የዘመኔ በረከቶች
(አልታየህ ኪዳኔ)
* አዳምን አነብበዋለሁ። ለተውህቦው ፣ ለቋንቋው ጉልበትና ርቅቀት ፣ ረቂቅ ስሜቶችን የሚገልፅበት መንገድ ይገርመኛል። ኢትዮጰያዊ ፍልስፍናን ከእንጀራ እየቀዳ ያለው አዳም የተለየ ከያኒ ነው።
* ሌሊሳን አነብበዋለሁ። ለሃሳቡ ጥልቀት። ነገሮችን የሚያይበት መንገድ ግሩም ነው። አጫጭር ታሪኮቹና ፍልስፍናዊ ወጎቹ የሚጠገቡ አይደሉም። ጥበብ ላይ ያለው መብሰልሰል ደግሞ የተለየ ነው።
* አለማየሁ ገላጋይን አነብበዋለሁ። ለማህበረሰብ ያለውን ተቆርቋሪነት ይገርመኛል። ቁጣው ያስቆጣኛል። ቁርፊያው ያስኮርፈኛል። አንደበቱ ይበረታብኛል። ድንቅ ብዕረኛና አንደበተርቱዕ ነው።
* በእውቀቱን አነብበዋለሁ። ለታሪክ አዋቂነቱ። ማህበራዊ ሂሶችን በቀልድ አዋዝቶ የሚያቀርብበት መንገድ ይማርከኛል። ግጥሞቹን ሳነብብ ደግሞ ቃላትን በማዘዝ አቅሙ እደነቃለሁ።
* እንዳለንጌታን አነብበዋለሁ። አጫጭር ታሪኮች መፃፍ ላይ የተለየ አቅምና ጉልበት ያለው ይመስለኛል። ያነበብኳቸው የእንዳለ አጫጭር ታሪኮች ምርጥ አጫጭር ታሪኮች ተርታ የማሰልፈው ነው።
* ዘነበን አነብበዋለሁ። Disciplined የሆነ የስነፅሁፍ ማንነቱ ይማርከኛል። የሚፅፋቸው መፅሀፎች የብዙ ጥረትና ድካም ውጤቶች ናቸው። ስነፅሁፋዊ ኮስታራነቱን አደንቃለሁ።
@yebirhan_fiker
@yebirhan_fiker