. የጂል ቀልድ አትቀልድ! ~ በጦር፣ በጠመንጃ፣ በሰይፍ፣ በጩቤ፣ በዱላ፣ በመጥረቢያ፣ በመኪና፣… ሰዎች ለማስደንገጥ ከመቀለድ፣ ከመቃጣት ተጠንቀቅ። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:– من أشار إلى أخيه بحديدة فإن الملائكة تلعنه حتى ينتهي. "ወደ ወንድሙ በመሳሪያ የጠቆመ እስከሚታቀብ ድረስ መላእክት ይረግሙታል።" [ሙስሊም] በሌላም ሐዲሥ እንዲህ ብለዋል:– لا يحل لمسلم أن يروع مسلماً. "ሙስሊም ሙስሊምን ሊያስደነግጥ አይፈቀድለትም።" አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል። ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ:– "አንድ ሰው በምርም ይሁን በቀልድ ወደ ወንድሙ ጠመንጃ ሊያዞር አይፈቀድለትም። መኪናም እንዲሁ (አይፈቀድም)። የከፋ ነውና።" [ሸርሑ ሶሒሒል ቡኻሪ: 9/ 502] = (ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 30/2010) የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor 322 views06:16