*** ሰው ስላንተ ምን እያለ ነው? *** “የሞተን ውሻ ማንም አይደበድበውም!” ዴል ካርኒጌ። | Vision-power Page
*** ሰው ስላንተ ምን እያለ ነው? ***
“የሞተን ውሻ ማንም አይደበድበውም!” ዴል ካርኒጌ።
ምንም ካልሰራህ ማንም ምንም አይልህም። መንቀሳቀስ ስትጀምር ግን የሚተቹህ፣ በነገር የሚጎነትሉህ፣ የሚሰድቡህ፣ የሚጠቋቆሙብህ … ይበዛል። ይህ ለአንተ የማደግህ ምልክት ነው። እየተንቀሳቀስክ ለመሆንህ ጠቋሚ ነው።ጥሩ እየሰራህ ነው ማለት ነው።
እናም ወዳጄ ሆይ ሰዎች ምን አሉኝ ብለህ እንቅስቃሴህን አትግታው። ይልቁንም ጠንክረህ ግፋበት።
ስኬታማ እና የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ!