Get Mystery Box with random crypto!

#የዘላለም_ሕይወት_ዋስትና (አለመጥፋት) ክፍል ሁለት #The_doctrine_of_eternal_se | መንገድና እውነት

#የዘላለም_ሕይወት_ዋስትና (አለመጥፋት) ክፍል ሁለት
#The_doctrine_of_eternal_security part two
========(#Small sized audio)
#በወንድም_ሀብታሙ_አዲሱ

ዋነኛው የአዲስ ኪዳን ትምህርት መሠረት የአንድ አማኝ ደኀንነት የሚያገለግለው ለዘለዓለም መሆኑን ማብሰር ነው።#ዮሐ3:15-18,36፣5:24

ይህ ደኀንነት በአማኙ መልካምነት እና ብርታት ላይ የተመሰረተ አይደለም። ኤፌ 2፡8-9

ማንም አማኝ ዳግመኛ የተወለደው
ኃጢአትን ላለማድረግና በጽድቅ ለመኖር ቢሆንም በዚህ ምድራዊ ተፈጥሮ ኃጢያትን ባለማድረ መቀጠል የሚችል አይሆንም ፣
ይህም ሲባል እውነተኛ ክርስቲያን በፀጋ የዳነ ከሆነ በሐጥያት የመቀጠል መብት አለው ማለት አይደለም ይልቅስ የእግዚአብሔር ፀጋ ሃጢያተኝነትን እና አለማዊ ምኞትን ያስክዳል። #ቲቶ 2፡11-14

ክርስቶስ በመስቀል ላይ ስለ ኀጢአት በመሞት የሰጠን የዘላለም ህይወት እኛ #በድካማችን #ተሣሥተንም ሆነ #አውቀን ስንበድል ከእኛ የሚወሰድና እኛን ለዘላለም ሞት የሚዳርገን አይደለም፡፡#1ኛጴጥ1:23.

1 ጴጥሮስ 1 :23፤
ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፥ በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ።

የወንጌል እውነት አገልግሎት ጅማ
Gospel Truth Ministry Jimma.
@DawitFassilMinistry