Get Mystery Box with random crypto!

Wasu Mohammed(ዋሱ መሀመድ)

የሰርጥ አድራሻ: @wasulife
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 200.44K
የሰርጥ መግለጫ

እንኳን ደህና መጡ‼
✔ማስታወቂያ ለማሰራት እና ጥቆማ ለመስጠት በዚህ ይጠቀሙ ☞https://t.me/WasuMohammed
✔ ቻናሉን ለመቀላቀል Join ☞http://t.me/Wasulife
ከልብ አመሰግናለሁ♥🙏

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-12 20:53:37
አሸንፈዋል

በአሜሪካ በተካሔደ ዓለም አቀፍ የሮቦፌስት ውድድር ታዳጊ ኢትዮጵያውያን የሮቦቲክስ ተወዳዳሪዎች አሸናፊ ሆነዋል።

በውድድሩ 23 ታዳጊ ኢትዮጵያውያን በተለያዮ ዘርፎች የተሳተፉ ሲሆን ከ10 ዓመት በታች በሮቦፓሬድ ምድብ የተወዳደረው ታዳጊ ማሸነፉ ተሠምቷል።

ሌላኛው ታዳጊ ተወዳዳሪ ከ14-16 ዓመት ምድብ ተሳትፎ ስፔሻል አዋርድ ሽልማትን ማግኘት ችሏል።

በየውድድሩ ከ1-3 ድረስ ለወጡ ተወዳዳሪዎች የሜዳሊያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
Via Tikvahuniversity
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው በዚህ ይከታተሉ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
ቤተሰብ በቅንነት ሰብስክራይብ       
https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g
ማስታወቂያና ጥቆማ መቀበያ
https://t.me/wasumohammed
13.6K viewsWasu Mohammed, edited  17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-12 19:02:39
Inbox

<<…አንድ ጥቆማ ላደርስህ ፈልጌ ነው ትናንት ቅዳሜ ከቄራ ከሙስሊም ስጋ ቤት ስጋ ገዝቸ ስመጣ ከምሽቱ አንድ ሰዓት  መገናኛ ቤተልሄም ፕላዛ አስፓልት ዳር ሁለት ደንቦች ያገኙኛል ምን እንደያዝኩ ጠየቁኝ  የያዝኩትን ነገርኳቸው ህገ ወጥ እርድ ነው ወደ ቢሮ መሄድ አለብን አሉኝ ከየት እንደገዛሁት በዝርዝር ነገርኳቸው በፍጹም ሊረዱኝ አልቻሉም ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ ወደ ቢሮ ሄድን እኔ የጠበኩ አለቃቸውን ነበር እነሱ ግን የድርድር ጥያቄ አቀረቡልኝ 7500 ብር  ከምትቀጣ ለእኛ 1000 ብር ስጠንና እንሸኝህ አሉኝ

ሌላ ጭቅጭቅ ተፈጠረ በዚህም ጊዜው እየመሸ ሄደ እኔ ደረኩ እነሱም እንደዛው መጨረሻ ላይ ልክ ባይሆንም 200 ብር ከፍየ ወደ ቤቴ ሄድኩ

እኔ ጋርም ችግር ነበር ደረሰኝ አልተቀበልኩም ነበር የመንግስት ተቋም ነው ቄራዎች ድርጅት እነሱም ለሁሉም ደንበኛ አስበው ቢሰጡ የደምብ ማስከበር ቢሮ የልጆቹን ስነ ምግባር ቢያርቅ ቢሰራ አንድ ህግ ሲወጣ ህጉን ከማስከበር በስበብ አስባቡ ህዝብን ማንገላታት ጥሩ አይደለምና ቢታሰብበት እላለሁ።…>>
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው በዚህ ይከታተሉ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
ቤተሰብ በቅንነት ሰብስክራይብ       
https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g
ማስታወቂያና ጥቆማ መቀበያ
https://t.me/wasumohammed
15.0K viewsWasu Mohammed, edited  16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-12 16:08:42
ከሌቦቹ ላይ የሚረከብ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ!!!

በተፈፀመ የቅሚያ ወንጀል መነሻነት በተደረገ የክትትል ስራ ከሌቦች ጋር ግንኙነት በመፍጠር የተሰረቁ ሞባይል ስልኮችን የሚረከብ  ግለሰብን  በቁጥጥር ስር በማዋለ በርካታ ሞባይል ስልኮችን ማስመለሱን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
     
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው ማሞ ድልድይ አካባቢ ግንቦት 4 ቀን 2016 ዓ/ም ከማለዳ 12 ሰዓት ከ20 ላይ አንድ ግለሰብ ሞባይል ስልክ መቀማታቸውን ገንደ ቆሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡

ሪፖርቱ የደረሰው ፖሊስ የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ከሌቦቹ ላይ የሚረከብ ታምራት ፍቅረማርያም የተባለን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡

ፖሊስ በመኖሪያ ቤቱ ባደረገው  ብርበራ  በእለቱ የተሰረቀውን የሞባይል ስልክና በልዩ ልዩ ጊዚያት ከሌቦች የተረከባቸውን 61  ስማርት ሞባይል ስልኮችን ፣ 251 የታብሌት ስልክ ሽፋኖችን ፣ 2 ላፕቶፖችን እና በጥሬ 60 ሺ አንድ መቶ ብር ከሌባ ተቀባዩ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ መያዙን ገልጿል ፡፡

ግለሰቡ የተሰረቁ እቃዎች መግዛትን እንደመደበኛ ስራ ይዞ እየሰራ መሆንን የገለፀው ፖሊስ  ወንጀሉን ለመሸፈን  የሌሎች ሰዎች መኖሪያ ቤት ለማስፈተሽ ቢሞክርም በህብረተሰቡ ትብብር ያሰበው እንዳልተሳካት ታውቋል፡፡

ወንጀለኛው የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን ከሌቦች ተቀብሎ የሚያስቀምጠው በተከራየው ቤት ውስጥ መሆኑን ፖሊስ አመልክቷል።

የሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል የሚል ማንኛውም ግለሰብ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገንደ ቆሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ ንብረቱን መረከብ  እንደሚችልም አዲስ አበባ ፖሊስ ፖሊስ  አስታውቋል፡፡
Join @wasulife
@wasumohammed
16.2K viewsWasu Mohammed, 13:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-12 14:49:44
በኢትዮጵያ ላይ የአውሮፓ ኅብረት ያሳለፈውን ውሳኔ ካልቀየረ መንግሥት ተመጣጣኝ ዕርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ

የአውሮፓ ኅብረት ምክር ቤት ከሳምንት በፊት ለኢትዮጵያውያን የሚደረገውን የቪዛ አሰጣጥ ሒደት ለማጥበቅ ያሳለፈውን ውሳኔ ካልቀየረ፣ መንግሥት ተመጣጣኝ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ አስታወቀ፡፡

የአውሮፓ ኅብረት በቪዛ ጉዳይ በቅርቡ ያሳለፈውን ውሳኔ እንዲሽር ኢትዮጵያ እንደምትፈልግ ጠቅሰው፣ ይህ ካልሆነ ግን ከውሳኔው ጋር የሚጣጣም የራሷን ተመጣጣኝ ዕርምጃ ትወስዳለች ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ ናቸው፡፡

ቃል አቀባዩ በሳምንታዊ መግለጫቸው የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ ላይ ያሳለፈው የቪዛ ውሳኔ ትክክል እንዳልሆነ በመግለጽ፣ ኢትዮጵያ ለኅብረቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱን በጠበቀ መንገድ ማሳወቋን አስረድተዋል፡፡

ኅብረቱ ወደ አውሮፓ የገቡ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ አገራቸው በመመለሱ ረገድ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ቢያቀርብም፣ ባለሥልጣናት ተገቢውን ምላሽ ባለመስጠታቸው በኢትዮጵያውያን ላይ የቪዛ አሰጣጥ አሠራሩን ማጥበቁን በማስታወቅ ነበር ውሳኔውን ያስተላለፈው፡፡

በአውሮፓ ኅብረት በተለይም ‹‹ሸንገን ቪዛ›› ውስጥ በሚገኙ አገሮች ጥገኝነት የጠየቁ ኢትዮጵያውያን ጉዳያቸው የመኖሪያ ፈቃድ የማያሰጥ ሆኖ ሲገኝ፣ ጉዳዩ በፍርድ ቤት ታይቶ ወደ አገራቸው መመለስ አለባቸው የሚባሉትን ኢትዮጵያ እንድትወስድ በመጠየቁ ምክንያት ውሳኔው መተላለፉን ቃል አቀባዩ ተናግረዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ከኅብረቱ ጋር እየሠራ የቆየ
መሆኑን የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ ውሳኔው በበርካታ ሚዲያዎች እንደተዘገበው የቪዛ ክልከላ አይደለም ብለዋል፡፡
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው በዚህ ይከታተሉ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
15.7K viewsWasu Mohammed, edited  11:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-12 14:46:42
የዋጋ ማስተካከያ የተደረገባቸው እጣዎች ሽያጭ

የዶ/ር አብዱ፣ ዶ/ር ሙሀመድ እና ጓደኞቻቸው ሪልስቴት ማህበር ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ ሚያዚያ 28/2016 ባደረገው ስብሰባ ከግንቦት 1/2016 ጀምሮ የእጣ ሽያጭ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ያደረገ ሲሆን እንደሚከተለው መሆኑን እንገልጻለን።

①. ደሴ ገራዶ ጡንጂት አምባ አደባባይ ላይ የሚገኝ 3 መጋቢ መንገድ ያለው የቅይጥ ንግድ ሳይት፤ ፕላን እየተሠራለት ያለ
ባለ 2 መኝታ መኖሪያ ቤት፤ አንድ ሱቅ  እና አንድ የጋራ ገቢ ያለው ፍሎር 170 ሺህ ብር

②. ደሴ ገራዶ አዲሱ ምሪት ጡንጅት አምባ ሳይት፤,ካርታ ጨርሰ፤ፕላን እየተሰራለት ያለ እና የሁለት ወር መዋጮ ያለው
ባለ 2 መኝታ መኖሪያ ቤት እና 1 ሱቅ 220 ሺህ ብር
በለ 3 መኝታ መኖሪያ ቤት እና 1 ሱቅ በ280 ሺህ ብር

ለበለጠ መረጃ በማህበሩ ስልኮች:—
0937411111 ወይም 0938411111 ይደውሉ
ታማኝነት መገለጫችን ነው።

ዶ/ር አብዱ፣ ዶ/ር ሙሀመድ እና ጓደኞቻቸው ሪልስቴት የማልማትና የማከፋፈል ህ/ሽ/ማ
15.1K viewsWasu Mohammed, 11:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-12 12:10:05
ባህር ዳር

በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው ድልድይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት መመረቁን ከመንግስታዊ የመገናኛ አውታሮች ለማየት ችለናል።ድልድዩ 1·4 ቢሊየን ብር ወጭ የተደረገበት ነው ተብሏል።በክልሉ ግጭት ተቀስቅሶ በመንግስት የፀጥታ ሀይሎችና የፈኖ ሀይሎች መካከል ተኩስ መካሄድ ከጀመረ በኋላ ጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ ባህርዳር ሲጓዙ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።ትናንት በጎርጎራ መቆየታቸው ታውቋል።በክልሉ አሁንም ግጭቱ በተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ ይገኛል።

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው በዚህ ይከታተሉ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
ቤተሰብ በቅንነት ሰብስክራይብ       
https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g
ማስታወቂያና ጥቆማ መቀበያ
https://t.me/wasumohammed
16.1K viewsWasu Mohammed, edited  09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-12 12:02:43
ADVERTISMENT

ገንዘብዎ ዋጋ የሚያገኝበት ስፍራ!

አያት አክስዮን ማህበር በ2015 ዓ.ም 51% ትርፍ /dividend/ ለባላክሲዮኖች አከፋፍሏል

የ 1 ሚሊዮን ብር አክሲዮን የነበራቸው ባለአክሲዮኖች 510ሺ ብር ትርፍ/Dividend/ አግኝተዋል

የ 5 ሚሊዮን ብር የገዙ 2.5 ሚሊዮን ብር አትርፈዋል

የአንድ አክሲዮን ዋጋ 100 ብር ነው

ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የአክሲዮን መጠን 2500 ነው

ዝቅተኛ የአክሲዮን ዋጋ 262,500 ብር ፣ 5% የአገልግሎት ክፍያን ጨምሮ

112,500 ብር ከፍለው ቀሪውን በሶስት ዓመት መጨረስ ይችላሉ

ከፍተኛ አክሲዮን ገደብ የለውም

አክሲዮኑን ከገዙ ከአንደኛው ወር ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ ይሆናሉ

ለበለጠ መረጃ: በ 0910798353/ 0926692990 ይደውሉ ( ቀጥታ ወይም Whatsapp)
14.8K viewsWasu Mohammed, 09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-12 10:59:43
እናት ለዘላለም ትኑር!

እናት የአለም መድሃኒት ነች ስለእሷ ለመግለፅ ለሁሉም በየትኛውም ቋንቋ ይከብዳል።ለዚህም ይመስላል "እናት ለዘላለም ትኑር" የሚለው ሃሳብ አብዝሃኞቻችንን የሚያግባባን።የፍቅር ተምሳሌቷ፣ዝቅ ብላ ሠርታ ለልጇ ከፍታ የምትደክመዋ፣ቤትና ትዳሯን አክባሪዋ፣የአለም ጌጧ እናት ለዘላለም ትኑር

ዛሬ ይቺን ምድር ከፈጣሪ በታች የቀላቀለችን ፤ አለም ፊቷን ብታዞርብን እሷ ግን በደስታ ምትቀበለን ፤ ለኛ ሁሉ ነገራችን የሆነች ፤ ከአይኗ ብሌን በላይ ምትሳሳልን እናታችን ቀኗ ነው በእርግጥም ሁሉም ቀን እናታችንን ማክበር አለብን ነገርግን ዛሬ ልዩ ቀኗ ነው።

የእናቶች ቀን እናቶችን፣ እናትነትን እና እናቶች በህብረተሰቡ ላይ ያላቸውን ተጽዕኖ የምናስብበት ቀን ነው።ዘመናዊው የእናቶች ቀን የተከበረው በ1908 እ.ኤ.አ. አና ጃርቪስ የተባለች ሴት እናቷን ለመዘከር ባዘጋጀቸው ዝግጅት ሲሆን ጃርቪስ ከዚያን ጊዜ አንስቶ የእናቶች ቀን በአሜሪካ እንዲታወቅ እና እንዲከበር የተለያዩ ቅስቀሳዎችን ማድረግ ጀመረች። ከ6 አመት በኋላ ውጤቱ ሰምሮላት በ1914 በዓሉ መከበር ጀመረ::

በተለያዩ የአለም ክፍሎች በተለያየ ቀን ታስቦ የሚውለው ይህ በአል በሰኔ ወር ከሚከበረው የአባቶች ቀን ጋር ወላጅነትን የምናወድስበት ቀን ነው። በአሉ በዘመናዊነት በአሜሪካ መከበር ከመጀመሩ በፊት በግሪክ እና በሮም በተመሳሳይ ፌስቲቫሎች ይካሄዱ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ።
ክብር ለእናቶች
@wasulife
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው በዚህ ይከታተሉ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
እ ና ት
14.2K viewsWasu Mohammed, 07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-12 10:58:28
ADVERTISMENT

አፊያ ሙሀመድ ከፍተኛ የባህል ሕክምና እና ዘመናዊ የዋግምት አገልግሎት

  የምንሰጣቸው የባህል ህክምናዎች

➢ ለውጭና ለውስጥ ኪንታሮት
➢ ለማድያት
➢ ለሱኳር በሽታ
➢ለጉበት(ለወፍ በሽታ)
➢ለጨጎራ ህመም
➢ለስፈተወሲብ
➢ለደም ግፊት
➢ለአስም ወይም ሳይነስ
➢ለሚጥል በሺታ
➢ ለእሪህና ቁርጥማት
➢ለራስ ህመም (ማይግሪን)
➢ለቺፌ ና ለጭርት
➢ለቋቁቻና ፎረፎር
➢ለእጢና ለእባጭ
➢ለወገብ ህመም
➢ለመካንነት ለወድም ለሴትም
➢ለጆሮና ለአይን ህመም
➢ለሆድ ህመም
➢ዘመናዊ የዋግምት አገልግሎት በተቋማችን እንሰጣለን።
ከኢትዮጵያ ባህላዊ ህክምና አዋቂዎች ማህበር በዘርፉ ህጋዊ የባህል ህክምና ፍቃድ ያለን ነን።
አድራሻ:አዲስ አበባ አየር ጤና
   ስልክ ቁጥር   0927506650
                         0987133734
                          0956522222
ቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/+08vmUP_ntvE5NmM0
14.0K viewsWasu Mohammed, 07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-12 09:30:03
አዲስ አበባ

ጎሮ አካባቢ በተከሰተ የእሳት አደጋ 13 የንግድ ሱቆችና በጋራዥ ዉስጥ የነበሩ አምስት ተሽከርካሪዎች ሙሉ በሙሉ ወደሙ።

ትናንት ግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት 6:50 በለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 9 ጎሮ ገብርዔል ቤተክርስቲያን አጠገብ የተነሳዉ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

በእሳት አደጋዉ በቤተክርስቲን ዙሪያ ያሉ 13 የንግድ ሱቆችና በጋራዥ ዉስጥ የነበሩ አምስት ተሽከርካሪዎች ሙሉ ሙሉ የወደሙ እና በጋራዡ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል።

የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠር 12 የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪዎች 66 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የተሰማሩ ሲሆን የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠርም 4 :10 ሰዓት መፍጀቱን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ተናግረዋል።

15 ተሽከርካሪዎችን ከቃጠለው ማትረፍ መቻሉንና በአደጋዉ በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት አልመድረሱን አቶ ንጋቱ ጨምረው ተናግረዋል።

በጋራዡ ውስጥ የነበሩ ተሽከርካሪዎች የያዙት ነዳጅና ሌሎች ፈሳሽ ተቀጣጣዮች እንዲሁም ንግድ ሱቆቹ እሳትን ሊቋቋሙ ከማይችሉ ቆርቆሮና መሰል ግብዓቶች መገንባታቸዉ ለእሳቱ መባባስ አስተዋጾኦ ማድረጉን አቶ ንጋቱ ተናግረዋል።

የተሽከርካሪ ጥገና አገልግሎት የሚሰጡ ጋራዦች ደረጃቸዉን በጠበቁ ግብዓቶች የተገነቡና ከንግድ ሱቆች ከመኖሪያ አካባቢዎች የራቁ መሆን እንዳለበት ኮሚሽኑ አስጠንቅቋል።የአደጋውን መንስኤ ፖሊስ እያጣራ ይገኛል።

መረጃው ከብስራት ሬዲዬና ቴሌቪዥን የተወሰደ ነው።

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው በዚህ ይከታተሉ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
14.6K viewsW M, 06:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ