከአሸናፊዎች እንበልጣለን፦

ይልቁንም፣ በክርስቶስ በማመን የዳኑት (ሮሜ.3፡23–26፤ ዮሐንስ 3፡16–18) ክርስቶስ ለእኛ በጣም አስፈላጊ የሆነውን ድል እንዳገኘ በማሰብ እነዚያን አስፈሪ ነገሮች አሸንፈዋል። ያ ድል፣ በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ ያለን ቦታ፣ በክብሩ ርስት ውስጥ ያለን ድርሻ በምንም መንገድ ከእኛ ሊወሰድ አይችልም። እኛ የምናሸንፈው አሸናፊዎችን ሁሉ ነው። ሰዎችን የሚያሸንፉ አሸናፊዎች ብዙ ቢሆኑም እንኳን እኛ በክርስቶስ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን።

በክርስቶስ የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሆይ ከወደደን ጌታ የተነሳ እኛ ከአሸናፊዎች እንበልጣለንና ሁልጊዜ በሚበልጥ መንፈስና ማንነት መመላለስ ይሁንልን።

አሜን!!

ዘላለም ተሾመ (ወንጌላዊ)

@yemengedusewoch
@SolenTse
+251941214813
260 viewsSolomon Tsegaye, edited  04:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 07:07:27
216 viewsSolomon Tsegaye, 04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 00:05:36 "ምጥን የእሁድ ምስባክ"

ርዕስ፦ “የሕይወትን/የአገልግሎትን ሩጫ እንዴት እንሩጥ?”  (ክፍል-3)

የንባብ ክፍል=ዕብ12፡1-2

በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያተኮሩ የመጽሐፉ ቁልፍ ጥብጦች መካከል፦

ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ እና ፍጹም ሰው ነው (1፡1-4፣ 2፡5-18)፣

ይህ መጽሐፍ የኢየሱስ ክርስቶስን ፍጹም አምላክነትና ሰውነት በተገቢው ሁኔታ ዘግቧል። የኢየሱስን ፍጹም ሰውነት ስንቃኝ፦
1) እንደሰው ጸልዮአል#  ስለጸሎትም አስተምሯል፤ እንደሰው ተፈትኗል በፈተናውም አልፎ የሚፈተኑትን ይረዳል፤ እንደሰው መከራ ተቀብሏል በመከራ የምንጸናበትን/የምንታገስበትን አቅም ይሰጠናል፤ እንደሰው ሞቷል ከሞት ፍርሃት ነፃ አውጥቶናል!

ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ፣ የመጨረሻው የእግዚአብሔር መገለጥ፣ ፈጣሪ፣ የፍጥረት ደጋፊ/መጋቢ (1፡1-14)
ኢየሱስ ክርስቶስ ለዘላለም እንከን የሌለበት ሊቀ ካህን ነው (1፡3፣ 2፡10-18፣ 4፡15-16፣ 9፡10-11፣ 19)፣

ሊቀ ክህነቱም ከመልከጸዴቅ ጋር ተነጻጽሯል፣ ራሱ ካህን ነው እዲሁም እንከን የሌለበት መስዋዕት ነው፣ ካህኑ በነገር ሁሉ የተፈተነ ስለሆነ የሚፈተኑትን የሚረዳና የሚረዳ ነው፣ ምንም ኃጢአትን አላደረገም፣ ክህነቱም በሞት ምክንያት የሚገታ ሳይሆን በሰማይም የሚቀጥል ነው፣ እርሱ ለራሱ መስዋዕት መቅረብ አላስፈለገው ለሌሎች ቤዛነት እንጂ፣…

ኢየሱስ ክርስቶስ ከነቢያት፣ ከመላዕክት፣ ከአሮጌው ኪዳን፣ ከአሮን ክህነት፣ ከመገናኛው ድንኳን/መቅደስ፣ ከብሉይ ኪዳን መስዋዕት፣… ይበልጣል (1፡4-2፡18፣ 3፡1-6፣ 5፡1-10፣ 7፡1-10፣18)፣
የሁሉም ነገር ፍጻሜ በኢየሱስ ክርስቶስ በመጀመሪያ ምጽዓቱ ተጀምሯል በዳግም ምጽዓቱ ይጠናቀቃል (1፡2፣ 9፡9-28፣ 12፡22-29)።

ክርስቶስ ላይ ማተኮር ስንል፡-

ክርስቶስን መመልከት/በእርሱ ላይ ማተኮር ቅጽበታዊ እይታ ሳይሆን ሁልጊዜ በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የሕይወታችን መልዕቅ፣ ሮል ሞዴል፣ የድልና የአሸናፊነታች መሰረት ማድረግ ማለት ነው፣

ውጤታማ የእምነት ሩጫ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ዓይንን/ አትኩሮትን በማሳረፍ የሚመጣ ነው፣

እውነተኛ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር በክርስትና ሩጫ ውስጥ የሚገጥመውን ፈታኝ ሁኔታዎች ክርስቶስ ላይ በማተኮር በጽናት ሊወጣቸው ይገባል፣

የክርስትናን ሩጫ ክርስቶስን በመመልከት የሚሮጥ ሩጫ ነው፤ ለዚህም ክርስቲያኖች ክርስቶስን እንዲመለከቱ ጥሪ ቀርቦላቸዋል (12፡1-2፤ 6፡11-12፤ 3፡1-2)፣
በዘመናችን ያለችውም ቤተ ክርስቲያንም በዘመኑ ካሉ ፈታኝ ሁኔታዎች ራሷን ለማስመለጥ እንድትችል ዛሬም አይኗን በክርስቶስ ላይ አድረጋ መሮጧ አማራጭ የሌለው አስገዳጅ ነገር ነው፣

ኢየሱስ እንከን የሌለበት የእምነት ሯጭ መሆኑን በእረኝነቱ፣ በመሪነቱ፣ በካህንነቱ፣ በአስተማሪነቱ፣ በአገልጋይነቱ፣ በጽናቱ፣ በትዕግሥቱ፣ በማይቀፍ ሕይወቱ፣ ወዘተ አሳቷል።

ኢየሱስ የእምነታችን ራስና ፈጻሚ ነው
“ራስ” (originator, founder, leader, pioneer) “የሕይወትንም ራስ ገደላችሁት…” (ሐዋ. 3፡15)፣ “…ራስም መድኃኒትም አድርጎ በቀኙ ከፍ ከፍ አደረገው።” (ሐዋ. 5፡31)። ስለሆነም ጌታ ኢየሱስ እንደመሪ ሌሎችን የሚያስቀድም ትሁት መሪ ነው (ዮሐ. 13)።

“በፊቱ ስላው ደስታ መስቀሉን ታግሦ የመስቀሉን ውርደት ንቆ” (ዓመት)
“በፊቱ ስላለው ደስታ”፡ የኢየሱስ ሩጫ ግብ ያለው ሩጫ ነበር። ይህም ነፍሱን ለኃጢአተኞች ቤዝዎት በመስጠት የሚያጠናቅቀው ዋንኛ ደስታው ነበር። የኢየሱስ ደስታ በእርሱ የመስዋዕትነት የመስቀል ሞት የሚድነውን ከቁጥር በላይ የሆነ ሕዝብ ወደ ፊት አሻቅቦ ተመልክቶ የመስቀሉን ውርደት ታግሷል (ማር. 10፡45፣ ዮሐ. 15፡11፣ ሉቃ. 10፡20-21)።

“የመስቀል ሞት”

ኢየሱስ የእምነትን ሩጫ ከግርግም እስከ መስቀል በሚገባ ሮጦ የፈጸመ ሯጭ ነበር (ሉቃ.2፡7፤ ዮሐ.17፡3-4፣ 19፡30፤ ፊል.2፡8)
ክስ (ወንጀለኛነት/ እርግማን፣ ግርፋት፣ መዘባበቻ መሆን፣ ምራቅ መተፋት፣ ጥፊ፣ ስድብ፣ ፌዝ፣ በጦር መወጋት፣ አጥንት መሰበር፣ የእሾህ አክሊል፣ መቸንከር፣ መስቀል ተሸክሞ ረዥም ጉዞ ማድረግ፣ ጥም (የባሕርና የውቅያኖስ ፈጣሪ)፣ በአምላክ መተው፣…  (ፊል. 2፡6-8)፣“በእንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር፤ ነገር ግን አምላክህ እግዚአብሔር ርስት አድርጎ የሰጠህን ምድር እንዳታረክስ በእርግጥ በዚያው ቀን ቅበረው። (ዘዳ. 21፡23፣ ገላ. 3፡13)፣

መስቀል የጣር ስፍራ፣ የመተው ስፍራ፣(ማቴ.27፡46)

በመስቀል ላይ ጌታ ኢየሱስን የተገረፈው፣ የተቸነከረውን ቁስል በዝንቦች እንኳን ሲበላ እሽ ማለት አለመቻል (ኢሣ. 53፡4-6)፣
ጌታ ኢየሱስ ስቃዩን ለማደንዘዝ/ለመርሳት በባህላዊ ማደንዘዣ አልወሰደም (ማቴ.27፡34)!

በመስቀል ላይ ሸክሙን ለመያዝ ወደላይ መሳብና የተቸነከረበት ሚስማር የሚፈጥረው መተልተል፣… ማሰብ ከአእምሮ በላይ ነው!
በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና
“እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።” (2)

ጌታ ኢየሱስ ሰው በመሆን በቤተልሔም የጀመረው ሩጫ እስከ መስቀል ሞት በመሞት እስከታችኛው ወለል ድረስ ዝቅ በማለት ትህትናን አሳይቷል። መክበሩ ደግሞ ከሞት በመነሳት፣ በማረግና በአባቱ ዙፋን ቀኝ በመቀመጥ አሳይቷል።

ጌታ የመጨረሻ የሚባለውን በመስቀል የመሞት ጽነትና ትዕግሥትን ምሳሌ፦

“…በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው። ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ፤…” (ፊል. 2፡1-12)

ማጠቃለያ፦ ከላይ በዝርዝር እንደተመለከትነው የክርስቶስ ደቀ መዝሙርነት በሩጫ የተመሰለ የሕይወት ዘይቤ ነው። ሩጫው እጅግ ትዕግሥትንና ጽናትን የሚጠይቅ እደሆነ እሙን ነው። ሩጫውን የጀመረ ሁሉ ደግሞ አይጨርስም። ስለሆነም በዚህ የሕይወትና የአገልግሎት ሩጫችን በውጤታማነት ለመጨረስ በእምነት የሩጫ ሜዳ ላይ በመፋለም ሩጫቸውን የጨረሱትን የእምነት አባቶች ጽናት ዋቤ በማድረግ (11 እና 1ሀ)፣ ለውጤታማ ሩጫ እንቅፋት የሚሆኑ ሸክሞችንና የኃጢአት ልምምዶች ከሕይወታችን በማስወገድ (1ለ) እንዲሁም የሃይማኖታችን ሐዋርያና ሊቀ ካህን (3፡1)፣ የእምነታችን ራስና ፈጻሚ (12፡1-2) በሆነው በክርስቶስ ላይ በማተኮር ሩጫችንን በጽነት ልንፈጽም ይገባናል።

እግዚአብሔር የጸጋ ሁሉ አምላክ ይርዳን!

አበቃሁ!!

ዘሪሁን ታከለ (አስተማሪ )

@yemengedusewoch
@SolenTse
+251941214813
329 viewsSolomon Tsegaye, 21:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 00:04:42
251 viewsSolomon Tsegaye, 21:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 07:46:31 በ - ምክንያት መታጠር ሰበቡ ቀርቶብኝ
ግ - ላዊ ተሀድሶ እንደሚያስፈልገኝ
ል - ወቅ አስቀድሜ በቅጡ ልረዳ
መ - ታዘዝን ልልመድ ልግባ ወደ ጓዳ
ታ - ሪክ ብቻ ሆኜ ዘመኔ እንዳያልቅ
ደ - ስታ ሰላም ርቆኝ ተዳክሜ ሳልወድቅ
ስ - መለስ መልሰኝ ከአንተ ጋር ልታረቅ
1.1K viewsSolomon Tsegaye, 04:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 07:52:28 የእንደገና መርሆች!

እንደገና ሊታረም፣ ሊታደስና በአዲስ መልክ ሊጀመር የማይችል ምንም አይነት ስህተት እንደሌለ በማስታወስ ሳምንታችሁን ጀምሩ፡፡

የማይንቀሳቀስን ነገር ሁሉ ሕይወት የሌለው ግዑዝ ፍጥረት እንለዋለን፡፡ የሚንቀሳቀሰውን ደግሞ ሕይወት ያለው ሕያው ፍጡር እንለዋለን፡፡ ሕይወት ካለ መንቀሳቀስ አለ፡፡ መንቀሳቀስ ካለ ደግሞ ስህተት የማይቀር ነው፡፡ ለስህተት ሊሰጥ የሚገባው ትክክለኛው ምላሽ - እንደገና መነሳት! እንደገና መጀመር! እንደገና መገስገስ! እንደገና!!!

ሆኖም፣ ይህንን የእንደገና አመለካከት ተግባራዊ፣ ሚዛናዊና ጤናማ የሚያደርጉልንን መርሆች አንዘንጋ፡፡

1. ይቅርታ መጠየቅ - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ስህተቱ የጎዳው ሰው ካለ ይቅርታን መጠየቅ የግድ ነው፡፡

2. ይቅርታ ማድረግ - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ስህተቱ የተከሰተው በሰዎች ሰበብ ከሆነ ሰዎቹን ይቅር ማለት የግድ ነው፡፡

3. በራስ ላይ አለመጨከን - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ በሰራችሁት ስህተት ምክንያት ራሳችሁን ከመደብደብና ከመኮነን መቆጠብ የግድ ነው፡፡

4. ከስህተቱ ትምህርት ማግኘት - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ከተሰራው ስህተት ያላችሁ ብቸኛ ትርፍ፣ ያገኛችሁት ትምህርት መሆኑን በማወቅ ትምህርታችሁን መውሰድና ስህተቱ እንዳይደገም ማቀድ የግድ ነው፡፡

5. እንደገና መጀመር - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ የተሰራውን ስህተት በማስተካከል እንደገና መጀመር የግድ ነው፡፡

6. በአዲስ መቀየር - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ሊታደስ የማይችሉ ሁኔታዎች ካሉ እነዚህን ሁኔታዎች ስታብሰለስሉ መዋል ማደሩን ትታችሁ በአዲስ በመቀየር ወደፊት መራመድ የግድ ነው፡፡

7. ከ“ግን” መጠበቅ - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎች የእንደገና መነሳት መርሆችን እንዳትተገብሩ ከሚያደርጋችሁ፣ “አዎ፣ ግን . . .” ከሚል ምክንያት ፈላጊነት መጠበቅ የግድ ነው፡፡

https://t.me/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
161 viewsSolomon Tsegaye, 04:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 07:52:11
የእንደገና መርሆች!
126 viewsSolomon Tsegaye, 04:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ