Get Mystery Box with random crypto!

ይሰበካል የእዉነት ወንገል

የቴሌግራም ቻናል አርማ yeihunetwongel — ይሰበካል የእዉነት ወንገል
የቴሌግራም ቻናል አርማ yeihunetwongel — ይሰበካል የእዉነት ወንገል
የሰርጥ አድራሻ: @yeihunetwongel
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 720
የሰርጥ መግለጫ

ወደ አለም ሀሉ ሂዱ ወንገልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፡፡ያመነ የተጠመቀ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል፡፡ማርቆስ 16:15
@Any comment
@Altishyeapo

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-03-03 23:58:14 #ቀጠሮ አለኝ ዋራ!

አለኝ አንዳች ሚስጢር
አለኝ አንድ ነገር
ለሰው ሳይሆን ለኢየሱስ የሚነገር

ቀርቤ የማዋየው አለኝ አንድ ጉዳይ
በቅዱሱ ስፍራ በዋራ ሜዳ ላይ

አለኝ አንዳች ነገር ነፍሴን ያነቀ
ጠፍሮ የያዛት ልቤን ያስጨነቀ
ለሰው የማላወራው ውስጤን የረበሸኝ
ለኢየሱስ የምነግረው አንዳች ነገር አለኝ

ጌታዬ ቀጥሮኛል ሊያገኘኝ በዋራ
ዝም ብሎ ሊሰማኝ የልቤን ሳወራ

ታምራቱን እንዳይ የእጆቹን ስራ
ታዳሚ እንድሆን በቅዱሱ ስፍራ
በአምላኬ ግብዣ ቀጠሮ አለኝ ዋራ

እሰይ ቀኑ ደረሰልኝ ልቆም በአባቴ ፊት
ልወጣ ነው በቃ የሁለት አመት ናፍቆት

የከበደኝን ሁሉ ለእሱ ተንፍሼ
አዲስ ሰው ልሆን በብዙ ታድሼ

ለሶስት ቀናት ከእቅፉ ልሰነብት
ክብሩን ለማየት በቅዱስ ሕዝቡ ፊት

ሀጢያቴ በሙሉ በምሕረቱ ተደምስሶ
ከሕይወቴ ጠፍቶልኝ ሀዘንና ለቅሶ

በጉጉት ልሰማ ቃሉ ሲሰበክ
ጉልበቴን ሳልሰስት ከልቤ ለማምለክ

የድልን ችቦ በደማቁ እንዳበራ
አመቱን ጠብቆ ደረሰልኝ ዋራ

Link @MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH


@Taddyapostolic

comment @Taddyapostolic or

@marantawoch group
273 views20:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-03 23:47:54 #ቀጠሮ አለኝ ዋራ!

አለኝ አንዳች ሚስጢር
አለኝ አንድ ነገር
ለሰው ሳይሆን ለኢየሱስ የሚነገር

ቀርቤ የማዋየው አለኝ አንድ ጉዳይ
በቅዱሱ ስፍራ በዋራ ሜዳ ላይ

አለኝ አንዳች ነገር ነፍሴን ያነቀ
ጠፍሮ የያዛት ልቤን ያስጨነቀ
ለሰው የማላወራው ውስጤን የረበሸኝ
ለኢየሱስ የምነግረው አንዳች ነገር አለኝ

ጌታዬ ቀጥሮኛል ሊያገኘኝ በዋራ
ዝም ብሎ ሊሰማኝ የልቤን ሳወራ

ታምራቱን እንዳይ የእጆቹን ስራ
ታዳሚ እንድሆን በቅዱሱ ስፍራ
በአምላኬ ግብዣ ቀጠሮ አለኝ ዋራ

እሰይ ቀኑ ደረሰልኝ ልቆም በአባቴ ፊት
ልወጣ ነው በቃ የሁለት አመት ናፍቆት

የከበደኝን ሁሉ ለእሱ ተንፍሼ
አዲስ ሰው ልሆን በብዙ ታድሼ

ለሶስት ቀናት ከእቅፉ ልሰነብት
ክብሩን ለማየት በቅዱስ ሕዝቡ ፊት

ሀጢያቴ በሙሉ በምሕረቱ ተደምስሶ
ከሕይወቴ ጠፍቶልኝ ሀዘንና ለቅሶ

በጉጉት ልሰማ ቃሉ ሲሰበክ
ጉልበቴን ሳልሰስት ከልቤ ለማምለክ

የድልን ችቦ በደማቁ እንዳበራ
አመቱን ጠብቆ ደረሰልኝ ዋራ

@Taddyapostolic

comment @Taddyapostolic or

@marantawoch group
246 views20:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-19 15:14:37 @yeihunetwongel አንርሳ • ስንወጣ መፀለይ ስንገባ ማመስገንን አንርሳ • መፆም መፀለይን አንርሳ • መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብን አንርሳ • ለአገልግሎት እጅግ መትጋትን አንርሳ • የከበረ ደሙን እንዳፈሰሰልን አንርሳ • ሀጢአታችንን በደሙ እንዳጠበልን አንርሳ • ብዙ ምህረት እንዳደረገልን አንርሳ • ነፍሱን እስከ መስጠት እንደወደደን አንርሳ • ከድቅድቅ ጨለማ እንዳወጣን አንርሳ • ከወደቅንበት…
854 views12:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-10 17:55:43
623 views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-26 21:44:20 የግል መዝሙር

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የተማሪዎች ህብረት
(wachemo fellowship)

ዘማሪ እያኤል ሳሙኤል

እኔ ማነኝ

አቤቱ እኔ ማነኝ ውድህ የመጣልኝ
ዋጋዬን ከፍ አርገህ በኩሩን ሸለምከኝ
የኃጢአቴን ዋጋ አይከፍልም ናርዶስ
ግን ልብህ ራራልኝ ተቀበልከኝ ኢየሱስ

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
770 views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-08 00:24:05 ጭንገፋው በቃ ተገኘ ምሕረት

በእህት ሰላም

ተንኮለኛው እባብ አዳምንና ሴትቱን ስላሳተ በተንኮል
በአንተና በሰትቱ መካከል በዘርሕና በዘርዋ መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ ራስህንም ይቀጠቅጣል አንተም ሰኮናውን ትቀጠቅጠዋለህ ፤

እግዚአብሔር አምላክም አለ፦
እነሆ አዳም መልካሙንና ክፉውን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ አሁንም እጁን እንዳይዘረጋ ከህይወት ዛፍ እንዳይበላ ለዘላለም ህያው ሆኖ እንዳይኖር አደረገው።

እግዚአብሔር አዳምን ከኤደን ገነት አወጣው
በአንተና በሰትቷ መካከል በዘርህና በዘርዋ መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ እርሱም ራስህን ይቀጠቅጣል ብሎ ቀጠሮ ሰጠ እንጅ በል ተነሳና ቀጥቅጥ አላለውም
አዳምም ሆነ በሴትቱ የተወለዱ ልጆቻቸው
እነ ቃዬን እነ አቤል እባቡን ለመቀጥቀጥ አቅም ስለሌላቸው የእባቡን ጭንቅላ ልቀጠቅጡ አልቻሉም
እንድሁም ሙሴ ፌርኦንን አሸነፈ እንጅ
ከፌርኦን በስተጀርባ ያለውን ልያባርር አልቻለም
ዳውትም በ እግዚአብሔር ፍት እየሄደ አምላኩን አስደሰተው ደግሞም ፍልስጠማውያንን አተረማመሳቸው

ይሁን እንጅ አንድም ሴጣን አላወጣም
ገና ክፉ መንፈስ የገባበትን ሳኦልን ሸሸው
ኤልያስም ብሆን ሰማይ ያስከፍታል
እምነቱ ሀያል ነው ስያስፈልግ ያዘጋል
አምላኩን ይለምናል ድንቅ ታምራትን ይደርጋል
ይሁን እንጅ አንድም ሴጣን አላወጣም በፅዮን የምኖር
እልፍ አእላፍት የምሰግዱለት 24ቱ ሽማግሌዎች ከፍቱ ሳይርቁ የምሰግዱ ቀን ከሊቲ ያ ሁሉም ሆኖ ከእኛ ፍቅር ጋር ስላልተመጣጠነለት ሀያሉ ጌታ፦

ወገኔ በከንቱ ተወስዶአል አሁንስ በዝህ ምን አለኝ ብሎ
የእባቡ ጭንቅላት የመቀጥቀጡ ግዜ ደርሶ
መንፈስ የነበረው ስጋን ለብሶ የሴጣንን አናት መቀጥቀጥ የምችለው ጌታ ባልታሰበና ባልተጠበቀ መንገድ መጣ።

" እነሆ ድንግል ትፀንሳለች
ወንድ ልጅም ትወልዳለች
ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች "

የተባለው ይፈፀም ዘንድ የትንብቱ ቃል
እነሙሴ ስለ እኔ ፅፈዋል ስል የነበረው
በምድር ላይ ነግሳለሁ ብሎ ያሰበው
ወደ አለም ስመጣ ያ ሀያሉ ጌታ አለቀለት በቃ አጋንንት ተመታ ሰው መንገድ ማለፍ እስክሳነው ድረስ
እጅግ ክፉ የነበረው ያ ሌግዎን መንፈስ

"እየሱስ ሆይ የእግዚአብሔር ልጅ ከአንተ ጋር ምን አለኝ
ግዜው ሳይደርስ ልታሰቃየኝ ወደ እዝህ መጣህን" እያለ ጮኼ ።

ግጥም፦ #ጭንገፋው_በቃ_ተገኘ_ምሕረት

ሰይጣን ግዜውን ረስቶ
ሳአቱ መድረሱን አላወቀም ከቶ
እየሱስማ ግዜውን ጠብቆ ሰዐቱን አይቶ
የእባቡን አናት ልቀጠቅጥ ከዙፋኑ ተነስቶ
እጁን ዘርግቶ ከሕይወት ዛፍ እንዳይበላ
ባስቀመጠው ስፍራ ለዘላለም ህያው ሆኖ እንዳይኖር ከኤደን ገነት የወጣውን የአዳምን ዘር
ከተበታተኑበት ሰብስቦ ሀጥያታቸውን ይቅር ልል
አምላክ ስጋን ለብሶ ወደ ምድር መጥቷል/2*
አምላክነቱን ትቶ የባርያን መልክ ይዞ
ክብሩን ጥሎ ፍቅርን ይዞ
የልጆቼ እስራት በቃ ከእንግድህ ብሎ
ከራሱ ጋር ልያስታርቀን ራሱን አዋረደ
የተወለደው ህፃን ሆነ የአለም ብርሃን
በቤቴልሄም ተወልዶ በከብቶች በረት
መድሀንት ሆነ አመጣ ምሕረት
ምስጥሩ የገባቸው የህፃኑ ማንነት
አማኑኤል ነው አሉ ወድቀው ሰገዱለት
ሰባ ሰገዶቹ የዕጅ መንሻ አመጡለት
#ጭንገፋው_በቃ_ተገኘ_ምሕረት / 2*

አምላክ በስጋ የተገለጠበት ትልቁ አላማ
እኛን ለማዳን ነው ከእባቡ ግዛት
ሀሉን እየቻለ ሁሉ የዕርሱ ሆኖ
ፍቅር አስገድዶ አላስችል አለው
በእባቡና ጊንጡ ላይ ስልጣን ሰጠን
አጋንንት ምንቀጠቀጥበትን ስሙን አሳወቀን የምናሸንፍበትን መንገድ አሳየን የልጅነትን
ስልጣን መልሶ አወረስን
እባቡን ለመቀጥቀጥ አጋንንትን ለማውጥት
ስልጣን ሰጠን ወርዶ ከሰማያት
ቀድሞ ወገን ላልነበረን ወገን ልሆነን
በሽተኞች ሳለን መድሃንት ልሰጠን
በጨለማ ሳለን ብርሃን ልያበራልን
የምንሸሸውን ክፉ መንፈስ እንድንገስፀው
የእባቡን አናት እንድንቀጠቅጠው
ከኤደን ገነት የወጣነውን የአዳምን ዘር
ዳግም እንድንወለድ ከውሀና ከመንፈስ
#የሁሉ ቤዛ የሆነ መጣ እየሱስ /2*

በእ/ት ሠላም

join join join

&

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
711 views21:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 02:36:57 ተፈፀመ ቃሉ

ቃሉ ሰጋ ሆኖ የመገለጥ ነገር
ለአይን ድንቅ ነው ለጆሮ ተዐምር
ቢሆንም እንግዳ ያልተለመደ አዲስ
ትንቢት ተፈፀመ እግዚያብሄር ሊዳሠሥ
ማድረግ ያለበትን የዘመናት ዕቅድ
ያለተቀናቃኝ ሊፈፅመው ቢወርድ
ስለሠው ዝቅ ቢል ስለሠው ቢጎዳ ፤
ለታሠረው ቢዋስ ቢከፍልለት ዕዳ
ማን ጣልቃ ይገባል
በእግዚአብሔር አጀንዳ ።

ያን ብርቱ ማህተም በጥበብ የፈታ
ኤልሻዳይ ተብሎ የተጠራ ጌታ
የዘንዶውን ራስ ቀጥቅጦ ከመታ ፤
ሁሉን ማከናወን መፈፀም የሚያውቀው
ይህን ካደረገ ምንም አልተሳነው ።
ልዕልናው በዝቶ ሆኖ ባለጠጋ
ስም ይዞ ቢገለጥ እግዚያብሄር በስጋ
በምስሉ እነደሠው የመምጣቱ ዝና
ከሜዶናውያን ከፋርስ ህግ የፀና
ከቶ የማይለወጥ አድርጎት ገናና
ውል የቀረፀበት የአዲስ ኪዳን አርማ
ትውልድ እንዲማረው ፍጥረት እንዲሠማ

ንጉሱ ተስማምቶ ወዶ ከፈረመ
ባበቃ ነገር ላይ በተደመደመ
ሙግት ምን ይጠቅማል
ቃሉ ተፈፀመ ።
ፈርሶ የሚሠራው የእግዚአብሔር መቅደስ
በውስጥ እሱነቱ አብ ቢሆን ኢየሱስ
ይግባኝ አይባልም በፍርድ አይከሰስ ።
መፅሐፍ አዋቂ የህግ መምህር
ተምሮ ያደገ ከጎቶልያል ስር
ቢሆንም ሚከበር የካህን አለቃ
አልሻውም ቃሉን ተፈፀመ በቃ!!!!!


በነቢዩም ከጌታ ዘንድ ፦
"እነሆ ድንግል ትፀንሳለች ፣ወንድ ልጅም ትወልዳለች ፤ስሙንም አማኑኤል ይሉታል" የተባለው ይፈፀም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኗል ።ትርጓሜውም እግዚያብሄር ከእኛ ጋር የሚል ነው "
ማቲ1:21

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH

የመወያያ ግሩፕ @marantawoch
498 views23:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-05 09:24:35 (1) .#ኢየሱስ_የተወለደው_ታኅሣሥ_29_ነው?

እምነት፦ ኢየሱስ የተወለደው ታኅሣሥ 29 (ታኅሣሥ 25 እ.ኤ.አ) እንደሆነ የሚታመን ሲሆን ልደቱ በዚህ ዕለት ይከበራል። የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል ያዘጋጀው የአማርኛ መዝገበ ቃላት፣ ገና “በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ታህሳስ 29 . . . የሚከበር ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደበት ቀን” እንደሆነ ይገልጻል።

ምንጩ፦ ዘ ክሪስማስ ኢንሳይክሎፒዲያ እንደገለጸው “[ገና] ታኅሣሥ 25 ላይ መከበር የጀመረው መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት በማድረግ ሳይሆን . . . በዓመት መጨረሻ ላይ ይከበሩ የነበሩ የሮማውያን አረማዊ በዓላትን በመከተል ነው”፤ በሰሜናዊ ንፍቀ ክበብ ይህ ጊዜ የሚውለው ቀኖቹ አጭር በሚሆኑበት ወቅት አካባቢ ነው። እነዚህ በዓላት የእርሻ አምላክ የሆነው #ሳተርን የሚከበርበትን የሳተርናሊያ በዓል “እንዲሁም ሁለት የፀሐይ አማልክት ይኸውም የሮማውያኑ #ሶል እና የፋርሳውያኑ #ሚትራ የሚከበሩባቸውን ጥምር በዓላት ያካትታሉ” ይላል ይኸው ኢንሳይክሎፒዲያ።
የእነዚህ አማልክት የልደት በዓላት የሚከበሩት በጁልያን የዘመን አቆጣጠር መሠረት ቀኑ በጣም አጭር በሆነበት ዕለት ይኸውም በታኅሣሥ 25 ነበር።

የእነዚህ የአረማውያን በዓላት “ክርስቲያናዊ” መልክና በዓላት የሆኑት በ350 ዓ.ም. ሲሆን በዚህ ወቅት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጁልየስ ቀዳማዊ፣ ታኅሣሥ 25 የክርስቶስ የልደት ቀን መሆኑን አውጀው ነበር። ኢንሳይክሎፒዲያ ኦቭ ሪልጅን እንዲህ ብሏል፦ “ቀኖቹ አጭር በሚሆኑበት ጊዜ አካባቢ የሚከበሩት በዓላት በሙሉ ቀስ በቀስ በልደት [በገና] በዓል ተተኩ። ከሞት የተነሳውን ክርስቶስን (ሶል ኢንቪክቱስ ተብሎም ይጠራል) ለማመልከት በፀሐይ ምስል መጠቀም እየተለመደ የመጣ ሲሆን ቀደም ሲል . . . በነገሥታት አናት ላይ ይደረግ የነበረው የፀሐይ ምልክት በክርስትና ቅዱሳን አናት ላይ በሚደረገው አክሊለ ብርሃን ተተካ።”

#መጽሐፍ_ቅዱስ_ምን_ይላል? 

መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ የተወለደበትን ቀን አይናገርም። ያም ቢሆን ኢየሱስ ታኅሣሥ 29 (ታኅሣሥ 25 እ.ኤ.አ) እንዳልተወለደ በእርግጠኝነት መናገር እንችላለን።
እንዲህ የምንለው ለምንድን ነው?
ኢየሱስ በተወለደበት ወቅት እረኞች በቤተልሔም አቅራቢያ “ሌሊት ሜዳ ላይ መንጎቻቸውንሲጠብቁ” እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። (ሉቃስ 2:8) ቀዝቃዛ የሆነው የዝናብ ወቅት አብዛኛውን ጊዜ የሚጀምረው በጥቅምት ወር ነው፤ በዚህ ጊዜ በተለይ እንደ ቤተልሔም ባሉት ደጋማ አካባቢዎች የሚኖሩ እረኞች በጎቻቸውን የሚያሳድሩት መጠለያ ባለው ቦታ ነበር። በጣም ቀዝቃዛ የሆነው ወር ታኅሣሥ ሲሆን በዚህ ወቅት አንዳንድ ጊዜ በረዶ ይጥላል።

የጥንቶቹ ክርስቲያኖች (ብዙዎቹ ኢየሱስ አገልግሎቱን ሲያከናውን አብረውት ነበሩ) በየትኛውም ቀን ቢሆን የኢየሱስን ልደት አክብረው የማያውቁ መሆኑ ልብ ሊባል የሚገባው ነው።
እነዚህ ክርስቲያኖች ኢየሱስ ባዘዛቸው መሠረት ያከበሩት ሞቱን ብቻ ነበር። (ሉቃስ 22:17-20፤1 ቆሮንቶስ 11:23-26)
እንዲያም ሆኖ አንዳንዶች ‘ገና ከአረማውያን በዓል የተወረሰ መሆኑ ለውጥ ያመጣል? ይሉ ይሆናል። አዎን፣ የአምላክ ለውጥ ያመጣል።
ኢየሱስ ክርስቶስ “እውነተኛ አምላኪዎች አብን በመንፈስና በእውነት [እንደሚያመልኩት]” ተናግሯል።—ዮሐንስ 4:23

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
428 views06:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-02 03:35:32 እንዳትሸወዱ

ለአርሴናል ለቸልሲ ማድሪድ ባርሴሎና
ተመድቦ ጊዜዉ በከንቱ ያልቅና
ጓደኛን ለመምሰል ስትል ቀና ቀና
አስተዉል ወንድሜ እረጋ በልና
ያለጊዜዉ ደስታ እንዳለዉ ፈተና፡፡

ፊልም አለ ፊልም እንይ
ኳስ አለ ኳስ እንሂድ
'አቦ ዘነጥ' ነዉ ፈታበል በአሪፍ 'ሙድ'
ክፉ ባለእንጀራ ሲያስለዉጥህ መንገድ
አደራ እንዳልተባልክ በወላጅ በዘመድ
ወንድሜ ተጠንቀቅ ከቶ እንዳትሸወድ፡፡

ቢጨርሱ ስራ ቢጨርሱ ጥናት
ለየዋሁ አበሻ ኳስን ፈጠሩለት
እንዲከተላቸዉ ሁሉን ነገር ትቶት
ወዳጄ አይምሰልሀ መገለጫዉ የእዉቀት
አርቆ የማሰብ የዘመናዊነት
የራስን ወርዉሮ መምሰል 'ፈረንጂነት'፡፡

ለሁሉም ጊዜ አለዉ ጊዜ ለኩሉ
አምላክም እንዳለዉ በማይሻር ቃሉ
በነፈሰዉ ሁሉ ስትሄዱ ስትነጉዱ
አደራ ወንድሞች፤ አደራ እህቶቼ እንዳትሸወዱ፡፡
Br Tekle T.

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
429 views00:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ