Get Mystery Box with random crypto!

Woldia University Muslim Students Union

የቴሌግራም ቻናል አርማ woldiauniversitymuslimstudent — Woldia University Muslim Students Union W
የቴሌግራም ቻናል አርማ woldiauniversitymuslimstudent — Woldia University Muslim Students Union
የሰርጥ አድራሻ: @woldiauniversitymuslimstudent
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 395
የሰርጥ መግለጫ

ብቸኛው የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ አህል አል-ሀዲስ( أهل الحديث والأثار ) ሙስሊም ተማሪዎች ጀምዓ የቴሌግራም ቻናል።

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-08 09:34:35 • - ‏‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌سُئِلَ عُلماءُ اللجنةِ الدائمة للإفتاء:

• - ‏‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌السؤال: السؤال الخامس من الفتوى رقم(6914)

أحيانا يسرع الإمام في القراءة في صلاة التراويح حتى يكاد المصلي خلفه لا يستطيع أن يقرأ أو أن يكمل سورة الفاتحة فما حكم ذلك، وهل الصلاة صحيحة؟


الجواب:

يشرع له أن يلتمس إماما آخر يرتل القراءة ويطمئن في الصلاة، فإن لم يتيسر ذلك صلى التراويح منفردا في بيته، وينبغي لخواص المأمومين أن ينصحوا هذا الإمام حتى يرتل ويطمئن؛ لقول النبي - صلى الله عليه وسلم -: « الدِّينُ النَّصِيحةُ»

وبالله التوفيق وصلى الله على نبينا محمد وآله وصحبه وسلم.

عبد الله بن قعود ... عضو
عبد الله بن غديان ... عضو
عبد الرزاق عفيفي ... نائب الرئيس
عبد العزيز بن عبد الله بن باز ... الرئيس

【 اللَّجْنَةُ الدَّائِمَةُ لِلْبُحُوثِ الْعِلْمِيَّةِ وَالْإِفْتَاءِ (٧ / ١٩٩) 】
═════ ❁✿❁ ══════
347 views06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 09:31:54 السلام عليكم وىحمة الله وبركاته
320 views06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 16:53:14 السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ውድ የ channalu ተከታታዮች ይህ channale ሊዘጋ ስለሆነነ አዲሱን channale በዚህ link ይቀላቀሉ።
https://t.me/wdumuslimstu
422 views13:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 07:22:52 ሪፍቅ (ልስላሴ)
አላህ ለፍጡራኖቹ አዛኝ ነው። ለዚህም ስለሆነ በተውሂድ ያዛቸዋል፣ ሽርክን
እንዲርቁ ያስጠነቅቃቸዋል። በተውሂድ ላይ ኖረው፣ ሽርክን ከነባለቤቶቹ
ርቀው፣ በተውሂድ ላይ ከሞቱ ጀነት የሚባል ልብ ጠርጥሮት፣ ጆሮ ሰምቶት፣
አይን አይቶት የማያውቅ አገር ተዘጋጅቶላቸዋል።
በተገላቢጦሹ አዛኙ አላህ፣ ፍትሃዊ፣ አያያዙ የበረታ፣ አሸናፊ ፈራጅ ነውና በሱ
ላይ የሚያጋሩትን "አጋርያን እርኩሶች (ነጃሳዎች)" ናቸው ሁሉ ብሎ
ጠርቷቸዋል። በዱንያ ውርደትን፣ በአኸይራ አሳማሚ ቅጣትን
አዘጋጅቶላቸዋል። አላህ ይጠብቀን።
ልክ እንደዚሁ ለአማኞች ከነፍሳቸው በላይ የሆኑት ውዱ የአላህ መልክተኛ
(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አዛኝ ናቸው። በጣም አዛኝ ከመሆናቸውም የተነሳ
ሰዎችን ዘላለም አለም እሳት ውስጥ የሚከታቸውን ሽርክ
1) እያዩ እንዳላዩ ዝም አላሉም፣
2) በሽርክና ቢድአ ጉዳይ ላይ አንድ ነን ብለው አልተስማሙም፣
3) ወደ ሽርክና ቢድአ የሚጣራን አይደለም ወደነዚህ መንገድ የሚወስዱን
ነገሮች ዝም አላሉም።
በጣም አዛኙ ነብይ ስለ ቢድአ ሲያስጠነቅቁ ፊታቸው ደም ይለብስ ነበር፣
ይቆጡ ነበር ምክንያቱም ቢድአ ነውና የዚህ ኡማ ትልቁ ፀር።
ስለ ሪፍቅ ሲወራ ባይጠቀስም አብሮት ሺዳ በውስጡ አለ።
እዝነትም (ልስላሲ)፣ ጥንካሪም ቦታ ቦታ አላቸው። መቼም አንድ ዳኢ ሽርክን
ስለሚያክል ታላቅ አደጋ እያስተማረ ለምን ይኮሳተራል? ተብሎ ሊጠየቅ
አይገባውም። ምክንያቱም የነብያትም፣ በተለይ የነብዩ ሰለላሁ አለይሂ
ወሰለምም አካሄድ ይሄ ነበረና።
ቢድአና ወንጀልንም ለያይተን ማስቀመጥ አለብን። የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ
አለይሂ ወሰለም ዘንድ ወንጀለኞች (መጠጥ ጠጪዎች፣ ዝሙት የሰሩ) ሲመጡ
የነበረውን አቀባበል አንርሳ። ልስላሲ ነበር ከመልክተኛው ሰለላሁ አለይሂ
ወሰለም የነበረው። እኚሁ የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ጁምአ
ኹጥባቸው ላይ "አዳዲስ በዲን ላይ ያሉ ፈጠራ ጭማሪዎችን ተጠንቀቁ፣
ሁሉም ፈጠራ ጥመት ነው፣ ሁሉም ጥመት የእሳት ነው" ሲሉ ምን ያህል
ይቆጡ እንደነበር የሀዲስ መዛግብትን ማየት ይበጃል።
አንድ እናት ልጇን ብትገርፍ፣ አንድ አባት ልጁን ቢቆጣ እንዲስተካከልላቸው
እንጂ ጠልተውት አይደለም። ስለሱ የማይጨነቁ ቢሆን ኖሮ ልጃቸውን
ከነመጥፎ ባህሪው ይተውት ነበር።
ልክ እንደዚሁ ሁሉ መጥፎ ነገር ሽርክ፣ ቢድአ፣ መሀይምነት፣ ድራማ፣ ፊልምና
የመሳሰሉት ተስፋፍተው ሲያዩ የአላህ ባርያዎች ስለሚያዝኑ ነው ለኡማው ያ
ሁሉ ውርጅብኝ ከየአቅጣጫው እየወረደባቸው ሀቁን የሚናገሩት። አላህም
ለባሮቹ ስለሚያዝን ነው አዛኝ ከመሆኑም ጋር ማስጠንቀቂያዎችንና ዛቻዎችን
አብሮ ያስቀመጠው። ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምም እንደዚሁ እዝነት
በሚያስፈልገው ቦታ እዝነት፣ ጠንከር ማለት በሚያስፈልገው ቦታ ጠንከር
ብለው ያሳዩን።
አሁን ያለንበት ወቅት ላይ በጣም እዝነት ያስፈልገዋል ይህ የማይካድ እውነታ
ነው። ይህ ማለት ግን ቢድአና ሙብተዲ ላይ አለመናገር ማለት አይደለም።
ቢድአና ሙብተዲ ላይ መናገር ለኡማው በጣም እጅግ በጣም ከማዘን ነው።
ምክንያቱም ኢስላምንና ሙስሊሞችን ከውስጥ የሚንደውና የሚያዳክመው
አዳዲስ መንገዶችና የቢድአ ሰዎች ናቸውና።
አላህ ሁሉንም በቦታው ላይ ከሚያስቀምጡት ባርያዎች ያድርገን። አላህ ሆይ!
እውቀትን ጨምርልን፣ በምናውቀውም የምንሰራ አድርገን፣ በፈተና ወቅትም
በሃቅ ላይ ከሚፀኑት አድርገን።
@wumjbot
418 views04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 00:22:35 The account of the user that owns this channel has been inactive for the last 5 months. If it remains inactive in the next 9 days, that account will self-destruct and this channel may no longer have an owner.
21:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 02:25:21 『ተጠንቀቅ』

ሸይኽ ሙሐመድ ብን ሷሊህ አል‐ዑሰይሚን -ረሂመሁሏህ- እንዲህ ብለዋል:‐

አላህ ባሮች እኔነ ይፈራሉ አይፈሩም የሚለውን ለመሞከር ሀራም ነገሮችን ያመቻቻል፡፡ አላህ በምግብና በመጠጥ ሰዎችን ይፈትናል፡፡ ሀራም እንዲበሉ ሁኔታዎችን ያመቻችላቸዋል ፣ ገር ያደርግላቸዋል፡፡ ይህ ከፈተናዎች መካከል አንዱ ነው፡፡
የሚከተለውን የአላህ ቁርኣን ምሳሌ ማድረግ እንችላለን፡-
﴿يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُواْ لَيَبْلُوَنَّكُمُ اللّهُ بِشَيْءٍ مِّنَ الصَّيْدِ تَنَالُهُ أَيْدِيكُمْ وَرِمَاحُكُمْ لِيَعْلَمَ اللّهُ مَن يَخَافُهُ بِالْغَيْبِ﴾ 
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! (በሐጅ ጊዜ) እጆቻችሁና ጦሮቻችሁ በሚያገኙት ታዳኝ አውሬ አላህ ይሞክራችኋል፡፡ በሩቅ ሆኖ የሚፈራውን ሰው አላህ ሊገልጽ (ይሞክራችኋል)፡፡ (አል‐ማኢዳህ፡ 94)

ይህ አንቀጽ ሀጅን የሀረሙ ሰዎች የዱር አውሬዎችን ማደን እንደተከለከሉ ይገልጻል፡፡
አላህ እንዲህ ብሏል፡-
﴿يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُواْ لاَ تَقْتُلُواْ الصَّيْدَ وَأَنتُمْ حُرُمٌ﴾ 
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እናንተ በሐጅ ስራ ውስጥ ስትሆኑ አውሬን አትግደሉ፡፡” (አል‐ማኢዳህ፡ 95)

አላህ ሶሃቦችን እጆቻቸውና ጦሮቻቸው እንዲደርሱባቸው በማድረግ በሚታደኑ አውሬዎች እንዲፈተኑ አደረገ፡፡ ከመሰረቱ በእግራቸው የሚሮጡ የዱር አውሬዎች በጦር ፤ በራሪ ወፎች ደግሞ በቀስት ካልሆነ መታደን አይችሉም ነበር፡፡ ነገር ግን አላህ ለፈተና ወይም በሩቅ ማን ነው እኔን የሚፈራኝ የሚለውን ግልጽ ለማድረግ በግራቸው የሚሮጡ የዱር አውሬዎችን በቀላሉ በእጆቻቸው እንዲይዟቸው በራሪ ወፎችን ደግሞ በጦር ወርውረው እንዲገድሏቸው ሁኔታዎችን አመቻቸ፡፡ ነገር ግን ሶሃቦች እርሱን በሩቅ የሚፈሩ በመሆናቸው ሁኔታዎች ቢመቻቹም ጥንቸልም ይሁን ወፎችን ሊያድኑ አልቻሉም፡፡ አላህን ፈርተው ነው ማደኑን የተውት፡፡ ስለዚህ ክልክል ነገሮችን ለመስራት አላህ ካመቻቸልህ የአላህን ህግ ከመጣስ ተጠንቀቅ፡፡

@woldiauniversitymuslimstudent
كن على بصيرة
407 views23:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 02:16:58 https://www.facebook.com/538944909813847/videos/1418039828371245/?flite=scwspnss
286 views23:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 10:32:33 1- ክርስቲያን ጎረቤት ቢታመም መጠየቅ ይቻላል?
አዎ ይቻላል። ነብያችን ﷺ የታመመን የሁዲ ጠይቀዋል። [ቡኻሪ፡ 1356]
2- የክርስቲያንን የግብዣ ጥሪ መቀበል ይቻላል?
አዎ ይቻላል። ነብዩን ﷺ አንድ የሁዲ ጠርቷቸው ሄደዋል። [አሕመድ፡ 13201]
3- ክርስቲያን የሆነ ሰው ቤተሰብ ቢሞትበት ለተዕዚያ ወይም ለማፅናናት መሄድ ይቻላል?
አዎ ይቻላል። ከላይ የተጠቀሱት መረጃዎች ለዚህ ድጋፍ መሆን ይችላሉ።
4- ለክርስቲያን ደሃ ሶደቃ መስጠት ይቻላል?
አዎ ይቻላል። [ቡኻሪና ሙስሊም]
5- በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ለክርስቲያን መልካም መዋል ይቻላል?
አዎ ይቻላል። [አልሙምተሒናህ፡ 8-9]
6- ለገና በዓል "እንኳን አደረሳችሁ" ማለት ይቻላል?
በፍፁም!
ከላይ የተዘረዘሩት የሚፈቀዱ ከሆነ ይሄኛው የሚከለክልበት ምክንያት ምንድነው?
የመጀመሪያዎቹ ነገሮች የተፈቀዱት እምነታዊ ሳይሆን ዱንያዊ ጉዳዮች ስለሆኑ ነው። ሃይማኖታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ግን ይሄ የሚፈቀድ አይደለም። በቃልም በተግባርም ማጀብ አይቻልም፡፡ የአላህ ነብይ ዒሳን ጌታ አድርጎ ሲገልፅ፣ ከዚያም "ጌታ ተወለደልኝ" ብሎ ሲደሰት "እንኳን ጌታ ተወለደልህ!" ትላለህ? የእምነታችን አንዱ መሰረትኮ "አላህ አልወለደም፣ አልተወለደም" ነው። በሌሎች ሃይማኖታዊ በአላትም ወይም ድግሶችም ላይ እንዲሁ ነው። እና ወንድሜ! የእምነትህን ህግ ለመጠበቅ ፈፅሞ ወኔ አይጠርህ። ጓደኝነት፣ ትውውቅ ሸብቦህ፣ አጉል እፍረት አስሮህ ከጌታህ ጋር አትጣላ። በነገራችን ላይ ይሄ "የጌታ መውሊድ" ብለው የሚያከብሩት የገና በአል መፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ የማይገኝ በቅድመ-ክርስትና ከነበረው የጣኦታውያን እምነት የተኮረጀ ነው። በዚያ ላይ ዛሬ የጎርጎሮሳዊውን አቆጣጠር የሚከተሉት የሚያከብሩበት December 25ም ሆነ "የኢትዮጵያውን" አቆጣጠር የሚከተሉት የሚያከብሩበት ታህሳስ 29ም በርግጠኝነት ዒሳ (እየሱስ) የተወለዱበት ቀን አይደለም።
-
መነሻ ሃሳቡ ዋትሳፕ ላይ ያገኘሁት 0ረብኛ ፅሁፍ ነው።
==
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
335 views07:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 05:14:53 ለሙስሊሞች ምሕረት መጠየቅ (እስቲግፋር ማድረግ) የዘነጋነው ትልቅ ዒባዳ

አላህ ወንድ አማኝና ሴት አማኞችን በሒይወት ያሉትንም ሆነ የሞቱትን እንዲምራቸው መለመን (ለነርሱ እስቲግፋር ማድረግ) እጅግ ብዙ ምንዳን የሚያስገኝ ትልቅ ዒባዳ ነው።

قال النبي صلى الله عليه وسلم «ﻣﻦ اﺳﺘﻐﻔﺮ ﻟﻠﻤﺆﻣﻨﻴﻦ ﻭاﻟﻤﺆﻣﻨﺎﺕ ﻛﺘﺐ ﻟﻪ ﺑﻜﻞ ﻣﺆﻣﻦ ﻭﻣﺆﻣﻨﺔ ﺣﺴﻨﺔ» حسنه الألباني

ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል:- «ለወንድ እና ለሴት አማኞች ምሕረት የለመነ(እስቲጝፋር ያደረገ) አላህ በሁሉም ወንድ እና ሴት አማኞች ልክ መልካም ምንዳ (ሐሰናት) ይፅፍለታል» [አልባኒ ጃሚዑ ሶሒሕ ላይ (ቁ 6026)ሐሰን ብለውታል]

ሱብሓነላህ የዚህን መልካም ስራ አጅር በደንብ አስተውል አንተ ለሙስሊሞች እስቲግፋር በማድረግህ አላህ በሙስሊሞች ቁጥር ልክ ምንዳ ይሰጥሃል በቁጥር የማይዘለቅ እጅግ በጣም ብዙ ምንዳ ምክኒያቱም የሙስሊሞችን ቁጥር ብዛት አላህ እንጅ ማንም አያውቀውም።
አስብ ከዚህ በስተፊት ስንትና ስንት ሙስሊም ሙቷል? አሁን ዱኒያ ላይ በሒወት ስንት ሙስሊም አለ? ወደፊት ስንት ሙስሊም ይመጣል? ሱብሓነላህ የዚህን ቁጥር አላህ እንጅ ማን ያውቋል? ስለዚህ ወንድሜ እንድህ በሐሳብ የማይዘለቅ እሄ ይሆናል ተብሉ ብዛቱ ሊገመት የማይችል ቁጥሩን አላህ እንጅ ሰው የማያውቀው አጅረ ብዙ የሆነ ዒባዳ መፈፀም ከፈለግክ ለሙስሊሞች ምሕረት ለምን!!

ኢማሙ ሸውካኒ (ረሒመሁሏህ) «ከአላህ ትሩፋትና ሐሰናት ማብዛት የፈለገ ለወንድና ሴት አማኞች ምሕረት ይጠይቅ ምክኒያቱም ለርሱ ገደብ የሌለው አይምሮ ሊቀርፀው የማይችል ምንዳ(ሐሰናት) ይፃፍለታል» ይላሉ [ቱሕፈቱ አዝ–ዛኪሪይን (1/384)]

ምንዳው እንደህ ገደብ የሌለው መሆኑን ካወቅክ እሄን ዱዓ አብዛ ለሙስሊሞች ዘውትር እንድህ በማለት እስቲግፋር አድርግ
{اللهم اغفر للمسلمين والمسلمات والمؤمنين والمؤمنات الأحياء منهم والأموات}
ትርጉም: "አላህ ሆይ ለወንድ እና ሴት ሙስሊሞች ለወንድ እና ሴት አማኞች ምሕረት አድርግ»

ጊዜ የማይፈጅ ጉልበት የማያስፈልገው በቦታና ጊዜ ያልተገደበ ልፋት ድክመት ሳይኖረው በቀላሉ ቁጥር ስፍር የሌለው ምንዳ የሚያስገኝ በጣም ቀላል ዒባዳ!! ወንድም እህቶች እንንቃ የአላህ ፈድል ሰፊ ነው ነፍሳችንን ከመልካም ነገር አንከልክላት በተለይ ደግሞ በዚህ የተከበረ የረመዳን ወር አላህ አንድን ኸይር ስራ እጥፍ ድርብ አድርጎ በሚመነዳበት ወር እንድህ አይነት ቀላልና አጅረ ብዙ የሆነ ዒባዳን በማብዛት ምንዳችን እናብዛ! ወደጌታችን እንቃረብ!

ልብ በል በሙስሊሞች ቁጥር ልክ ሲባል አሁን በሒወት መሬት ላይ ያሉት ማለት አይደለም ((እሄ ብቻ ኘኳ ቢሆን ምንያክል ብዙ እንደሆነ እሰበው)) ግን ሐዲሱ ላይ እንደዚያ የሚል ገደብ የለም ስለዚህ ያለፉት ሙስሊሞች ቁጥር ብዛት በሒወት ያሉትንና ወደፊት የሚመጡትን ብዛት ቆም ብለህ አስተውልና በአላህ ትሩፋት እዝነት ስፋት ተደነቅ!! ሱብሓነሏህ!!
___

ወንድሜ ልብ በል ለዚህም ሲባል ይህ የተባረከ ዱዓ ከነቢያቶች ጥቅል ዱዓ ውስጥ ነበር።
አላህ ስለኑህ እንድህ ብለው ዱዓ ማድረጋቸውን በቁርኣኑ ነግሮናል:-

{رَّبِّ اغْفِرْ لِي وَلِوَالِدَيَّ وَلِمَن دَخَلَ بَيْتِيَ مُؤْمِنًا وَلِلْمُؤْمِنِينَ وَالْمُؤْمِنَاتِ}

«ጌታዬ ሆይ! ለእኔም ለወላጆቼም ምእመን ኾኖ በቤቴ ለገባም ሰው ሁሉ ለምእመናንና ለምእምናትም ምሕረት አድርግ፡፡» (አለ)፡፡ [ኑሕ (28)]

ስለ ነብዩሏህ ኢብራሂምም እንድህ በማለት በተከበረው ቁርኣን ነግሮናል: -
{رَبَّنَا اغْفِرْ لِي وَلِوَالِدَيَّ وَلِلْمُؤْمِنِينَ يَوْمَ يَقُومُ الْحِسَابُ}

«ጌታችን ሆይ! ለእኔም ለወላቼም ለምእመናንም ሁሉ ምርመራ በሚደረግበት ቀን ማር፡፡» [ኢብራሂ (41)]

አላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ የመጨረሻውን ውድና የተከበሩ ነብይ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ለሙእሚኖች ምሕረትን እንዲለምኑ እንዲህ ሲል አዟቸዋል:-

{فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ وَاسْتَغْفِرْ لِذَنبِكَ وَلِلْمُؤْمِنِينَ وَالْمُؤْمِنَاتِ }

እነሆ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንም ዕወቅ፡፡ ስለ ስህተትህም ለምእመናንም ምሕረትን ለምን፡፡ [ሙሐመድ (19)]

ከሱሐቦች በሗላም ስለመጡ አማኝ ባሮቹ ለአማኞች ምሕረትን እንደሚለምኑ እንዲህ ሲል በቁርኣን አውስቱልናል:-

{وَالَّذِينَ جَاءُوا مِن بَعْدِهِمْ يَقُولُونَ رَبَّنَا اغْفِرْ لَنَا وَلِإِخْوَانِنَا الَّذِينَ سَبَقُونَا بِالْإِيمَانِ وَلَا تَجْعَلْ فِي قُلُوبِنَا غِلًّا لِّلَّذِينَ آمَنُوا رَبَّنَا إِنَّكَ رَءُوفٌ رَّحِيمٌ}

እነዚያም ከበኋላቸው የመጡት «ጌታችን ሆይ! ለእኛም ለእነዚያም በእምነት ለቀደሙን ወንድሞቻችን ምሕረት አድርግ፡፡ በልቦቻችንም ውስጥ ለእነዚያ ለአመኑት (ሰዎች) ጥላቻን አታድርግ፡፡ ጌታችን ሆይ! አንተ ርኅሩህ አዛኝ ነህና» ይላሉ፡፡ [ሐሽር (10)]

ይህ ሁሉ መረጃ የሚያመላክተን የዚህን ዱዓ ትልቅነት ነው ስለዚህ በዚህ ዱዓ ላይ ልንዘናጋ አይገባም ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ትልቅ ዱዓና ዒባዳ ነው።

ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይምያህ ረሒመሑላህ እሄን ዱዓ በጣም ትኩረት ይሰጡ ነበር ለዚህም ተማሪያቸው ኢብኑልቀይም ረሒመሁላህ ይህ ዱዓ በፍፁም የማይተውት የእለት ከእለት ውርዳቸው መሆኑንና እንድሁም እሄን ዱዓ በየሶላቱ ሁሉ በሁለቶቹ ሱጁዶች መካከል ሲቀመጥ በዚህ ዱዓ ማድረግ የተፈቀደ መሆኑን ሲናገሩ እንደ ሰሟቸው አስተላልፈዋል።
ምንጭ [ሚፍታሁ ዳሪ ሰዓዳህ (2/298)]

فنسأل الله الكريم المنان أن يغفر لنا ولوالدينا وللمسلمين والمسلمات وللمؤمنين والمؤمنات الأحياء منهم والأموات
@woldiauniversitymuslimstudent

​•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈•
301 views02:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 03:39:55 The account of the user that owns this channel has been inactive for the last 5 months. If it remains inactive in the next 19 days, that account will self-destruct and this channel may no longer have an owner.
00:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ