Get Mystery Box with random crypto!

የፍቅር ለዛ (YEFKIR LEZA)

የቴሌግራም ቻናል አርማ yefkir_leza — የፍቅር ለዛ (YEFKIR LEZA)
የቴሌግራም ቻናል አርማ yefkir_leza — የፍቅር ለዛ (YEFKIR LEZA)
የሰርጥ አድራሻ: @yefkir_leza
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 732
የሰርጥ መግለጫ

አሪፍ ,ውብ እና መሳጭ የሆኑ ታሪኮችን አና ግጥሞችን ታገኛላችሁ።
For any comment @ABDU_EMRE

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-04 21:45:09 #ሀያትና_የአይን_ፍቅር
#ክፍል_ሰባት

አብዱ ኤምሬ

እናቴ በደስታ ስሜት ሆና መናገር ጀመረች "የእኔ እና የአባታችሁ አባቶች በጣም የቅርብ ጓደኛሞች ነበሩ እና ይሄን ቅርበታቸውን ወደ ዝምድና ለማሳደግ ሲሉ የአባትሽ አባት እና አባቴ እኛን ለመዳር ወሰኑ ያኔ የአስራ ሰባት አመት ልጅ ነበርኩ እኔ ትዳሩን ባልፈልገውም አባቴ በግድ ዳረኝ በእርግጥ እንቢ የማለቱም ድፍረት አልነበረኝም በጊዜው ማህበረሰባችን ሴት ልጅ እንድትማር የሚፈቅድ ስላልነበር የመማር እድሉን አላገኘሁም እና ቤተሰቦቼ ሀገር ምድሩ በተገኘበት በወግ ማዕረግ ዳሩኝ" አባቴ በመሀል ምን ማለትሽ ነው ቤተሰቦቼ ብቻ ስትይ የእኔስ ቤተሰቦች አብረው አይደለም እንዴ የደገሱት አላ ቆጣ ብሎ ...

"አዎ በቃ ልክነህ ተሳስቼ ነው አሁን አታስቁመኝ ልናገርበት" ብላ ታሪኩን ቀጠለች <የአባታችሁ ቤተሰቦች እና የእኔ ቤተሰቦች ገጠር ውስጥ ጉራጌ ሀገር ይገኙ ስለነበር ከሰርጉ 3ቀን ቡሀላ ወደ እዛው አቀናን መጀመሪያ ወደ እኔ ቤተሰቦች አጎቶቼ እና አክስቶቼ ጋር ጌቶ ውስጥ ስኩት የሚባል አከባቢ ሄድን ባልጠበቅነው መልክ የአከባቢ ሰዎች በጉራግኛ ጭፈራ እና በእልልታ ተቀበሉን መጀመሪያ አጎቴ ቶፊቅ ቤት ነበር የሄድነው እዛ ስንገባ አንድ ጠቦት ታረደና የአከባቢው ሰው እንግዳ ተቀበይ በመሆኑ ምሽቱን በጭፈራ እና በደስታ አሳለፍነው በቀጣዩ ቀን ደግሞ ሌላኛው አጎቴ ሱልጣን የአባቴ ወንድም ጋር ሄድን ተው አይሆንም ብንልም እዛም አንድ በግ ታረደ እና አሁንም የጉራጌን ህዝብ እንግዳ ተቀበይነት በሚገልፅ መልኩ በሁለታኛውም ቀን በጭፈራ በደስታ አደርን በሶስተኛው ቀን ወደ አባትሽ ቤተሰቦች ጋር ልንሄድ ብንፈልግም የአባቴ እህት አክስቴ የኔ የሴት ቤት ስለሆነ ነው እንዴ ጥላችሁ ምትሄዱት ብላ በግድ ካላደራችሁ ብላ ጠቦት አረደች እና ሶስተኛውንም ቀን የአከባቢው ሰው የአቅሙን ያህል እያመጣ በሚያስደስት መልኩ አሳየን የዛኑ ቀንም በጭፈራ ካደርን ቡሀላ በጠዋት ተነስተን ቤተሰቦቼን እና የአከባቢውን ሰው ከተሰናበትን ቡሀላ ወደ አባታችሁ ቤተሰቦች ሄድን...

ገጠር ውስጥ መኪና ስለሌለ በፈረስ ነበር የሄድነው እናም ከቀኑ ስድስት ሰአት ቡሀላ እነሞር ማፌድ አከባቢ ደረስን አሁንም የአባትሽ ቤተሰቦች እና የአከባቢው ሰው ወጥቶ በጭፈራ እና በእልልታ ተቀበልን የአባታችሁ አጎት ቤት አደርን እዛ ከምነግራችሁ በላይ ነበር የተንከባከቡን እናም እዛም በሬ አረዱ እናም የአከባቢው ሴቷች ስጋውን ከትፈው ምሽቱን ጣፋጭ ክትፎ አበሉን እስከዛሬ ክትፎ በበቃኝ በልቼ አላውቅም" አለች እናቴ በረጅሙ እየተነፈሰች "እናም እዛ ለሊቱን ሙሉ ስንጨፍር አደርን ጠዋት ስንነሳ ወላንዷ ተሰርቷ ነበርና እሱን በልተን ወደ አዲስአበባ ልንመለስ ብንፈልግም በግድ ካላደራችሁ ብለው አሳደሩን የበሬው ስጋ እያለ በተጨማሪ በግ ታረደ ስጋ ያስጠላን ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል... እናም በጊዜ ተኛን እና በጠዋት ተነስተን የአባትሽን ቤተሰቦች እና የአከባቢውን ሰው ተሰናብተን ወደ አዲስ አበባ ተመለስን...

"አዲስ አበባ ከመጣን ቡሀላ ምንም እንኳን እኔ ልጅ ብሆንም አባታችሁ በጣም ታጋሽ እና እንክብካቤ የሚያውቅ ሰው ነበር ካሰብኩት በላይ ለኔ ጥሩ ነበር አንዳንዴ ፍቅር በመተዋወቅ ሳይሆን በትዳር ውስጥ እንዳለ አምናለሁ".. አባቴ በእናቴ በመሞገሱ ደስተኛ እንደሆነ ፊቱ ያስታውቃል "ልጅ መውለድ የምፈልግበት ወቅት ባይሆንም በአባታችሁ እና በቤተሰቦቼ ግፊት ምክንያት በአስራ ስምንት አመቴ የመጀመሪያ ልጃችንን ሙሀመድን ወለድኩ። በእርግጥ ለኔ ከባድ ጊዜ ቢሆንም የአባታችሁ ቤተሰቦች ከሚገባው በላይ እንክብካቤ ያደርጉልኝ ነበር ...."

ልነግርሽ ስፈራ ቀን ቀንን ወለደ:
ሳምንቱ ወራቱ ወዲያ ተሰደደ:
ልነግርሽ ያልኩ እለት መውደዴን አውጥቼ
በሰው ተገፍቼ ብታይ ተርበትብቼ
ምንም ሳልናገር ሄዳለሁ ፈርቼ


ልነግርሽ ስፈራ ፅንሰት ተወለደ ሌላ ሽል ተያዘ:
አንደበቴ ታስሮ ባንቺ እንደናወዘ:
ይመስለኛል ሆኗል እልፍ ክስተት:
ሳልነግርሽ መውደዴን መናገር በመፍራት:

ልነግርሽ ስፈራ ዘመን ተለወጠ አዲስ ዘመን መጣ:
አዲስ ጎህ ቀደደ አዲስ ቀንም ወጣ:
እኔ ሳልናገር ቃል ከአፌ ሳይወጣ።

ይቀጥላል.....

@YEFKIR_LEZA
@YEFKIR_LEZA
883 viewsAbdu Emre, edited  18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 21:35:42 #ሀያትና_የአይን_ፍቅር
#ክፍል_ስድስት

አብዱ ኤምሬ


ከመድረሳ ስንወጣ ኢክራም ውጪ ነበረች ሲመስለኝ ሀያትን እየጠበቀች ነበር። አቡኪ "በቃ እሷን እጠይቃታለሁ አንተ እየሄድክ ጠብቀኝ ብሎ ወደ ኢክራም ሄደ። እኔም በቀስታ መራመድ ጀመርኩ የነበረኝ ደስታ ፊቴ ላይ ያስታውቃል....

አምስት ደቂቃ እንኳን ሳይቆይ አቡበከር መጣ ፊቱ ላይ የሚታየው ነገር ግን የተሳካለት አይመስልም ምነው አቡኪ ችግር አለ እንዴ አልኩት? "ኢክራምን የሀያትን ስልክ እንድትሰጠኝ ጠይቄት ነበር ግን ስልክ የላትም አለችኝ ደጋግሜ ብጠይቃትም ስልክ የላትም አለችኝ እኔም ከመጨቅጨቅ ብዬ ትቼት መጣሁ።" አለኝ ፊቴ በአንዴ ሲለዋወጥ ይታወቀኛል የነበረኝ ተስፋ ሁሉ የባከነ መስሎ ታየኝ መከፋቴን ለአቡኪ ማሳወቅ ስላልፈለኩ ችግር የለውም በቃ ቸው ብዬ ሄድኩ ፊቴ ላይ ይታይ የነበረው ደስታ አምስት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ወደ ሀዘን ተቀየረ በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኔ ቤት ደረስኩ ቤት ስገባ የነበረው ደስታ እና ጭፈራ ሁሉ በኔ መሳለቅ መስሎ ታየኝ። ቤት ውስጥ ከማንም ጋር ሳልነጋገር ወደ መኝታ ክፍል ገባሁ ለመተኛ እና ለመርሳት ብሞክርም የባሰ ጭንቀት ውስጥ እና ራሴን መውቀስ ጀመርኩ ለምንድነው ፍቅሬን እንኳን ለመግለፅ ድፍረት ያጣሁት ይሄ ጥያቄ አይምሮዬ ላይ ይመላለስ ጀመር ሳላስበው እንባ ከአይኔ ይፈስ ጀመር ላስቆመው ብሞክርም ይበልጥ ማልቀስ ጀመርኩ...

ማልቀስ አለብኝ እንዴ እራሴን መጠየቅ ጀመርኩ ቢያንስ ለራሷ ነግሬያት የሚመጣውን ነገር እቀበላለሁ ከተኛሁበት ተነስቼ ፊቴን ታጥቤ ወደ ሳሎን ገባሁ የመግሪብ(የፀሀይ መግቢያ) ሰላት ሰግጄ ከቤተሰቤ ጋር ተቀመጥኩ እናቴ ፊቴን እያየች <ቅድም ፊትህ ጥሩ አልነበረም የሆንከው ነገር አለ እንዴ ሰሚሬ> አለች አረ ምንም አልሆንኩም እናቴ ዝም ብለሽ ነው አልኳት። ትንሿ ሰብሩ ቤቱን አድምቃዋለች የሰርግ ነከፍቷ እየጨፈረች ሌሎቻችን እያጨበጨብን ነው...

እማ እናንተ ስትጋቡ እንዴት ነበር አለች? ኑራ በእርግጥ እናቴ እና አባቴ ከዚህ ቀደም ቢያወሩልንም ሁሌም ቢያወሩልን የማንሰለቸው እና ለመስማት የምንጎጎው ነው። "አባትሽን ጠይቂው እሱ ይንገርሽ" አለች እማ ሁላችንም ወደ አባታችን ዞረን ንገራና አባ እንዴት ነበር? አልነው። እሱም እሺ እነግራችሆለሁ ብሎ መናገር ጀመረ "እኛማ ስንጋባ ሁለታችንም አንተዋወቅም ነበር በቤተሰብ ልጅህን ለልጄ ተብሎ ነበር የተጋባነው ሰርጋችን ሀገር ምድሩ በተሰበሰበበት አዲስ አበባ ድልበር አከባቢ ባለው ሸገር መናፈሻ ተደግሷ በዘመኑ እንደኛ አይነት ሰርግ ታይቷም ተሰምቷም አይታወቅም።" አባቴ እያጋነነ አልነበረም እኔም ሰርጋቸው ላይ የተቀረፀውን ቪዲዬ ስላየሁት የደመቀ ሰርግ እንደነበር መመስከር እችላለሁ። እናቴ <እሱ ከላይ ከላይ ነው ያወራው ያ ብቻማ አይደለም እኔ እነግራቹሀለሁ ብላ መናገር ጀመረች.....

እንቡጡ ፈንድቶ አበባው ረገፈ:
ቃሌን ሳላወጋሽ አረ ስንቱ አለፈ:
ዶፍ ዝናብ ወርዶ ጎርፉን አጎረፈ:
ጎልማሳውን ጠርቶት ከአፈሩ አረፈ:
እኔ ሳልናገር ቃሌ እንደ ከሸፈ።

ነጭ ቅኔ ዘረፈ ሸለለ እንደ ሀገሬው:
አምባሰል አንቺሆዬ ባቲንም ዘፈነው:
ማሲንቆ በገና ክራሩን ገረፈው:
ልነግርሽ ስፈራ አረ ስንቱን አየሁ:
እኔ እዛው ቆሜ ልነግርሽ ስፈራ:
ስር ሰድጄ ቀረው እንደ ደጅሽ ወይራ።

ይቀጥላል......

@YEFKIR_LEZA
@YEFKIR_LEZA
738 viewsAbdu Emre, edited  18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 21:57:49 #ሀያትና_የአይን_ፍቅር
#ክፍል_አምስት

አብዱ ኤምሬ


ከፍቅር አይነቶች ሁሉ ከባዱ ፍቅር የአይን ፍቅር ነው ምክንያቱም ለምትወደው ሰው ፍቅርህን ሳትገልፅ በልብ ስለሚያዝ ነው ከሌሎች የፍቅር አይነቶች የሚለየውም ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ቢሄድም አንድ ደረጃ እንኳን ከፍ ማለት አይችልም። የአይን ፍቅር አስደሳች ጣፋጭ የመሆኑን ያህልም ከባድ እና ፈታኝ ነው።

ዛሬ መድረሳ ያስገረመኝ እና ያስደሰተኝ ነገር አቡበከርን ማየቴ ነበር እኛ መድረሳ አይማርም ዛሬ መምጣቱ አስደንቆኛል አጠገቡ ሄጄ ሰላም ካልኩት ቡሀላ "ዛሬ ለምን መጣህ አልኩት " በመገረም ስሜት "ምነው መምጣት አልችልም እንዴ አለኝ?" ፈገግ እያለ "አረ እንደዛ ማለቴ አይደለም መምጣትህ ገርሞኝ ነው "የመጣሁትማ ከሀያት ስልኳን የመቀበል ድፍረት ስሌለህ እኔ ልጠይቅልህ ብዬ ነበር ?" ሲያስጨንቀኝ የነበረው ነገር ስለቀለልኝ ፈገግ ብዬ የምርህን ነው አቡኪ "አዎ ግን ዛሬ መጥቼ ዛሬውኑ ጠይቅ እንዳትለኝ" እና መቼ ልጠይቃት ነው አልኩት ቀዝቀዝ ብዬ "ሀያትን ዛሬ አሳየኝና ነገ እጠይቃታለሁ ዛሬ በዛሬ መጠየቅ ይከብዳል ፍየል ከመድረሷ ቅጠል መበጠሷ ይሆናል" እሺ በቃ ችግር የለውም ስንወጣ አሳይሀለሁ አልኩት...

ከመድረሳ ከወጣን ቡሀላ ሀያት አስክትወጣ ውጪ ቆመን መጠበቅ ጀመርን ብዙም ሳይቆይ ሀያትና ኢክራም አብረው ወጡ ሀያት ጥቁር ሂጃብ አድርጋ ስለነበር በሂጃቧ ምልክት አድርጌ አሳየሁት በቃ እሺ ነገ እጠይቃታለሁ የእሱ ቤት ከመድረሳው በታች ስለሆነ በቃ ልሂድ ብሎ ሰላም ከተባባልን ቡሀላ ወደ ቤቱ ሄደ እኔም በደስታ ሰሜት እንዳለሁ ወደ ቤቴ ተመለስኩ...

ቤታችን እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ በሰርግ ዝግጅት እና ነሺዳ ደምቋል ሰርጉ የቀረው ሁለት ሳምንት ብቻ ነው ቤተሰብ አዝማድ ሁሉ ለሰርጉ በስልክ ጥሪ እየተደረገላቸው ነው። ምሽቱን ሙሉ ከመጠን በላይ ደስታ ውስጥ ነኝ ስልኳን ሳላገኝ እንደዚህ የሆንኩ ስልኳን ባገኝ ደግሞ እንዴት ልሆን እንደምችል አላውቅም? ለሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ልተኛ አልቻልኩም እስኪነጋ እና ስልኳን እስካገኝ ቸኩያለሁ ገና ከአሁኑ ለሊቱን ሙሉ የማስበው ከሀዩ ጋር ወደፊት ስለሚኖረኝ የደስታና የፍቅር ህይወት ነው።

ጠዋት ጣፋጩን የእናቴን ፍርፍር ከበላሁ ቡሀላ ወደ ት/ቤት ሄድኩ ቀን ሙሉ ከአቡኪ ጋር ደስ የሚሉ ጊዜያትን እያሳለፍኩ ነው ከአቡኪ ጋር እንደ ዛሬ ከተጫወትን እና ካወራን አመታት ተቆጥረዋል ደስታዬን የነጠቀኝ የሀዩ ፍቅር ሆኖ ኗሯል ምንም ጥሩ ጊዜ እያሳለፍኩ ቢሆንም ቀን ሙሉ የመድረሳ ሰአት እስኪደርስ መጠበቅ አቅቷኛል...

ከት/ቤት ከተመለስኩ ቡሀላ ቤት ውስጥ ትንሽ ካረፍኩ ቡሀላ በጥድፊያ እና በደስታ ስሜት ውስጥ ሆኜ ወደ መድረሳ ሄድኩ መድረሳ ስገባ ዛሬም አቡኪ ቀድሞኝ መጥቶ ነበር ከአቡኪ ጋር ሰላም ከተባባለን ቡሀላ የእለቱን ደርስ ተከታትለን ከጨረስን ቡሀላ ከመድረሳ ወጣን...

ልነግርሽ ስፈራ ዳዴ ሚለው ተራመደ ኮልታፋው አወራ:
ገበሬው አረሰ ምርጥ ዘሩን ዘራ:
ወላጅ ልጁን ዳረ ቀለጠ ጭፈራ:
ለጋ እድሜ ተጉዞ በሰለ ጎመራ:
ከደጃፍሽ ቆሜ ልነግርሽ ስፈራ:

እንቡጡ ፈንድቶ አበባው ረገፈ
ቃሌን ሳላወጋሽ አረ ስንቱ አለፈ:
ዶፍ ዝናብ ወርዶ ጎርፉን አጎረፈ:
ጎልማሳውን ጠርቶት ከአፈሩ አረፈ:
እኔ ሳልናገር ቃሌ እንደ ከሸፈ።

ድንጋይም ፈራርሶ አፈሩን መሰለ:
የሞላው ጎተራ ለማለቅ ጎደለ:
ልቤ ድፍረት አጥቶ ፈራ ተባ እያለ።

ይቀጥላል...

@YEFKIR_LEZA
@YEFKIR_LEZA
774 viewsAbdu Emre, edited  18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 21:51:18 #ሀያትና_የአይን_ፍቅር
#ክፍል_አራት

አብዱ ኤምሬ


አባቴ ከሽምግልናው ከመጣ ቡሀላ የነበራቸውን ውሎ ሁሉንም ነገር ከነገረን ቡሀላ ሰርጉ ከሶስት ሳምንት ቡሀላ በጋራ እንዲሆን መስማማታቸውን ነገረን ቤታችን ይበልጥ በደስታ ተዋበ ደመቀ በዚህ ሳምንት ያየነው ደስታ ሁሌም እንዲቀጥል ተመኘሁ...

እናቴ ሳምንቱን በሙሉ በሰርጉ ድግስ ጉዳይ ተጠምዳለች እኛም ቢሆን በአዳራሽ ኪራይና በመሳሰሉት የሰርግ ጉዳዮች ተጠምደናል ለሀዩ ዛሬ ነገ እነግራታለሁ እያልኩ ብቆይም ጊዜ እና ድፍረቱን አጥቻለሁ ለሀዩ ካለመናገሬ ይበልጥ እየጎዳኝ ያለው ግን ለማንም አለመናገሬ እና አለማማከሬ ነው ምናልባት አቡኪን ባማክረው ጭንቀቴ ይቀልልኝ ይሆናል ነገር ግን አቡኪ ጥሩ የሆነ ራሴን የማረጋጋበት መፍትሔ ይሰጠኝ እንደሆነ አላውቅም? እነዚህ ጥያቄዎች ቀን ሙሉ ራሴን እያጨናነቁኝ ነው...

ት/ቤት ከሄድኩ ቡሀላ ክፍል ውስጥ ለአቡበከር ላናግረው እንደምፈልግ ነገርኩት አቡኪ "እሺ ምንድነው? ንገረኛ" የምለውን ለመስማት የፈለገ እና የጓጓ ይመስላል አሁን አይደለም ቡሀላ ምሳ ሰአት ላይ እነግርሀለሁ አልኩት በቀዘቀዘ ስሜት...

ምሳ ሰአት ሲደርስ ከአቡኪ ጋር አብረን ከክፍል ወጣን ምሳ ከበላን ቡሀላ የተለመደው ቦታ ተቀምጠን ማውራት ጀመርን በመሀል ቅድም እነግርሀለሁ ያልከኝ ምንድነው? አለኝ ለመስማት እንደፈለገ ከፊቱ ላይ ያስታውቃል እኔም ሁሉንም አንድ በአንድ መናገር ጀመርኩ መድረሳ ውስጥ ሀያት የምትባል ልጅ እንዳለች ካየሆት ሁለት አመታት እንደሆነኝና ካየሆት ጀምሮ የሚሰማኝን ስሜት ከልቤ ልትወጣ እንዳልቻለች ሁሉንም ነገርኩት እና ምን እንዳደርግ ትመክረኛለህ ስል ጥያቄ አስከተልኩ "እንደምትወዳት ነግረሀታል እንዴ አለኝ?" አረ አልነገርኳትም ምን ብዬ እንደምነግራት አላውቅም ፊቷ እንኳን መቆም አልቻልኩም አልኩት አንገቴን አቀርቅሬ "እና በቴሌግራም አታወራትም ስልክ ቁጥሮ አለህ" አለኝ ግራ በመጋባት ስሜት አረ አስቤውም አላውቅም አልኩት በደስታ ስሜት በእርግጥ እስከዛሬ እንዴት ላስበው እንዳልቸልኩ አላውቅም "በቃ በአካል ማውራት ከፈራህ ስልኳን ፈልግና በቴሌግራም አውራት እንደዛ ብታደርግ ጥሩ ይመስለኛል?" እኔም በደስታ ስሜት ውስጥ አቡኪ በጣም ነው ማመሰግነው ጭንቀቴን ነው ያቀለልክልኝ አልኩት በደስታ ስሜት ምንአልባት እስከዛሬ ብነግረወወ ኖሮ ይሄን ያህል ባልተጨነኩ ነበር በሌላ በኩል አቡኪ እንደዚህ ከልቡ ማወያየቱ አስደንቆኛል እንዲህ ሰው ሲያማክር አይቼው አላውቅም አረ አስቤውም አላውቅም ት/ት ከጨረስኩ ወደ ቤት ተመለስኩ...

የመድረሳ ሰአት ሲደርስ ወደ መድረሳ ሄድኩ መንገድ ላይ ግን ስልኳን እንዴት እና ከማን ማግኘት እንደምችል አላውቅም ከእሷ ግን ሊሆን አይችልም በዚህ ሀሳብ ውስጥ ሆኜ መድረሳ ደረስኩ መድረሳ ገና ስገባ ያልጠበቅኩት ሰው ተቀምጦ አየሁ በድንገት የተለያየ ስሜት ተሰማኝ ድንጋጤ ግርምት እና ደስታ የተቀላቀለበት ስሜት።

ይቀጥላል....

@YEFKIR_LEZA
@YEFKIR_LEZA
634 viewsAbdu Emre, edited  18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 21:35:30 #ሀያትና_የአይን_ፍቅር
#ክፍል_ሦስት

አብዱ ኤምሬ

ከቤት ከወጣሁ ቡሀላ ወደ መድረሳ በቀረብኩ ቁጥር ፍርሀቴ እና የልብ ምቴ እየጨመረ ነው አሁንም ቢሆን ግን ልነግራት ቆርጫለሁ... መድረሳ ውስጥ የእለቱን ደርስ (ት/ት) ከጨረስኩ ቡሀላ ከመድረሳ ወጣሁ የመድረሳችን ግቢ በር ላይ ሀዩ ቆማ ጓደኛውን እየጠበቀች ነበር እናም ልክ ሳያት ልቤ በፍርሀት ይመታ ጀመር እንደምንም ወደርሷ ቀርቤ ላወራት እንደምፈልግ ነገርኳት አንገቴን አቀርቅሬ መሬት መሬቱን እያየሁ እሺ እያዳመጥኩህ ነው ተናገር አለቺኝ ፊቷን ወደ ጎን አዙራ እኔም እንደምንም ሀሳቤን ሰብስቤ ሁሉንም ልነግራት "ምን መሰለሽ ሀዩ..." ብዬ ንግግሬን ስጀምር ከአፌ ነጥቃ ሀዩ ነው ያልከው ማነው እንደሱ ብለህ እንድትጠራኝ የፈቀደልህ ስሜ ሀያት ነው እሺ ብሎ አቋረጠችኝ እኔም በድንጋጤ በጣም ይቅርታ ሳላስበው ነው አልኳት እሺ አሁን የምትናገረውን ቶሎ ንገረኝ ጊዜ አትግደልብኝ አለች በመሰላቸት ስሜት እኔም ምን ብዬ እንደምነግራት ቃላት ስመርጥ ስትጣብቃት የነበረችዋ ጓደኛዋ ኢክራም መጣች በቃ ሌላ ቀን ትነግረኛለህ ብላ ጥላኝ ሄደች...

በህይወቴ እንደዚህ ተናድጄ የማውቅ አይመስለኝም በአንድ በኩል ምናለ ከምንተባተብ ቶሎ ነግሬያት በሆነ ሁሉን ነገር ለመናገር እድሉን አግኝቼ ባለመጠቀሜ ራሴን ወቀስኩ የአፍጥር ሰአት እየደረሰ ስለነበር ብዙ ጊዜ ሳልወስድ ወደ ቤቴ ተመለስኩ...

ልነግርሽ ስፈራ ነግቶ መሸ ቀኑ:
ብርሀን ተሸሸገ የሰማይ ክዳኑ:
አእዋፋት ዘመሩ ጎሁም ቀዶ መጣ:
እኔ ሳልናገር አንድም ቃል ሳይወጣ
ጨረቃም ፈንጥቃ ደግማ ተሸሸገች:
ልነግርሽ ስፈራ አለም ብዙ ሄደች።

በጋ መጥቶ ሄደ ክረምቱም ከረመ:
መውደዴን ሳልነግርሽ ልቤ እንደታመመ:
ልነግርሽ ስፈራ ቀን ቀንን ወለደ:
ሳምንቱ ወራቱ ወዲያ ተሰደደ:
ተክሉም አድጎ ደርቆ ከእሳት ተማገደ:
ልነግርሽ ስፈራ ስንቱ ተዋደደ።

ምሽቱን ከቤተሰብ ጋር ቁጭ ብለን እየተጫወትን ነው እኔ ግን ዛሬ እንደሌላ ቀኑ ሳልሆንም በሀሳብ ዝም ብዬ ቁጭ ብያለሁ ሁሉም ምን እንደሆንኩ ቢጠይቁኝም ምንም እንዳልሆንኩ ትንሽ ራስ ምታት እንደያዘኝ ነግሬቸው ጥያቄያቸውን ቀንሰውልኛል በዚ መሀል የቤቱ የመጀመሪያ ልጅ የሆነው ሙሀመድ (ማሜ) አንድ የምነግራችሁ ነገር አለ ብሎ ሲናገር ሁሉም ምን እንደሆነ ለመስማት ዝም አሉ <<ከፈቲሀ ጋር ማለቴ ከሴት ጓደኛዬ ጋር ለመጋባት ወስነናል እና እሁድ ሽምግልና እንድልክ ነግራኛለች እንድትሄዱ ለመጠየቅ ነው።>>

አባዬ እና እማዬ ይሄን ሲሰሙ በጣም ተደሰቱ ይባስ ብሎ ማዘሯ ቤቱን በእልልታ ቀወጠችው ይሄም የምስራች ነው እንጂ ልጄ አየኑን በአይኑ ሊያይ ነው ማሜ ሄዳ እቀፈችው እናቴ እንደዚህ ስትደሰት አይቼ አላውቅም በእርግጥ ሁላችንም ይሄን ስንሰማ በጣም ተደስተናል የሰባት አመቷ ሰብሪና እራሱ የኛን ደስታ አይታ ተደስታለች እኔም ብሆን ሁሉን ነገር ረስቼ በደስታ አለም ውስጥ ነኝ ሁላችንም እየተጫወትን ስላመሸን አርፍደን ተኛን...

ሳምንቱን ሙሉ ቤታችን በሰርግ ነሺዳ ደምቆል ስተኛም ስነሳም ወሬያችን ሁሉ ለቤተሰባችን የመጀመሪያው ስለሆነው ሰርግ ነው። ዛሬ ሽምግልና ሚላክበት ቀን ነው አባቴ እና አጎቶቼ ልጅህን ለልጄ ብለው ለመጠየቅ ከሰአት ላይ ወደ ፈቲሀ ቤተሰቦች ቤት ሄደዋል። ሁላችንም የፈቲሀ ቤተሰቦች የሚሰጡትን መል ስለመስማት እየጠበቅን ነው 9 ሰአት አከባቢ ላይ የእናቴ ስልክ ጠራ ስልኩ ቲቪ ስታንዱ ላይ ስለነበር ለማንሳት ብነሳም ሰብሪና ቀድመኝ ሄዳ አነሳችው አባቴ ነበር <ሄሎ አባ> አለች ስልኩን ለእናትሽ ስጪ ስላላት ለእናቴ ሰጠቻት የእናቴን መልስ ለመስማት ሁላችንም እየጠበቅን ነው እማዬ እልል ብላ ቤቱን ቀወጠችው እኛም አብረን ቤቱን በጩኽት አቀለጥነው በእርግጥ ለምን እንደጮህኩ ባላውቅም እናቴ መልካም ነገር ሰምታ እንደሆነ ግልፅ ነው እናቴ ስልኩን ከዘጋችው ቡሀላ ሁላችንም እ እማ ጥያቄውን ተቀበሉ እንዴ አልናት አዎ አለች እማ ፍልቅልቅ እያለች ሁላችንም በድጋሜ በደስታ ጮህን የወንድም ደስታ ይሄን ያህል እንደሚያስደስት አላውቅም ነበር...

ቤተሰቦቼ እንደዚህ ሲደሰቱ አይቼ አላውቅም እኔም ብሆን በዚህ ሳምንት ከመጠን በላይ ደስታ ውስጥ ነኝ እኔም ከሀዩ ጋር ወደፊት ጥሩ የሆነ የፍቅር እና የደስታ ጊዜዎች እንዲኖሩኝ እመኛለሁ.....

ይቀጥላል....

@YEFKIR_LEZA
@YEFKIR_LEZA
634 viewsAbdu Emre, edited  18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 20:51:04 #ሀያትና_የአይን_ፍቅር
#ክፍል_ሁለት

አብዱ ኤምሬ

ከአቡኪ ጋር ቅዳሜና እሁድ ስላልተገናኘን በመነፋፈቅ ስሜት በደንብ ሰላም ከተባበልን ቡሀላ ወደ ት/ቤት ገባን አሁን ላይ የ11ኛ ክፍል ሶሻል ተማሪ ነኝ እኛ ት/ቤት ባንዲራ መስቀልና ሰልፍ መሰለፍ ስለሌለ በቀጥታ ወደ ክፍላችን ገባን ክፍል ውስጥ ከአቡኪ ጋር አንድ ላይ ነው የምንቀመጠው ነገር ግን እሱ አንድ ቦታ ላይ መቀመጥ ስለማይችል የተለያየ ቦታ ነው ሚቀመጠው። እኔ በባህሪዬ ዝምተኛ እና ከሌሎች ጋር ቶሎ ለመግባባት ጊዜ ይወስድብኛል በትምህርቴ ግን ትጉህ ከሚባሉት ተማሪዎች አንዱ ነኝ...

ምሳ ሰአት ላይ ሁሌ አብረን ነው የምንበላው ሰኞና ሀሙስ ሲቀር እና ምሳ እንብላ ብሎ ቢጠይቀኝም አውቆ የጠየቀኝ ስለመሰለኝ ተኮሳትሬ ጠግቤለሁ ለራስህ ብላ አልኩት። የተናደድኩበት ስለመሰለው ካልበላህ ብሎ ሲጨቀጭቀኝ በንዴት ፆመኛ መሆኔን ራስተህ ነው ራስህ ብላ ብዬ ጮህኩበት በእርግጥ ይሄ የመጀመሪያው አይደለም በጣም ይቅርታ ሰሚሬ ረስቸው ነው በቃ እኔ በልቼ ልምጣ የተለመደው ቦታ ጠብቀኝ ብሎ ሄደ እኔም ቁጭ ብዬ ብጠብቀውም አልመጣም ለምን እንቀረ ግን ገብቶኛል ምክንያቱም ከአንዷ ጋር እያወራ ነው ሚሆነው ምን እንደሆነ ባላውቅመም ብዙ ሴቶች ቢወዱትም እሱ ግን የትኛዋንም ሴት ወዶ አያውቅም ከአንዷ ጋርም ከሳምንት እና ከአስራ አምስት ቀን በላይ በፍቅር አይቆይም እና ምሳ ሰአት አልቆ ክፍል ከገባን ቡሀላም ክፍል ውስጥ አልነበረም አብዛኛው ጊዜ ከሰአት ቡሀላ ያሉትን ክፍለ ጊዜዎች መማር አይወድም ...

ከት/ቤት ከተለቀቅን ቡሀላ እንደተለመደው ብቻዬን ተመለስኩ ቤት ውስጥ ትንሽ ካረፍኩ ቡሀላ የመድረሳ(የቁርዐን ት/ቤት) ሰአት ስለደረሰ በጣም ደስ ብሎኛል ሁሌም በናፍቆት እና በጉጉት የምጠብቀው ሰአት ነው እንደዚህ የተደሰትኩበት ምክንያትም ሀያት ነች ሀዩን ከመድረሳ ውጭ የማይበት እድል ስለሌለኝ ነው..

ሀያት የእኛ መድረሳ ከገባች ሁለት አመት ሞልቷታል ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሆትም የመጣች ቀን ከመድረሳ ግቢ ውጭ ነበር ከዛ ቀን በፊትም ቡሀላም ልቤን እንደዛ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም ስተኛም: ተቀምጬም: ት/ቤትም ሁሉም ቦታ የማስበው ስለሷ ብቸሰ ነው። ያለኝን ፍቅር በተደጋጋሚ ልነግራት ብፈልግም እንዴት መናገር እንዳለብኝ አላውቅም እንደ ድሮ ፍቅር በደብዳቤ ልገልፅላት ብሞክርም እሷን እና ፍቅሬን ለመግለፅ ቃላት ያንሱብኝ እና ሳልጀምር አቆማለሁ ብዙ ጊዜ በአካል ልነግራት ብሞክርም እሷን ሳያት አይደለም የልቤን ልናገር ከፊቷ መቆምና ቃላትን ማውጣት የተራራ ያህል ይከብዱኛል።

<< አንቺ ማለት ለኔ ቃላቶች ያጥሩኛል
በቃ ምን ልበልሽ አንቺ እኮ ለኔ
እንዲያው እንዴት ልግለፅ በሰሙ በቅኔ
የሌለሽ እስኪመስል በአካል በእውኔ
ደርሶ ይጠፋኛል ልነግርሽ በወኔ

የአይኔ ብርሀን የፍቅሬ መስታወት የሰማይ ዳርዳርታ
የህብራተ ከዋክብት የፀሀይ መኝታ
የጨረቃ ድምቀት ሲመሽ ወደማታ
ለቀስተ ደመና የነጠፍሽ ምንጣፍ
ወለባ ሠኪ ነሽ ወይስ ምርግ አጥናፍ?

በኔ ጠባብ አለም በዚህ ጭንቅላቴ
እንዲህ ነሽ አይልም ልጉም አንደበቴ።

ማነሽ አንቺ ለኔ?
ምንድኑ ነሽ ለአይኔ?>>

ዛሬ ግን ለሁለት አመታት እንቅልፍ ያጣሁበትን በሀሳብ የሰመጥኩበት በምኞት እና በተስፋ የጠበቅኩትን ፍቅሬን ለመግለፅ ወስኛለሁ ሁሉንም ነግሬት የምትሰጠኝ መልስ ምን ሊሆን እንደሚችል እያሰብኩ ከቤት ወጣሁ...

ይቀጥላል....

@YEFKIR_LEZA
@YEFKIR_LEZA
531 viewsAbdu Emre, edited  17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 00:24:50
ሀያት እና የአይን ፍቅር የሚለው ትረካ ይቀጥል?
Anonymous Poll
86%
አዎ!
14%
አይ!
50 voters396 viewsAbdu Emre, 21:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:15:16 #ሀያትና_የአይን_ፍቅር
#ክፍል_አንድ

አብዱ ኤምሬ

ዛሬ ከሀያት ጋር አንድ ላይ የምንተሳሰርበት የብዙ ጊዚያት ምኞቴ እና ጉጉቴ የሆነው የሰርጋችን ቀን ነው አዳራሹ በታዳሚዎች ተጨናንቆል የእኛን መግባት ሲጠብቁ የነበሩ የሰርጉ ታዳሚዎች በሙሉ የእኛን ወደ አዳራሽ መግባት ሲያዩ አዳራሹን በእልልታ እና በፉጨት አደመቁት ልቤ እንደ ዛሬ በሁለት ስሜት መሀል ሆኖ አያውቅም በጣም ከመፍራቴ የተነሳ ፊቴ ላይ የሚታየው ላብ ባልዲ ይሞላል በሌላ በኩል ደግሞ ከሀዩ ጋር በዚህ አይነት መልኩ በመዳሬ እና አብሮ የመኖር ጅማሬያችን መሆኑን ሳስብ የደስታ እንባ ይተናነቀኛል ዲጄው የነስሩ ከድርን <ባረከሏሁ> የሚለውን የሰርግ ነሸዳ ከፍቶ አዳራሹን አድምቆታል።

እናት እና አባቴ ከሀያት ወላጆች ጋር ከፊት ተቀምጠው ይታዩኛል በአይን ከነሱ ጋር ሰላምታ ከተለዋወጥኩ ቡሀላ ወንድሞቼ እህቶቼ ወደ ተቀመጡበት ቦታ ዞርኩ እነሱ ላይ የሚታየው የደስታ ስሜት ሁሉ ነፍስን ሀሴት ይሞላል። የሚሆነው ነገር ሁሉ እውን አልመስል አለኝ ከሀዩ ጋር ስለሚኖረኝ የወደፊት ጣፋጭ ህይወት እና ልጆች እያሰብኩ... ሀዩን በእጆቼ ይዤ የሙሽራዎቹ ወንበር ላይ ለመቀመጣት ደረጃዎቹን በመውጣት ላይ ሳለሁ ድንገት... የስልኬ አላርም ጠራ.. በድንጋጤ ከመኝታዬ ስነሳ ለካ ያየሁት ነገር ሁሉ የእውነት ሳይሆን በህልሜ ነበር ፊቴ በላብ ተዘፍቋል... ስልኬን አንስቼ ስመለከት የሱቢህ(የንጋት) ሰላት(ስግደት) ሰአት ላይ እንዲቀሰቅሰኝ ብዬ የሞለሁት አላርም ነበር... በህልሜ ያየሁት ነገር በጣም አስደስቶኛል እውን ሆኗ ባየው ብዬ ተመኘሁ....

የሱብሂን ሰላት ከሰገድኩ ቡሀላ በህልም አለም ያየሁት ሁሉ በእውኑ አለም እንዲሆን አብዝቼ አላህን ከተማፀንኩ ከለመንኩ ቡሀላ... ከሱቢህ ቡሀላ የመተኛት ልምዱ ስለሌለኝ ዛሬ የቀኑ መጀመሪያ ስለሆነ ወደ ት/ቤት መሄጃ ሰአቴ እስኪደርስ የተከበረውን ቁርዐን: ወይም ሌሎች መፅሀፍትን አነባለሁ...

ሰኞ እና ሀሙስ ፆመኛ ስለሆንኩ ቁርስ ሳልበላ ነው ምወጣው ዩኒፎርሜን ከለበስኩ እና ቦርሳዬን ከያዝኩ ቡሀላ ከቤት ወጣሁ ሰፈራችን ላይ ከእኔ ጋር አንድ ት/ቤት የሚማር ስለሌለ ብቻዬን ነው የሚሄደው ደግነቱ ት/ቤቱም ከቤታችን ብዙ ስለ ማይርቅ ብቻዬን መሄዱ አይደብረኝም.. የት/ቤቱ ቅጥር ግቢ አከባቢ ስደርስ ሰሚር የሚል ድምፅ ሰማሁ ማንነቱን ለማረጋገጥ ስዞር...

ሰሚር እባላለሁ የምኖረው አዲስ አበባ ከተማ ነው ለቤተሰቤ አራተኛ ልጅ ነኝ ሶስቱ ወንድሞቼ ሙሀመድ:ነቢል:አህመድ ሁለቱ እህቶቼ ደግሞ ኑራ እና ሰብሪና ናቸው። ሙሀመድ የመጀመሪያ ልጅ ሲሆን ተከታዩ ነቢል ቀጥላ ኑራ ከዛ እኔ ቀጥሎ አህመድ የመጨረሻዋ ደግሞ ሰብሪና ነች። አባቴ ነስሩ ከማል እናቴ ደግሞ ሰሚራ ሀሰን ይባላሉ። አጠቃላይ ቤተሰቦቼ ስምንት ነን ይህም በብዙ ፍቅርና እንክብካቤ እንዳድግ ረድቷኛል እናቴ ከሁሉም በላይ ለኔ ፍቅር አላት ሰሚር የሚለውንም ስም ያወጣችልኝ እሷ ነች። እናቴና አባቴ በመሀል ለሶስት አመት ያህል ተለያይተው ስለነበር እናቴ ወላጆቾ ጋር እኛ ሁላችንም ደግሞ ከአባታችን ጋር ነበር የምንኖረው አሁን ላይ ግን አባት እና እናቴ ታርቀው አንድ ላይ መኖር ከጀመርን አምስት አመት ሆኗል...


ሰሚር የሚል ድምፅ ሰምቼ ማንነቱን ለማረጋገጥ ስዞር አቡበከር ነበር። አቡኪ የልጅነት ጓደኛዬ እና አብሮ አደጌ ነው ብዙ ሰዎች ከመመሳሰላችን የተነሳ ከወንድምም አልፎ መንታ ናችሁ የሚል ጥያቄ ይሰነዝራሉ። አሁን ላይ ግን ሰፈራችንን ስለቀየርን ከት/ቤት እና ከመማሪያ ክፍል ውስጥ ውስጥ ሰፈርም ሆነ ሌላ ቦታ የመገናኘት እድሉ የለንም....

ከአቡኪ ጋር ቅዳሜና እሁድ ስላልተገናኝን በመነፋፈቅ ስሜት በደንብ ሰላም ከተባባልን ቡሀላ ወደ ት/ቤት ገባን...

ይቀጥላል.....

@YEFKIR_LEZA
@YEFKIR_LEZA
593 viewsAbdu Emre, edited  18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 23:16:40 አስሊ እና ከረም በቅርቡ

ተርጓሚ: አብዱ ኤምሬ

ከረም እና አስሊ የሚከናወነው በአሲክ ነው። እነዚህ ይዘምራሉ እና በከረም የሙስሊም ፓዲሻህ ልጅ የኢስፋሃን ልጅ እና የአርሜናዊ-ክርስቲያን መነኩሴ ወይም ካህን ሴት ልጅ አስሊ መካከል ያለውን ፍቅር ይናገራሉ። አንዳንድ ጊዜ አባቷ እንደ ገዥው ገንዘብ ያዥ ይገለጻል። ከረም ከአስሊ ጋር በፍቅር ወደቀ። ይሁን እንጂ አባቷ በሃይማኖታዊ ቁርኝቱ ምክንያት ለሠርጉ ፈቃደኛ አልሆነም. አባትየው ፓዲሻህን በመፍራት ሀገር ጥሎ ከልጁ ጋር ሸሸ፣ እና ከረም እሷን ለማግኘት ከጓደኛው ሰፍዋ ጋር ተነሳ። ረጅም የእግር ጉዞ ካደረጉ በኋላ በመጨረሻ አስሊን አገኙ እና በአሌፖ ፓሻ ትዕዛዝ ጥንዶቹ ተጋቡ። በሠርጉ ምሽት መነኩሴው ሴት ልጁን የለበሰው የአስማተኛ ቀሚስ ቁልፎች ሊለቁ አይችሉም. ከረም በጣም ጥልቅ በሆነ ትንፋሽ ይተነፍሳል, በእሳት ውስጥ ይወጣል. አስሊ እሳቱን ለማጥፋት እና ከረምን ለማዳን ብትሞክርም ምንም ውጤት አላስገኘም። አስሊ ለፍቅረኛዋ ስታለቅስ በአመድ ክምር ላይ ስትደገፍ ፀጉሯ በእሳት ይያዛል እሷም ታቃጥላለች።

ኮሆይ፣ ትብሊሲ፣ ጋንጃ እና ዬሬቫን የሚሹትን የከረምስ እና የሶፉስ ጀብዱዎች በዝርዝር በመግለጽ ታሪኩ በብዙ ተለዋጮች ቀርቧል። አሲክ ከረም እንደ ስሙ በካራቫንሰራይስ ወይም በሆቴሎች ግጥሞችን ያነባል።በዚህም የአስሊን ውበት ያጎናጽፋል ይህም እንደ ኔምሩት ተራራ እና ሱፋን ተራራ እና እንደ ሙራት ወንዝ እና ኪዝሪማክ ካሉ ወንዞች ጋር በማጣመር ነው። ከክሬኖች እና ከጋዛል ውበት ጋር ሲነፃፀር። ከሶፉዋ ጋር አብረው ብዙ አደጋዎችን ይጋፈጣሉ።

ታሪኩ ብዙ ጊዜ በተጨባጭ በአጋጣሚዎች እና በተጨባጭ ስሜት የበለፀገ ነው፡ ሁለቱ ፍቅረኛሞች በአንድ ሰዓት ተወልደው አብረው ያደጉ ናቸው። አንዳንድ ጊዜ ድግምት ሁለቱ ዋና ዋና ገፀ-ባህሪያት ሲወለዱ ወይም ሰይዱና ኸድር ከረምን ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ሲታደግ፣ ከረም ግጥም ሲጀምር ወንዞችና ተራራዎች መንገዱን ጠርገው፣ ከረም ደግሞ የኖህ መርከብ ባለበት በጁዲ ተራራ ላይ የራስ ቅሎችን ተናገረ።


በጣም የታወቀው መዝገብ በ 16 ኛው ክፍለ ዘመን መክሙቱ ለጢፍ ሳንዱካቱዝ-ዘሪፍ (የቀልዶች ስብስቦች, የቀጭኔዎች ደረት) ውስጥ ይገኛል. ታሪኩ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ብዙ ጊዜ ታትሟል። አህመድ ፋህሪ በ 1888 በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ በአምስት ስራዎች ተውኔት ጻፈ። በዚያው አመት ሊዮፖልድ ግሩንፌልድ ከረም እና አስሊ ወደ ጀርመንኛ ተረጎመ (ከካባ ዲል በላይፕዚግ 1888 የአናቶሊያን የህዝብ ዘፈኖች)። ከከርም እና ከአስሊ ጋር የተነጋገሩ ሌሎች ምሁራን መህመት ፉአት ኮፕሩሉ፣ ፐርቴቭ ናይሊ ቦራታቭ እና ካሂት ኦዝቴሊ ነበሩ። Üzeyir Hacıbəyov ቁሳቁሱን ወደ ኦፔራ ("Əsli və Kərəm") በ1912 አቀናጅቶ እንደ አህመድ አድናን ሳይጉን ("ከረም") ከብዙ አሥርተ ዓመታት በኋላ። ፎልክ ሙዚቃ የራሱ የሆነ የዘፈን ቅርጽ አለው እሱም "Kerem havaları" ይባላል።

እ.ኤ.አ. በ 1942 አዶልፍ ኮርነር እና 1971 ኦርሃን ኤልማስ ጽሑፉን ቀረጹ። እ.ኤ.አ. በ 2002 ፣ “አስሊ ኢሌ ከረም” የተሰኘ ተከታታይ የቴሌቪዥን ጣቢያ እንደ ወቅታዊ ዝግጅት ተጀመረ ።
አስሊ እና ከረም በቅርብ ቀን...

@YEFKIR_LEZA
@YEFKIR_LEZA
1.2K viewsAbdu Emre, edited  20:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 00:35:58
#አስሊ_እና_ከረም :
ውብ የቱርኮች ልቦለድ እና ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ....
ተርጎሚ: አብዱ ኤምሬ
በቅርብ ቀን.. coming soon..

@abdsebru
@abdsebru
1.3K viewsAbdu Emre, edited  21:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ