Get Mystery Box with random crypto!

#እግዚአብሔርን_ማወቅ “እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን # | አመልካለሁ /❖ worship...for God /

#እግዚአብሔርን_ማወቅ

“እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን #ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።”
— ዮሐንስ 17፥3

“እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል #እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ።”
— ፊልጵስዩስ 3፥10-11

“የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ቅዱሱንም #ማወቅ ማስተዋል ነው።”
— ምሳሌ 9፥10

“እግዚአብሔርም ሙሴን፦ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ #ታውቁ ዘንድ በግብፃውያን ያደረግሁትን ነገር ያደረግሁባቸውንም ተአምራቴን በልጅህ በልጅ ልጅህም ጆሮች ትነግር ዘንድ፥ ይህችንም ተአምራቴን በመካከላቸው አደረግ ዘንድ የእርሱን የባሪያዎቹንም ልብ አደንድኜአለሁና ወደ ፈርዖን ግባ አለው።”
— ዘጸአት 10፥1-2

“እግዚአብሔርን #ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው፤”
— ሮሜ 1፥28

“አሁንም በፊትህ ሞገስን አግኝቼ እንደ ሆነ፥ #አውቅህ ዘንድ በፊትህም ሞገስን አገኝ ዘንድ መንገድህን እባክህ አሳየኝ፤ ይህም ሕዝብ ሕዝብህ እንደ ሆነ ተመልከት አለው።”
— ዘጸአት 33፥13

“መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች #ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ።”
— ዮሐንስ 10፥14-15

“...ነገር ግን አምላካቸውን #የሚያውቁ ሕዝብ ይበረታሉ፥ ያደርጋሉም።”
— ዳንኤል 11፥32

“የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን #በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።”
— ኤፌሶን 1፥17

“#እንወቅ፤ #እናውቀውም ዘንድ እግዚአብሔርን እንከተል፤ እንደ ወገግታም ተዘጋጅቶ እናገኘዋለን፤ እንደ ዝናብም ምድርንም እንደሚያጠጣ እንደ መጨረሻ ዝናብ ይመጣል።”
— ሆሴዕ 6፥3