#ስም_ብቻ_ምን_ሊጠቅመኝ መጠሪያ ብቻ ከሆነኝ -- እኔ ክርስቲያን መባሌ በግብሬ ካላሳየሁት -- ካልተዋሐደ ከአካሌ በጨለማ መቅረዝ ሆናኝ-- እግሬን ከእንቅፋት ካላዳነ ጌታዬ በኔ ካልከበረ -- ስሙ በኔ ካልገነነ ሻማ ሆኜ ካላበራሁ -- ጨለማ ለዋጠው ወገኔ ስሙ ብቻ ምን ሊጠቅመኝ -- ምን ሊሠራልኝ ነው ለኔ? በአርባ ቀኔ ስጠመቅ -- ክርስቲያን ተብዬ ልጠራ በእምነት ዳብሬ እንዳድግ -- መልካም ፍሬን እንዳፈራ ሥነምግባር መጠመቄን-- እንዲያሳየኝ አጉልቶ ክርስትናዬን እንዲናገር -- በደረስኩበት ሁሉ ገበቶ የተቀበልኩት ልጅነት -- በእኔነቴ ዙርያ አብርቶ ለዚህ ነበረ ምክንያቱ -- የጥምቀት ክርስቲያን መሆኔ በጸበሉ ነጽቼ -- ልጁ የተባልኩ እኔ በአነጋገር በሥራዬ -- ክርስትናዬን ካላሳየሁ ጌታዬ በሰጠኝ መክሊት -- አትርፌበት ካልተገኘሁ እንደተዘናጋሁ ካለቀ -- ከተጨረሰ ዘመኔ ክርስቲያን መባሌ ምን ሊረባኝ -- ምን ሊጠቅመኝ ነው ለኔ? 101 views20:19