➭ በገነት ያሉ ሦስቱ አስደናቂ ነገሮች አንድ አባት ወደ ገነት ከገቡ በኋላ ለሌላ አባት በህልም እንዲህ ሲሉ ነገሩት። ወደ ገነት በገባሁ ጊዜ ሦስት ነገሮች አስደነቁኝ። ➻ የመጀመሪያው ገነት ውስጥ ይገኛሉ ብዬ ፈጽሞ የማልጠብቃቸው በእኔ ዓይን ኃጢአተኞች የሆኑ ሰዎችን በገነት ውስጥ ማግኘቴ ነው። ➼ ሁለተኛው በገነት እንደሚኖሩ በ እርግጠኝነት የምገምታቸውን ጻድቃን መስለው የታዩኝን ሰዎች በገነት ውስጥ አለማግኘቴ ነው። ➼ ከሁሉም በላይ ያስደነቀኝ ግን እንደኔ ዓይነቱን እጅግ ኃጢአተኛ ሰው በገነት ውስጥ ማግኘቴ ነው አለ። ▸ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው "እውነት እላችኋለሁ ቀራጮች እና ጋለሞቶች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በመግባት ይቀድሙአችኋል" ማቴ ፳፩፥፴፩ #ሼር እያረጋቹ @ORTODOX_RINGTONES 161 viewsP R O M O T E R, 19:37