መዝሙር 20 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እግዚአብሔር በጭንቅ ቀን ይስማህ፤ የያዕቆብም አምላክ ስም ይጠብቅህ። ² ከመቅደሱ ረድኤት ይላክልህ፤ ከጽዮንም ደግፎ ይያዝህ። ³ ቍርባንህን ሁሉ ያስብልህ፤ የሚቃጠል መሥዋዕትህን ይቀበልልህ። ሴላ ⁴ የልብህን መሻት ይስጥህ፤ ዕቅድህን ሁሉ ያከናውንልህ። ⁵ በአንተ ድል ደስ ይበለን፤ በአምላካችን ስም አርማችንን ከፍ እናደርጋለን፤ እግዚአብሔር የለመንኸውን ሁሉ ይፈጽምልህ። @TrueGrace From FiRam 93 viewsFirew Emiru2 በዋጋ የተገዛ ፍሬ , 05:36