Get Mystery Box with random crypto!

ትዝብተ—ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ (ሁሌም ከሀይማኖት ጎጠኝነት የ | Yasin Muhammed - Official Channel✔

ትዝብተ—ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬
(ሁሌም ከሀይማኖት ጎጠኝነት የማይፀዱ!)
እንደሚታወቀው ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ዛሬ አስመርቋል።
በምረቃ ስርኣቱም ላይ ዩኒቨርሲቲው ለቄስ አቡነ ኤርሚያስ እና ለአትሌት ደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬትንም ሰጥቷል።
||
በነገራችን ላይ እነዚህ ቄስ—አቡነ ኤርሚያስ የወልድያ ከተማ ባለውለታ የሀይማኖት አባት ናቸው። የህወሃት ኃይሎች ከህዝቡ ጋር እሰጣ ገባ ገብተው ለመጨፍጨፍ ሲንቀሳቀሱ የማግባባት ሥራ ሰርተው ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። ዶክትሬቱም ሲያንስባቸው እንጅ አይበዛባቸውም። ይገባቸዋል።

ነገር ግን አብረዋቸው ሲሰሩ የነበሩት ሐጂ ያሲን ኢድሪስ፤ የሙስሊሙ መሪ ለወልድያ ህዝብ እኩል ሲሰሩ የነበሩት ሙስሊም ክሪስቲያን ሳይሉ አብረው የሰሩት ለምን ለእነርሱስ አልተሰጣቸውም

አንዳንድ ግዜ የሚገርመዉ ነገር ሙስሊምን ለምን እደምትጠሉት ሳስበው ይደንቃል
ይህ ክልል ሁሌም ታጥቦ አይጠሬ ናቹህ።
እውነታውን ግን ታሪክ መዝግቦ አስቀምጦላችኋል።
:
ሁሌም ከሀይማኖት ጎጠኝነት የማይፀዱ፣ ታጥበው የማይጠሩ፤ ሁሉን ነገር ራሳቸው ከቆሙበት ሃይማኖት ብቻ እየሰፈሩ የቆሰለ ትርክት ለመፍጠር የማትፈነቅሉት ድንጋይ የለም።

እንደዚያ ባልሆነማ ኖሮ በደግነት መነፀር ከታሰበ በሀጅ ያሲንና በአባ ኤርሚያስ መካከል ልዩነት ባልተፈጠረ ነበር።
የሚሻለው ሁሉንም በልኩ መስፈር ነው።
:
የምንግዜም ኢስላሞፎቢያቸው ስለሚያናድድ እንጅ በመሰረቱ "ስለበጎ ስራ ምንዳ ከላይ ሲሆን ነው ጥሩው፤ የምድር ሰጥቶ መች ያጠግብና"
||
t.me/YasinMuhammed1