Get Mystery Box with random crypto!

ትረካ እና ግጥም

የቴሌግራም ቻናል አርማ terkagetm — ትረካ እና ግጥም
የቴሌግራም ቻናል አርማ terkagetm — ትረካ እና ግጥም
የሰርጥ አድራሻ: @terkagetm
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 447
የሰርጥ መግለጫ

➲የተለያዩ ትረካ እና ግጥም የምታገኙበት ቻናል ነዉ ::
ወደ ግሩፑ ለመቀላቀል 👉 @terkagetem

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-01-28 07:17:22
ይነጋል!
.
ታድለሻል ቢሉም፣
የ13 ወር ፀሀይ፣ የ13 ወር ፀጋ
ብርሀንሽ ተሰርቆ፣
ሲጨላልም እንጂ፣ መች አየን ሲነጋ?
ተፈጥሮ ቸር ሆና፣
ሰማይዋ ባይነጥፍ፣ ምድሯ ቢለመልም፣

ከልጆቿ ልብ ውስጥ፣
ፍቅር ሲጎድል ነው፣ ሀገር የምትጨልም!፣
"አረ ነግቷል" ቢሉ የታለ የነጋው?
አዕላፋት ተቧድነው፣ በየጎጥ በመንጋው፣
ሰው ከነገ ይልቅ፣ ዛሬን እያሰጋው የታለ የነጋው?
ታሪኩን እንዳይፅፍ፣ ትውልድ እጁ ታስሮ፣
በትላንቱ ሾተል ዛሬው ተሸንቁሮ፣
ባልኖረው ተካሶ፣ ባልሰራው ተዋቅሶ፣
ለፀብ መዶለቻ፣ ያ'ያቱን ስም ጠቅሶ፣
ላለፈው ሲናከስ ለመጪው ሳይተጋ፣
በምን ስሌት ይሆን፣
ትዉልዷ ጨልሞ ሀገር የምትነጋ?
.
የህሊና መስታወት በጥበብ ሲፀዳ፣
ማስተዋል እንዳ'አደይ ፈክቶ ሲፈነዳ፣
መገፋፋት ሲቀር ፣መደጋገፍ ነግሶ
አንዱ ማገር ሲሆን፣ ሌላኛው ምሰሶ፣
የአብሮነትን ሸማ ትዉልዱ ሲሸምን፣
ያኔ ነው ሀገሬ መንጋቷን የማምን።
.
በረከት በላይነህ

@terkagetm
@terkagetm
1.3K viewsedited  04:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-26 16:08:08 ይነበብ

አንድ ታካሚ ከባድ የሆነ የወገብ አደጋ ደርሶበት ዶክተር ጋር በጠዋቱ ይመጣል:

ዶ/ር:- "ወገብህ እንዲህ እስኪሆን ድረስ ምን ገጥሞህ ነው?"
ታካሚ:- "ይሄወልህ ዶክተርዬ ስራዬ ሌሊት ነው ታዲያ ዛሬ ጠዋት ኮንዶሚኒዬም ቤታችን ስገባ መኝታቤት ከሚስቴ ጋር የሆነ ሰው ሲያንኮሻኩሽ ሰማሁኝ: መኝታ ቤቱን ከፍቼ ዘው ብዬ ስገባ ሚስቴ ብቻ ነው ያለችው።

የቤቱ ሁኔታ ግን የሆነ ሰው እንደነበረ ያስታውቃል: ከመኝታ ቤት ወጣሁና በረንዳው ላይ ሆኜ ወደታች ስመለከት የሆነ ሰው ሱሪውን እየታጠቀ ሲሮጥ አየሁኝ... ዶክተርዬ በጣም ተናድጄ ስለነበር ጉልበቱን ከየት እንዳገኘሁ ሣላውቅ ሳሎን ያለውን ፍሪጅ አንስቼ ወረወርኩበት... ያንን ከባድ ፍሪጅ ሳነሳ ነበር ታዲያ ወገቤን ያመመኝ"

ዶክተሩ ይሄን ታካሚ ካከመ በሁዋላ ሌላ ታካሚ መኪና የተገጨ በሚመስል ሁኔታ ሰውነቱ ቆሳስሎ ይገባል:-
ዶ/ር:- ምንድነው የመጀመሪያው ታካሚዬ ሲገርመኝ ያንተ ደግሞ ባሰ! ምንሆነህ ነው?
ታካሚ 2:- "ይሄውልህ ዶክተር ዛሬ አዲሱን ስራዬን የምጀምርበት ቀን ነበር ድንገት አርፍጄ ተነሳሁኝና ከቤቴ ስወጣ ሱሪዬን እየለባበስኩኝ እየሮጥኩ እያለ ከየት መጣ ያላልኩት ፍሪጅ ላዬ ላይ ወደቀብኝ!"

ዶክተሩ ይሄንንም አክሞ ከሸኘ በሁዋላ ሌላ ታካሚ ይገባል:-
ይሄኛው ታካሚ ደግሞ ከሁለቱ በባሰ እና በሚዘገንን ሁኔታ ቆሳስሎ ነበር የገባው:-
ዶ/ር:- ኧረ ዛሬ ምን አይነት ቀን ነው!? አንተ ደግም ምን ሆነህ ነው?
ታካሚ 3:- "ዶክተር ለምን? እንዴት? ማን? ብለህ እንዳትጠይቀኝ: ዛሬ ጠዋት
ፍሪጅ ውስጥ ገብቼ እያለ ከፎቅ ላይ ተከስክሼ ነው

@terkagetm @terkagetm
1.1K viewsedited  13:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-25 19:15:40
ለ ፈገግታ ቻናሉን ይቀላቀሉ @terkagetm @terkagetm

ጎዳናው ዳር ቆሜ ሚኒ ባስ እየጠበኩ ድንገት ዞር ስል ግን አንድ ትዕይንት አይኔን ያዘው አንድ እጁ የተቆረጥ ጠብደል ለማኝ በቀኝ እጁ ገጀራ ይዞ እየነቀነቀ '' አረ ስለ ገብርኤል .....አረ ስለ ገብርኤል.... ...እኔ ተናግሬአለሁ ስለ ገብርኤል " በማለት አላፊ አግዳሚውን ይለምናል።አላፊ አግዳሚውም ገብርኤልን ሳይሆን ገጀራውን ፈርቶ ምፅዋት ይሰጣል

አዲስአበባ አበባ ሰሞኑን ማታ ማታ በጥቂቱ በርታ በብዙ ጠፍታ ፊልም የተጀመረበት ግዙፍ ሲኒማ ቤት ትመስላለች ።ከሬዲዮዎን ውስጥ ያለው ጋዜጠኛ "በቅርቡ ኃይል ቆጣቢ አምፖሎች ለህብረተሰቡ እንደሚታደሉ ተገልጿል ።
ይሁን እንጂ የሀይል ቆጣቢ አምፖሎች ለወትሮው ከምንጠቀምባቸው አምፖሎች ጋር ሲነፃፀሩ የብርሀን መጠናቸው አነስተኛ ነው የሚል አስተያየት አለ።እርሶ በዚ ላይ ምን አሰተያየት አለዎት ሲል ጠየቀ
'' ዌል ኃይል ቆጣቢ አምፖሎች የብርሀን መጠናቸው አነስተኛ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም '' አሉ ባለስልጣኑ .......ቀጥለውም

አምፖሎቹ ደብዛዛ ቢሆኑም ገረዳችንን ከሚስታችን ለመለየት የሚያስችል በቂ ብርሀን ይኖራቸዋል
@terkagetm
935 viewsedited  16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-24 09:51:30
ይችስ_ላም_ጠገበች

ወተት ለመጠጣት የገዛኋት ላም
መልኳን አሳምራ ቆዳዋ ለምለም
ሶስት ዓመት ሙሉ ስለፋ ስደክም
ወተቱ ቀርቶብኝ ነሳችኝ ሰላም

አሁን አበዛቺው በጣም ፈነጠዘች
የበረት ከብቶችን ሌሎችን አወከች
አጥንት በሌለው በምላሷ ቆመች
ወተቷን ካልጠጣሁ ጥጃ ካልወለደች
መልኳ ምን ይሰራል ገቢሯን ከሳተች
ልረዳት መሰለኝ

''ይችስ_ላም_ጠገበች''

ገባ በሉና አስተያየት ስጡ.......
Join us @terkagetm
910 viewsedited  06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-19 07:42:38
#እቴ

ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ
ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ
ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ
ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤
ይስጥሽ ከጸጉሮቼ ከአናቴ ላይ ዘግኖ
ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ
አወይ ጸጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ
ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ፤
... እቴ
ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ
ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ
ከአይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ
እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ።

እቴ
እጄን ብትፈልጊ
እግሬን ብትፈልጊ
አንገቴን ደረቴን
ተሰጥኦ ሀሳቤን
ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ
እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ
ያስቀርልኝ አይኔን
ያስቀርልኝ አይኔን
አንቺን ማየት ብቻ ያኖረኛል እኔን

በእውቀቱ_ስዩም

Join&share @terkagetm
944 views04:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-13 07:48:15 ነግሬሽ ነበረ

በላይ_በቀለ_ወያ
-------------
ሴት ክብሯን ረስታ ፣ ጭኗን እንዳታምነው
ሁሉን ያጣል ብዬ ፣ የሁሉም የሆነው!!!

ነግሬሽ ነበረ
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ
የወንድ ልጅን ዐይን..
ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ
ነግሬሽ ነበረ...
ትንሽ ስትዘነጊኝ ፣ ብዙ እንደማስብ!!!

ነግሬሽ ነበረ... ባትሰሚኝም እንኳ
ሳሙና ነው ብዬ ፣ የቆንጆ ሴት መልኳ
እድፋም ስሜቶችን...
አሽታ ስታነፃ ፣ ያበቃል ታሪኳ!!!

ነግሬሽ ነበረ
ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት
በክብር ነው እንጂ...
በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡
ክብረ ቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ እናቶች አይደሉም
ነግሬሽ ነበረ
እናትነት ስሟ
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ።

ነግሬሽ ነበረ...
ሴት ክብሯን ስትጥል ፣ እድሜዋ ይሔዳል
የወንድ ልጅ ቤቱ...
የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡

ነግሬሽ ነበረ...
ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው
ቁንጅናም ይረክሳል!
ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው!
ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ
"ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ውሸት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ።

ሞኝ ሰው ሲመክሩት
ሞኝ ሰው ሲነግሩት
የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ
ግን እነግርሻለሁ!
ነግሪያት ነበር ስል
ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ።

ግን እነግርሻለሁ
ግን እመክርሻለሁ
ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም
ሁሉም ይመኟታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!!

#በላይ_በቀለ_ወያ
545 views04:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-08 21:19:50 "ይቅር ከተባለ"
እንግዲህ ወንድሜ ይቅር ከተባለ፣
በመንፈሥ አካሄድ ከተሠላሠለ።
ትልቁ ቤንች ማርክ ለሁሉም ጥፋቶች፣
ይቅር የማይባል ወንጀል ፈጻሚዎች፣
የቀን ጅቦች ናቸው የጁንታው አባሎች።
ሥለዚህ ጁንታዎች ይቅር ከተባሉ፣
ተራ ወንጀለኞች ታዲያ ምን ሊባሉ።
ቢለዩ ቢለዩ አመትም አይቆዩ፣
ሁሉም ወንጀለኞች በእኩል አይን ይታዩ፣
ሌሎችንም ፍቱ ለምን ይሠቃዩ።
ችላ ከተባለ ደንቡ ህገ-መንግሥቱ፣
ሁሉም ክልል ያሉ በየ እሥር ቤቱ፣
ፍርድ ቢያገኙም እንኳን ይገባል ሊፈቱ።
የጁንቶች መፈታት እነ ሥብሀት ነጋ፣
ዛሬም ሠላማችን እንዳይረጋጋ።
ከማድረግ በሥተቀር ምንም የለው ዋጋ።

@terkagetm
@terkagetm
858 views18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-06 00:08:37 ፅናት



ክፍል ❶

ደራሲ ፅዮን መልካሙ



ፅናት እባላለው የምኖረው ሀዋሳ ከእናቴ ጋር ነው::
እናቴ አልኩአት ከናቴም በላይ ናት! ለሱአ የሚመጥን ቃል ሰላጣው
እናት ብዬ በ3 ፊደል ብቻ ገለፅኳት ለሱአ ሚመጥን ቃል እስካሁን
አልተፈጠረም እኔንጃ ሚፈጠርም አይመስለኝም
እማዬ ለኔ ሚስጥረኛዬ, ጉደኛዬ,ህይወቴ በቻ ብዙ ነገሬ ናት
አባቴ በአዕምሮ ካንሰር እኔ በተለድኩ በ1ወሬ ነበር የሞተው
አሰባቹት አደል ያባትን ጣዕም በልጅነት ማጣት እንዴት እንደሚከብድ?አው ያማል!!!
ግን እናቴ ይሄን ሁሉ ሸፍናልኛለች.አባትምእናትም ሆና አሳድጋኛለች
እሷን እየራባት እኔን ታበላለች ለሱአ ሳይመቻት ለኔ ምቾት ትጨነቃለች...እናቴ እኔን ስቶልድ ገና 18አመቱአ ነበር
አስባቹታል የራስን ለጅነት ሳይጨርሱ ልጅን ማሳደግ እንዴት
እንደሚከብድ? አው በጣም ይከብዳል እሷግን ምንም አይታክታትም ደከመኝ ሰለቸኝ አትልም.
የሰው ቤት ልብስ እያጠበች የሰው ፊት አየገረፋት ,እንጨትእየሸጠች ወገቧ እየጎረበጠ እንጀራ እየጋገረች ጪስ አይኑአን እያቃጠለ ከሰው በታች እራስዋን ዝቅ አድርጋ ደከመኝ ሰለቸኝ አመመኝ ቆረጠኝ ፈለጠኝ ሳትል እኔን ለዚ አብቅታለች እኔ አሁን የ12ክፍል መልቀቅያ ፈተና በከፍተኛ ነጥብ አልፌ ምደባ እየጠበኩ ነው እንግዲ ዛሬ ቅዳሜ ነው ያው ትምርት በሌለኝ ሰዓት ጉሊት እየሸትኩ እናቴን አግዛታለው እማ እኔ በቃለው ትለኛለች ግን እኔ አሻፈረኝ ብዬ ጉሊት መሸጡን ተያይዤዋለው እንግዲ ቁርስ ባይባልም ደረቅ ቂጣ በ ውሀ አወራርደን
አፋችንን አሟሽተን ከቤት ተያይዘን ወጣን እማ ወደ ልብስ አጠባ
እኔም ወደ ገበያ ሄድን እና ሁሌ ወደምቀመጥበት ቦታዬ አመራውና
ተቀመጥኩ እዚው ገበያ የተዋወኩአት አለም ምትባል ጉደኛዬ ሰላም አለችኝ
"ሰላም ፅኑ እንዴትነሽ"
"አግ/ር ይመስገን አልሚ"
"ሰኒ እንዴት ናት ወገብአን የሚያማት ተሻላት"አለችኝ አይ!የኔ ነገር ሳልነግራቹ ሰኒ(ሰናይት)የናቴ ስም ነው እናቴ ብዙ አመት እንጨት አየሸጠች ልብስም ሰለምታጥብ በተደጋጋሚ ወገቡአን ያማታል
"አው አሁን ደና ናት ጋሽ መዋኸኝስ እንዴት ነው ይንቀሳቀሳሉ"ጋሽ መዋኸኝ የአልሚ አባት ናቸው በጠና ታመው ከአልጋ ከተቆራኙአመታት አልፈዋል ከኔ በተቃራኒ እሷ ካባትዋ ጋርነው ምትኖረው እናትዋን በልጅነትዋ ነው በድንገት ያጣችው አልሚ እንደኔ እዚ አለምለይ
ለመቆየት ያቅምዋን እየፈጋች ነው ላያስችል አይሰጥ አይደል ሚባለው!!!
"አይ!ፅኑ ያባዬን ነገር እንዲ ብሎ መናገር ይከብዳል"አለችኝ እንባ ባዘለ ድምፅ
"ምነው አልተሻላቸውም"?
"መሻሉንስ ተሽሎታል ግን....የስኳርና የኩላሊቱን መዳኒትየዋጋ ን
ረት አልቻልኩትም በዚያለይ በየሳምንቱ ለchekup መሄድ አለበት
ለ ካርድ ብቻ የማወጣው...."ከዚበላይ መናገር አልቻለችም ማልቀሱን ተያያዘችው
"አይዞሽ አልሚ የምናሳልፈው ሁሉ ለበጎ ነው የኔንስ ታዋቂው የል
መች ጠግበን እናድራለን እማዬም ማታ እያመማት ምትታከምበት ስለ ሌለን ጠዋት ለስራ ቴዳለች እስኪ ዘይት የገባበት ምግብ ከበላን ቀናት ተቆጥረዋል..."ሳልጨርስ አንድ ድምፅ አቋረጠኝ
"ድንች ስጭኝ"የሚል የአንድ ሴት ድምፅ
"የስንት ?"
" የ20 ብር ስጪኝ መረቅረቅ አርገሽ"
ከሰጠዋት ብኅላ ከአልሚጋ ወሬያችንን ቀጠልን
"እና ምን አዲስ?"አልኳት
"ውይ የኔ ነገር ሳማርር ዋናውን ጉዳይ ረሳው ለኔም ላንቺም ህይወት ቀያሪ እድል አግንቻለው"
"ምን የምን እድል አልሚ"አልኳት ምትለውን ለመስማት እየቋመጥኩ.....


ይቀጥላል.....


ሼር ማድረግ አይርሱ!!!......
@terkagetm @terkagetm
713 views21:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-06 00:08:34
591 views21:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-31 10:35:54 ባሌ በ50 ብር ሸጠኝ !

ክፍል 15
.
.
#የመጨረሻ ክፍል
.
.
"ሰሞኑን ገንዘብ ከየት ነበር የምታመጪው?" እኔ አሁንም ዝም
"ዝምታ ካዋጣሽ እሺ" ብሎኝ ወደ መኝታ ቤታችን ገብቶ ተኛ። የሰውን ልጅ በድላችሁት ዝም
ከሚላችሁ ቢናገራችሁ ፣ ቢሰድባችሁ ፣ ቢመታችሁ ይሻላችኋል። ሶፋው ላይ በለሊት ብቻዬን ቁጭ
ብዬ የሲምቢሮዬ ሁኔታ አስጨነቀኝ። ያለ ልማዱ ዛሬ እንዴት ዝም ብሎኝ ሊተኛ ቻለ? እስከዛሬ
አንዳችን ባንዳችን ቅር ከተሰኘን ቁጭ ብለን ተነጋግረንበት ችግራችንን እንፈታው ነበር። ዛሬ በምን
ምክንያት ነው ዝም ብሎኝ ሊተኛ የቻለው? መቼም የሀበሻ አፍ ሰው ለማጣላት ሲሆን እንደ መርፌ
ይሾላልና አንዱ ጓደኛው አይቶኝ ነግሮት ይሆን እንዴ?.......አይ እሱ እንኳን አይሆንም ፤ ምክንያቱም
ቢዝነስ መስራት እንደጀመርኩኝ ቢያውቅ ሲጥ አድርጎ ይገድለኛል አሊያም አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ
ህሊናዬም ገላዬም ላይ የማይሽር ጠባሳ ጥሎብኝ ነበር የሚያልፈው!......እና ታዲያ ምን ሆንኩኝ
ብሎ ነው ፀባዩ እንደ ጠላ ቂጣ በድንገት የተገለባበጠው? ባዶ ግድግዳው ላይ ፍጥጥ ብዬ
ለሊቱን አነጋሁት። ያፈጠጥኩበት ግድግዳውም መልሶ አፈጠጠብኝ እንጂ ጭንቅላቴ መፍትሔ
አላገኘልኝም ነበር። እንደዚህ ብቻዬን መብሰልሰሌ ለውጥ እንደማያመጣ ስለገባኝ ወደ መኝታ
ቤታችን ለመሄድ ከተቀመጥኩበት ተነሳሁ። እግሬ ግን እሱ የተኛበት መኝታ ቤት ለመሄድ ድፍረቱን
አጣ። ዓይኖቹን ማየት ፈራሁኝ። እንኳን ዓይኖቹን አይደለም። ከፊት ለፊቴ ግድግዳው ላይ
የተሰቀለውን የተሸጠው ታክሲያችን ላይ የተነሳነውን ፎቶ ራሱ ቀና ብዬ ለማየት ፈራሁኝ። ተመሌሼ
ተቀመጥኩ። እዛው ሶፋው ላይ ተኛሁ።
ጠዋት እንቅልፌን ሳልጨርስ ሶፋው ላይ የተኛሁበት ወገቤን እያመመኝ እየተጨናበስኩኝ ነቃሁ።
የመኝታ ቤቱም የቤቱም በር ክፍት ሆኖ አየሁት። ለአቢ ጡቴን ላጠባው ስገባ የተኛበት አልጋ
ሳይነጠፍ አንሶላውና ብርድልብሱ መሬት ወድቆ አገኘሁት። ሲጋራ ሊገዛ ወጥቶ ይሆናል ብዬ
ስላሰብኩኝ እስኪመጣ ድረስ ቁርስ እየሰራሁ ልጠብቀው ቦርሳዬን ሳየው ተዘረጋግፏል የወዳደቁትን
ዕቃዎች መልሼ እየከተትኳቸው እያለ ማታ የሸቀልኩትን ብር አጣሁት። ያኔ ነገሮች በስሱም ቢሆን
እየገቡኝ መጡ። በርግጠኝነት ማታ እዛ ሚሚ ቂጦ ቤት የሱ የግሉ ብቻ የሆነውን ሴትነቴን ለጨረታ
ሳቀርብ ሚስቱ መሆኔን የሚያውቀኝ ሰው አይቶኝ ነገሮት ነው አመሉ የተለዋወጠብኝ ብዬ
ደመደምኩኝ። አድርጎት የማያውቀውንስ ቤቱ ውስጥ ምንም የሚቀመስ ነገር እንደሌለ እያወቀ ብር
ሰርቆኝስ መሄዱ ለምን አስፈለገው?
አሁን ደግሞ አእምሮዬን አዲስ ጭንቀት ተቆጣጠረው። በኔ ምክንያት ተስፋ ቆርጦ ራሱን ሊጎዳ
ይሆን? 'ጌታ ሆይ እኔ ብበድልህም ባልበድልህም ቅጣት ብርቄ እንዳይሆን አድርገህ ነውና
የፈጠርከኝ እኔኑ እንደፍጥርጥርህ አድርገኝ እንጂ አደራ ባሌን ክፉ እንዳታስነካብኝ' ብዬ እያየኝ
ለማይመለከተኝ እየሰማኝ ለማያዳምጠኝ ፣ እውር አሞራን እየቀለበ እኔን ለዘነጋኝ አምላኬ
ነገርኩት። በሌላ በኩል ደግሞ የሱን ፀባይ እስከማውቀው ድረስ ከሆነ በሰው ተበድሎ ከደረሰበት
ጉዳት በላይ በዳዩን ሳይበቀለው እንቅልፍ እንደማይወስደው ነው። ታዲያ ሲምቢሮዬ በኔ ላይ
ጨክኖ ከሌላ ወንድ ጋር አደረች ብሎ ሊጎዳኝ አስቦ ይሆን?........አይ......አይ........ኧረ
አያደርገውም!
ጭንቅላቴ አንዱን ሀሳብ እያነሳ አንዱን ደግሞ እየጣለ ሰዓቴን ስመለከተው አስር ተኩል ሆኗል።
እስከአሁን ድረስ ባሌ ከፍቶ የወጣውን በር ከፍቶ ተመልሶ አልገባም። እኔ ደግሞ ትናንት ምሳ
የበላሁ እስከአሁን ምንም ስላልቀመስኩ ሆዴ በረሀብ ሻፈደ። ለልጄ እንደገና ደረቅ ጡቴን
አጎረስኩት። ሲምቢርዬ ማታ ገብቶለት መጥቶ ይሰድበኛል ይጠፈጥፈኛል እኔም ሀጢያቴ ስለሆነ
ዝም እለዋለሁ ብዬ ስላሰብኩኝ የሱ ነገር ቀስበቀስ የሚያሳስበኝ መጠን ቀነሰልኝ።
ሆዴ ግን በረሀብ እንደ ወፍጮ ቤት ሞተር ሲጮህ በምን ላስታግሰው? አፌን መረረኝ። ተነስቼ
የመቆም ሀይል እንኳን አጣሁኝ። ጨጓራዬ የሚፈጨው አጥቶ እርስ በርሱ ተፋትጎ ጉሮርዬ ላይ
ጣፋጭ የሚያቃጥል አሲድ መርጨት ጀመረ። እንደምንም አካሌ ሀይል በማጣት ዝሎ መሸልኝ።
ሰውዬዬ እስከምሽቱ አንድ ሰዓት ድረስ አልመጣም።
እኔ ረሀቤን እንደ ምንም ችዬ ተኳኩዬ ሚኒዬን አድርጌ የደላት ሴት መስዬ ልጄን አክሱም ሆቴል
ጀርባ ላለችው አሮጊት ሰጥቼ ሰው ሰውን እንደሸቀጥ ወደሚሸምትባት ቺቺንያ ራሴን ወርውሬ
ዳይቭ ሰመጥኩኝ። ረሀቤን ቢያስታግስልኝ ብዬ ከአመታት በኋላ ከአንዱ ጀብሎ ሲጋራ ዱቤ ወስጄ
አጨስኩኝ። እንኳን ሊያስታግስልኝ የባሰ አዙሮኝ ያለችኝንም አቅም አሟጠጠብኝ። ወደ መጠጥ
ቤቱ ውስጥ ስገባ እንጠጣ እንጂ እንብላ የሚል ቃል ካፋቸው የማይወጣ ወንዶች
'ሪታ....ሪች.....ሪ .....ሪሃና....' ብለው እየጠሩኝ መጠጥ ለመጋበዝ ተሻሙብኝ። ይሄኔ መጠጥ
ከምትጋብዙኝ ባለ ብር ከሀያ
ዳቦ ግዙልኝ ብላቸው ፊታቸው እንደ ቫምፓየር ባንዴ ነበር የሚቀያየረው። ያው ያለነው ኢትዮጵያ
ውስጥ አይደለ? ራበኝ ብለህ አደባባይ ስቶጣ ይሄን ብላ ተብለህ ጥይት የምትጎርሰበት ሀገር ላይ
ሰውም ራበኝ ስትለው መጠጥ ጋባዥ ቢሆን ያን ያህል አይገርምም። ምክንያቱም ሁሉም አመዳም
ኑሮውን ከማስታወስ መደንዘዝን ይመርጣልና! እኔም ምንም አማራጭ የለኝምና አንዱ የቀነዘረበት
የመሰለኝን እሺ ብዬው አንድ ቢራ ከጠጣሁኝ በኋላ መውጫ ቆርጦ ለሾርት ይዞኝ ሄደ። አመሻሽ
ላይ ስራዬን ጨርሼ ወደ ቤት ሄድኩ።
እቤት ስደርስ ብዙም ሳልቆይ በሬ ተንኳኳ። ከፈትኩት። የታክሲ ሹፌር የሆነው የሱ ጓደኛ ጨርቅ
እስከሚሆን ድረስ ስክር ብሎ ቆሟል። በዚህ ሰዓት ቤቴ መምጣቱ እያወዛገበኝ 'ታዴ በሰላም ነው?'
ስለው ገፍተር አድርጎኝ ወደ ውስጥ ገባና በሩን ከውስጥ ቆለፈው። ይባስ ብሎ ሶፋው ላይ ጣለኝና
አስገድዶ ሊደፍረኝ ይታገለኝ ጀመር። 'ታዴ ምን ሆነሀል ሪች እኮ ነኝ!?' ብዬ ከላዬ ላይ ላነሳው ስል
፣ በተሟዘዘ የሰካራም ድምፅ "እኔም'ኮ ለዛ ነው የመጣሁት" 'እሱ የለም ብለህ ነው አይደል እንዲህ
የምትሆነው! ከሰማ ግን የገባህበት ገብቶ ነው የሚዘለዝልህ!!' "ሃሃሃሃሃሃሃ....ሃሃ..ማ? ኤልያስ
ነ...ው የሚመታኝ?
ሃሃሃሃሃሃሃ...ሃሃሃሃ.....ራሱ አይደል እንዴ ሚስቴን ሀምሳ ብር ክፈለኝና አብራቹ ተኙ ያለኝ" ልክ
ይሄንን ቃል ሲናገር መቶ ሀያ ሺህ መርፌዎች አእምሮዬ ላይ የተሰኩብኝ መሰለኝ......አናቴን
በዲጂኖ የተቆፈርኩ ያህል የላይና የታቹ ተገለባበጠብኝ......መላ ሰውነቴን ንዝርዝር
አደረገኝ........በሀምሳ ብር ከባሌ የገዛኝ ታደሰ ልብሴን ለማውለቅ ይታገላል.......እኔ ልክ
እንደልጄ የስሜት ህዋሳቶቼ በድን ሆነውብኝ ወደ ግዑዝ አካልነት ተቀይሬያለሁ በርግጥ ሲምቢሮዬ
እንደሚበቀልኝ እጠብቅ ነበር ፤ ለሰራሁ ሀጢያት ግን ደመወዜን ይሄን ያህል እጥፍ አድርጎ
ይከፍለኛል ብዬ ግን ለአንዲት ሰከንድም አስቤ አላውቅም...
.
.
.
ተፈፀመ

ታሪኩ ይሄ ነበር...........

@terkagetm @terkagetm
624 views07:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ