Get Mystery Box with random crypto!

⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ◎⃝ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ »‌✺◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝✺»‌◎⃝ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ | የማርያም መቀነት

⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ◎⃝ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ »‌✺◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝✺»‌◎⃝ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ◎⃝ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ ⃟ »‌

“በሀገራችን፥ ፍትህ ስደተኛ ናት፡ ከሰው ልብ ሸሽታ፣ በገዥዎች ሸንጎ ጥገኝነት የምትጠይቅ ደጅ ጠኝ ሆናለች። ሰው ራሱን መግዛት ሲያቅተው ' ከመንግስት ልብ ያዛል' ነበር የሚባለው? ለምን ይመስልሻል?”

"ልብ በተጨባጭ ያለን፥ መንግስት ደግሞ በተጨባጭ የሌለን ስለሆነ ነዋ!" አልኩት።

“ቀጣፊ ዱርዬ!” አለኝ። ማሾፌ መሆኑ ገብቶታል።

“በልቦናችን ፍትህ፣ እውነትና ሃቅ ሁሉ ስለነበሩ ነው። ግን ተገፉ። ራስ ወዳድነት፣ አስመሳይነት እና ስስት ተበራክተው ፍትህን አደቀቋት፣ ደበደቧት። መውጫ መግቢያ ነሷት። ሸሸች። ከሰው ልብ ጠፋች። ከሜዳ ሜዳ ስትዞር ከመንግስት ስር መጠጊያ አገኘች። መንግስት ደግሞ እንደ ማንኛውም ስደተኛ ንብረቱ አደረጋት፡፡ ሲያሻው ሰጥቶ ሲያሻው የሚነፍጋት ሆነች::

ሰው ከልቡ ያለውን ፍትህ አባርሮ፥ መንግስትን መልሰህ ስጠኝ ቢል ከየት ይሰጠዋል? እርሷ እንደሆን ዜግነቷን ቀይራለች፡፡ ከዚህ በኋላ በመንግስት ፍቃድ እንጂ በሰው ፍላጎት ኣትገኝም። ሰጭና ከልካይ አላት። 'ሰዶ ማሳደድ ካማረህ፥ ዶሮህን በቆቅ ለውጥ ይሉ ነበር የሀገራችን ሰዎች ሲተርቱ። እኛም ያው ሰዶ ማሳደድ አማረንና ፍትህን በጭቆና ቀየርን። ልባችንን ጭቆና ሞላው። ጨቋኝ ሰው እንጂ ጨቋኝ መንግስት የለም። ሰው በልቡ ከፋ፣ ጨቋኝ ሆነ። ፍትህ ብን ብላ ሄደች።
◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝
አለማወቅ