Get Mystery Box with random crypto!

ውስተ ቀራንዮ ነጽሩ(የምድያም ምድር)

የቴሌግራም ቻናል አርማ weset_keraniyo_netsiru — ውስተ ቀራንዮ ነጽሩ(የምድያም ምድር)
የቴሌግራም ቻናል አርማ weset_keraniyo_netsiru — ውስተ ቀራንዮ ነጽሩ(የምድያም ምድር)
የሰርጥ አድራሻ: @weset_keraniyo_netsiru
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 439
የሰርጥ መግለጫ

እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-28 07:18:11
"ማር" በምድርም "ያም" በሰማይ
.
.
.
ሀዘኔ በርትቶ፣
ስትጨነቅ ነፍሴ፣
ፈገግታዬ ጠፍቶ፣
ሲታወወክ መንፈሴ፣
ወድቄ ከፊትሽ፣
አድኚኝ እላለሁ፣
አልቅሼ ከደጅሽ፣
ከሀዘኔ እወጣለሁ፣
ማንስ ብዬ ልጥራዉ?
እናቴ ስምሽን፣
በምንስ ልግለፀዉ?
ጥዑም መዓዛሽን፣
ማር በምድር፣
ያም በሰማይ፣
የሥላሴን ክብር፣
አጉልታ ምታሳይ፣
እሙ ለፀሐይ ጽድቅ፣
የእግዚአብሔር ከተማ፣
ጥምን የምታርቅ፣
ፍቅር ለተጠማ።

በኤደን ታደሰ እንደተፃፈ
383 views£di_wub, 04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 18:31:36
( ያንተን ሙሴ ስጠን ! )

የንፁኃን ደም ሲጎርፍ ፥ ምድር በደም ታልላ
ዋይታና ጩኸት ሲበረታ ፥ የፈርዖናዊያን ግፍ ፅዋውን ሲሞላ

የራሄል እንባ ፥ ሲፈስስ ...
በልጆቹ ደም ተነክሮ ፥ የእናት አንጀት ሲላወስ
"አምላከ እስራኤል አዶናይ
የለም ወይ በዚህ ሰማይ?"
የሚል የፍጥረት ሲቃ ፥ ምድርን ሲያናውጣት

በመፅሐፍ ያነበብነው ፥ ይሄ የግፍ ጊዜ፥ የሰቆቃ ወራት
በእኛ ለኢትዮጵያውያን ሲደርስ
ፍርድ ሲገመደል ፥ እውነት በግፍ ሲታመስ ...

አገዛዝ ሲፀናብን ፥ የህዝብ ልብ ሲታወክ
ድረስልን ጌታ ፥ ሙሴን ለእኛ ላክ።

እውነት ነው ... !

የሙሴን መገለጥ ስለመራብ ፥ ስለ ፅኑ ናፍቆት ፥ ስለ ሙሴ ስስት
ባንተ ያልተቀባውን ፥ አንተ ያልሾምከውን ፥ ሙሴ ነህ በማለት
የራሳችን ሙሴ ፥ ልናቆም ፥ ቀብተን ልናነግስ
ቃላት በመደረድር ቅኔን ስንቀኝ ርሱን ስናወድስ ፥ ርሱን ስናሞግስ...

ብናሳዝንህም በዚህ ስንፍናችን
ጌታ ይቅር በለን ፥ አሁን ድረስልን
"የእኛን ሙሴ" ወስደህ ፥ "ያንተን ሙሴ" ስጠን።

#መታሰቢያነቱ ፦ ለአራት አመታት በኢትዮጵያ ለዘለቀው የንጹሐን ሰላሚዊ ዜጎች አሰቃቂ ግድያና ሀብት ንብታቸውን ተዘርፈው ለተፈናቀሉ ወገኖቼ ትሁንልኝ !

አቤቱ ክንድህ በክፉዎች ላይ ይጽና፤ በነፈሰ ገዳዮች ላይ የቅጣት ጂራፍህ ይጩህ፤ አቤቱ ግፈኞችን ተበቀል !
189 views£di_wub, 15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 22:14:52
"ኃጢአት ለመሥራት ቀጠሮ ትይዛለህ፤ ጽድቅ ለመሥራት ግን ጊዜ የለኝም ትላለህ፡፡
ጓደኛህን ለማግኘት ጊዜ አለህ፤ ንስሐ አባትህን ለማግኘት ግን ጊዜ የለህም፡፡ በሥጋ ስትራብ ከየትም አምጥተህ (ለምነህም ቢኾን) ትበላለህ፤
ነፍስህ የክርስቶስ ሥጋ ከራባት ግን ዘመናት ተቆጠሩ፡፡ ወዳጄ ሆይ! እባብ አሳተኝ ያለችውንና፥ ከፍርድ ያላመለጠችውን ሔዋን ታስታውሳለህን?

እንግዲያውስ፥ አንተም እንደ እርሷ ምክንያት በመደርደር ራስህን ለማጽደቅ አትሞክር፡፡
ይህ ሲነገርህም በተግባር እንጂ በከንፈርህ መልስ ለመስጠት አትጣር፡፡"
አስተውል ወዳጄ
አስተውል ወዳጄ
ያለፈው ዘመን ይብቃህ የኃጢያት ቫይረስ እንዳይገልህ በንስሐ ህይወት ተመለስ !!"

መልካም ምሽት
231 views 🄹, 19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 18:22:23 (የዝምታ ጩኸት )

ጸሐፊ መ/ር ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

አንባቢ ቢኒያም ብርሃኑ
_
ጌታ ሆይ ጩኸታችን አልሆነልንም:: ዝምታችንን ሰምተህ ሀገራችንን ከከበባት ጥፋት ታደግልን::
የእኛ መጨቃጨቅና ጠብ ባሕር አይከፍልም::
የእኛ ጩኸት ከመነካከስ በቀር አያሻግርም::
በአርምሞ የሚለምኑህን በእኛ ፊት ዝም አሉ የምንላቸው በአንተ ፊት ግን የሚጮኹትን ሰምተህ ታደገን::
272 views£di_wub, 15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 07:50:28 ±+ ጠላቴ ++
የማከር የምበጥሳት የምለኩስ የማጤሳት
በብርድ የምቆፈድዳት በሙቀት የማነዳት
አልብሼያት የጠኔን ሸማ የማቀልጣት እንደሻማ
ምቀኛዋ ደመኛዋ አሰቃይዋ ገራፊዋ
አሳሪዋ ደብዳቢዋ በክፉ የሚያይ ጣውንቷ
እኔ ራሴው ነኝ ለነፍሴ ባላጋራዋ ጠላቷ

ከቶ ወዴት ሊመጣ ከእኔ በላይ ለእኔ ጠላት
እኔ አይደለሁም ወይ ነፍሴን በኃጢአት የማቆስላት?
ማንም ቢጠላኝ ቢያጠቃኝ አያልፍም ከሥጋዬ
እኔ ግን አለሁኝ ክፉ የምኖር ነፍሴን በድዬ

በሥጋዬ እስር ቤት ውስጥ እያለቀሰች ታፍና
ጮኻ እንዳይወጣላትም ምላስ ለሥጋ ወግና
ያለ ምግብ ያለ ውኃ ከምትኖረው ተሰቃይታ
ከነፍሴ በላይ ማን አለ ከእስሩ ያልተፈታ?

ፈጣሪ ሆይ እባክህ አውጣኝ ከራሴ እሥራት
ነፍሴን ፍታልኝ እባክህ ከሥጋ አገዛዝ ሥርዓት
ሌላስ አላስቸግርም እባክህ ከራሴ ጠብቀኝ
ለጎስቋላዋ ነፍሴ የከፋው ጠላትዋ እኔ ነኝ

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
302 views£di_wub , 04:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-09 10:36:59 አንድ ናቸው

ሰላም እንደምን አላችሁ የልዑል እግዚአብሔር ልጆች የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአስራት የበረከት ልጆች የጻድቃን የሰማዕታት የመላዕክት ወዳጆች

በቅድሚያ አባቶቻችን ስለክርስቶስ ከማውቃችን በፊት ወይንም ነገረ ክርስቶስን ከመማራችን በፊት ስለድንግል ማርያም ወይንም ነገረ ማርያምን መማር ማወቅ አለብን እንዲሉ እንኳን ለእናታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም አመታዊ የልደት በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን

አስቀድሞ በቴክታ እና በጴጥሪቃ የጀመረው የቅድስት ድንግል ማርያም ታሪክ በዛሬው ዕለት ጸሐይ የተባለውን ኢየሱስ ክርስቶስ የምትወልድልን ጨረቃይቱ ቅድስት ድንግል ማርያም በሊባኖስ ተራራ ተወለደች።

እንዴት ድንቅ ነው ጸሐይን የምትወልድ ጨረቃ በቅዝቃዜው በሊባኖስ መወለድ

አንዳንዴ ግርም የሚለኝ ነገር ቢኖር የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እና የጌታችን አንድ መሆን ነው።አንድ መሆናቸው ከምን አንጻር ነው ብትሉኝ ከብዙ ነገሮች አንጻር ሲሆን ግን ለዛሬው የሚስማማውን ላንሳ

ሀና እና ኢያቄም በታላቅ ራዕይ ቅድስት ድንግል ማርያምን ለመውለድ ሀና በጸነሰች ጊዜ እመቤታችን በሀና ማህጸን ሆና በእግዚአብሔር ሀይል ብዙ ድንቅ የሚባሉ ተዓምራቶችን ስታደርግ አይሁድ ቀድሞ የሀና የኢያቄም ዘመዶች እነ ዳዊት እነ ሰሎሞን አርባ አርባ አመት ገዙን አሁን ከሀና እና ከኢያቄም የሚወለደው ምን ያክል ይገዛን ይሆን ስለዚህ እንግደላቸው ብለው ሲነሱ እነ ሐና ከእነሱ ሸሹ ከዚያም በስደት ሀገር በሊባኖስ ደረሱ።

በዛ በሊባኖስ በዛ ቅዝቃዜ በዛ ብርድ በበዛበት ቦታ የሚበላ እንኳን በሌለበት በስደት ባሉበት ቦታ ላይ ጨረቃይቱ ድንግል ማርያም በዚህ ዕለት ተወለደች ።

አይገርምም ድንግል ማርያም በዛ በማይመች ቦታ በዛ በቅዝቃዜ እንደተወለደች እሷም የአለም መድኃኒት ጌታችንን በቤተልሔም በከብቶች በረት በዛ በቅዝቃዜ ከቅዝቃዜው የተነሳም እንስሳት እስትንፋሳቸውን እየገበሩለት በነበረው በዛ በስደት ቦታ ወለደችው።

የእናታችን እና የጌታችን አንድ መሆናቸው በሁሉም ነገር ነው። ከእነዚህ መካከል አንዱ ይህ ነው።

ተጻፈ በኤልያቄም(E)
1/9/2014
543 viewsኤልያቄም, 07:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 18:27:32 ማስያስ ናይን
.
.
.


በቅናት ተሞልተው -ለክሳቸዉ ፅሕፈት-ነዉርን ቢያጡብህ፤
አይሁድ ተመካክረው-ምስክርን ገዙ-አደፍ ቢታጣብህ።

አይቶ ላስተዋለ-ልቆ የሚሰማ-ከአይሁድ ጫጫታ፤
ከንግግር በልጦ-ልብ የሚጠረጥር-ረጅም ዝምታ።

እንደምን ያለ ነው?

ምራቅ እየተፋ-ዲያቢሎስ አዳምን-ሲኦል እንዳስገባዉ፤
ጌታችን ተዋርዶ-ምራቅ ተተፍቶበት-ዳግመኛ ሊክሰዉ፤
ልምዳቸው እንዳይቀር-በርባንን ፍታልን ብለው ሲጠይቁ፤
ክርስቶስን ሰቅለው-ወንጀለኛን ገደልን-ብለው ሊራቀቁ።

የሾህ አክሊል -ጎነጎኑ -ከራሱ ሊያኖሩ፤
ሶኩን አቀዳጅተዉ-ንግሥናውን ሽረዉ-ሞቱን ሊናገሩ፤
ስቀለው!እያሉ - ሩህሩሁን ጌታ-ፍትሕን ነፈጉት፤
ንዋይ በገዛቸዉ-በሀሰት መሳክርት-ሞትን ፈረዱበት።

ስቀለው! ስቀለው !ይሰቀል !
የሚሉ ጩኸቶች -ከዛ ካደባባይ-አይለዉ ሲሰሙ፤
በጥላቻ መንፈስ -ፊቱን ተመልክተው-ሌሎች ሲራገሙ፤
መዝሙረኛው ዳዊት-በትንቢት መነፅር-ቀድሞ ተመልክቶ፤
በዉሻ አይሁዶች-የቀራኒዮዉ በግ-መከበቡን አይቶ።
"ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን
ወአኀዙኒ ማህበሮሙ ለእኩያን
ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን "


እንደምን ያለ ነው ?

ህመምን ፈዉሶ-ጎባጣ ያቀናን አልባስክን መገፈፍ፤
ከእጅህ በጎረሰ-ካንተ በተማረ -ወንበዴ መገረፍ።

ዉሃን የፈጠረ-ዉሃ ተከልክሎ-ሀሞት ሲቀርብለት፤
በሰፈነግ ሞልተው-ሆምጣጤ ቅልቅል-ቀድተው ሊያጠጡት፤
መራራ መጠጡን -ቀመሰና ተወዉ-ሊጠጣ አልወደደም፤
ለወጉት ከሳሾች-ሰድበው ለተፉበት-በቀል አልተመኘም።

ድንግሊቱ ታለቅሳለች-ከመስቀሉ ስር ተደፍታ፤
በመስቀል ዉሎ እያየች-ልጇ ሲንገላታ፤
ከደረቱ የተጠጋው -ታማኙ አገልጋይ-ትህትናን ያዘለዉ፤
እናቱ ትሆን ዘንድ-እሱ እንዲሆን ልጇ-አደራ ተሰጠዉ።

የአለም ብርሃን-ተከሶ ብታየዉ-ጠሀይቱ ጨለመች፤
የፍጥረታት ጌታ-መሞቱን ብታየው-ጨረቃ ደም ሆነች።

ዮሴፍ ወ ኒቆዲሞስ -በሐር በፍታ ገነዙት፤
መግነዙን አስረው-ባዲስ መቃብር አኖሩት።

ጌታችን ተነሳ- በሃይሉ-መቃብሩን ፈነቃቅሎ፤
በሥልጣኑ- ነፃ አወጣን -ሞታችንን ገድሎ፤
በፍቅር ተስቦ-ነፍሳትን አወጣ-ሲኦልን መዝብሮ፤
እብለት የሌለውን -ትንቢቱን ፈፀመ-ዲያቢሎስ አስሮ።

ግን እኔስ????

ከትንቢቱ ፍፃሜ-ከሞትና ትንሣኤው -አብሬ ያልተባበርኩ፤
ከመርከቢቱ ተኝቼ-ከጥልቁ ባህር የሰመጥኩ፤
መንገዱ የጠፋብኝ-በሃጢአት ሸክም የጎሰቆልኩ፤
ከቤት ርቄ-ስቅበዘበዝ-ማረፊያ አጥቼ፤
ወደ ኩነኔ የገባሁ-የፅድቅ መንገዱን ትቼ፤
ኪሪያላይሶን -ማረኝ አትለፈኝ፤
እንደቸርነትህ-ከእቅፍህ አስገባኝ።

የክፋትን መርዝ-በማር ለዉሼ-የምሸጥ፤
ከመቅደስህ ሰርቄ-ለመቅደስህ ስመፀዉት፤
ያቺን መክሊት -ቀበርኳት-እንዳተርፍበት ከሰጠኸኝ፤
ቆፍሬ አኖርኳት-ሸጬ ለዉጬ-ሳልገኝ፤
እብኖዲ ናይን -አምላክ ሆይ!ማረኝ፤
መፃጉዕ ነኝና- አይተህ አትለፈኝ።


ወንጌልን ሰምቼ-በሌላኛው ጆሮ-ዘፈን ስሰማበት፤
ቆሞ ባስቀደሰ-በክቡር አካሌ-እየጨፈርኩበት፤
ዘወትር ከደጅህ -የምገኝ-መንፈሴ ካንተ የራቀ፤
ብኩን ከንቱ -መሆኔ-አለማወቄን ያሳበቀ፤
ማስያን ናይን- መሲሕ ሆይ! ማረኝ
ለምፅ የወረሰኝ-ድዉይ ነኝና -አምላኬ ማረኝ፤
ማስያስ ናይን-መሲሕ ሆይ! ማረኝ።
639 views£di_wub , 15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-19 06:44:07

መስቀሉን ፍለጋ


ከሶስቱ ተራሮች በአንዱ ተቀብሮ፣
ሁሉም ከበዓቱ ቆሻሻን ጨምሮ።
አይሁድ ተመሣጥረዉ ፍቅርን ሊሸሽጉ፣
ለክርስቲያን ወገን መድኃኒት ሊነፍጉ።
ጌታ አልተነሳም ብለዉ ሊያስወሩ፣
የመስቀሉን ካሳ ዱካ ሊሰዉሩ።
ድዉይ እንዳይፈዉስ ሙት እንዳያነሳ፣
ምሥጢሩ እንዲሸሸግ ክብሩ እንዲረሳ።
የመስቀሉ ፍቅር ልቧን ቢያቃጥለዉ፣
የንግስቷን ሀሳብ ሰቅዞ ቢይዘዉ።
የጌታዋ መስቀል ባለም እንዲያበራ፣
መሻቷን ልትፈፅም ተራራ አስቆፍራ።
የንግስቷ አሽከሮች ስፍራዉ ጠፍቶባቸዉ፣
ቦታዉን ለማግኘት ተሟጦ ተስፋቸዉ።
ዉዝግቡ ቆሞ ልባቸዉ ሲረጋ፣
ታሪክ የሚያዉቁትን ተነሱ ፍለጋ።
አንድ ሽማግሌ ምሥጢሩን ያወቀ፣
ያባቶቹን ባህል ትዉፊት ያስጠበቀ።
መድኃኒት ስትፈልግ ኪራኮስን ይዛ፣
እምነትን ተጫምታ ወንጌል ተመርኩዛ።
እሳቱን ለኩሳ ደመራ አስደምራ፣
ጢሱ እንዲመራት እጣንን ጨምራ።
የደመራዉ ጢስ ወደላይ ነጎደ፣
መስቀል ወዳለበት ተራራ ሰገደ።
የነፃነት አርማ የድህነት ምልክት፣
ከባርነት መዉጫ መዳኛ ትምክህት።
የተዋህዶን ንጉስ አንግሱ በተስፋ፣
ዕፀ_መስቀል ያዙ ጠላት እንዲጠፋ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ኤደን
480 viewsCreamy , 03:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-11 22:26:03
90 viewsኤልያቄም, 19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-11 22:25:43
83 viewsኤልያቄም, 19:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ