Get Mystery Box with random crypto!

ጠባሴ ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ tebasemidea — ጠባሴ ሚዲያ
የቴሌግራም ቻናል አርማ tebasemidea — ጠባሴ ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @tebasemidea
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 177
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ሚዲያ ለጥበበኞች የተከፈተ
:- ግጥሞች
:- ሙዚቃ
:-ፎቶ ግራፍን ጨምሮ
የተለያዩ መዝናኛዎችን ሁሉን በአንድ የሚገኝበት ቻናል ነዉ
📚📝📖 የተሻለ ትውልድ ለተሻለች ኢትዮጵያ!!

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-10-19 20:16:56 እኖር ብዬ ብታረድም
ለመኖር ስል ብሰደድም
እኖር ብዬ ብዋረድም
ዘጠኜ ሞቴን ብሞተው ፣ አንዴ እንደመኖር አይከብድም!
መኖር ከመምት አይልቅም
ሞት እንደ መኖር አይጨንቅም፡፡
………………………………
የሞተ ‹‹እሞታለሁ›› ሲል…
በጭራሽ አያውቅም ፈርቶ፡፡
ያልኖረ አያውቅም ሞቶ።
።።።።
መኖር እንጂ የሚያስፈራኝ
መኖር እንጂ የሚያስገፋኝ
መኖር እንጂ የሚያስከፋኝ
መኖር እንጂ የሚበድል
መኖር እንጂ የሚያጎድል
ሞት አያምም ፣ ሰው ሲገድል!
5.0K views ☞net, 17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-17 20:21:47 From D.MEHRET DEBEBE


የራስህን ሩጫ ሩጥ

ሚዳቋ በጠዋት ተነስታ ለግጦሽ ትሰማራለች፡፡ በዕለቱ ሊበላት ከሚፈልግ አንድ አንበሳ በፈጠነ ሁኔታ ካልሮጠች ተበልታ አንደምትሞት ታውቀዋለች፡፡ አንበሳም ቢሆን በራሱ በጠዋት ተነስቶ ለአደን ይሰማራል፡፡ የእለቱ ራት እንዳያደርጋት ሚዳቆዋ ስትሮጥ አንበሳው ከእሷ በፈጠነ ሁኔታ ሮጦ ካልደረሰባትና ካልያዛት በረሃብ እንደሚሞት ያውቀዋል፡፡

ሚዳቋዋ ራሷን በንቃት በመጠበቅ አንበሳው ሊበላት ሲመጣ ከእርሱ በፈጠነ ሁኔታ ሮጣ ከማምለጥ ይልቅ፣ “ፈጣሪ ለምን በሰላም እንዳልኖር አንበሳ የሚባል ፈጠረ . . . አንበሶች ግን ምን አይነት ክፉዎች ናቸው? ምናለበት ቢተውንና አርፈን ብንኖርበት . . . ሌሎች ሚዳቆ ዘመዶቼ ግን እንዴት ጨካኞች ናቸው ገና አንበሳ ሲመጣ ለማንም ግድ ሳይሰጣቸው ሮጦ ማምለጥ ነው ትዝ የሚላቸው . . .” እያለች ቆማ ብትነጫነጭ በአንበሳው ከመበላት አታመልጥም፡፡

አንበሳም በበኩሉ የቻለውን ያህል ሮጦ ሚዳቆዋን አባሮ ከመብላት ይልቅ፣ “ፈጣሪ እንደዚህ ከምለፋ ምናለበት እየረጋገጥኩት የማልፈውን ይህንን ሳር-በሊታ አድረጎ ቢፈጥረኝ . . . ሚዳቆዎች ግን ምን አይነቶ ናቸው? እነሱ የትም የምይንቀሳቀስ ሳር እየበሉ፣ እኛን ግን ያሯሩጡናል . . . አንበሳ ዘመዶቼን ግን ታዘብኳቸው፣ ለራሳቸው ተሯሩጠው አድኖ ከመብላት ውጪ ለሌላው አንበሳ ረሃብ ትዝም አይላቸው . . .” እያለ ሲነጫነጭ ቢውል በረሃብ ከመሞት አያመልጥም፡፡

አንዳንድ ሰዎች ማን ምን እንዳደረገላቸውና እንዳላደረገላቸው . . . ማን ምን እንዳደረገባቸውና እንላደረገባቸው . . . ይህቺ አለም ምን ያህል ፍትህ እንዳልሆነች . . . ሁሉም ሰው የራሱ ጉዳይ ብቻ ግድ እንደሚለው . . . እና የመሳሰሉትን ሲያሰላስሉና ሲያወሩ መኖር እንደሚያስቀድም፣ ወደኋላ እንደሚያስቀርና አንዳንዴም እንደሚያስበላ ከገባቸው ቆይተዋል፡፡ ስለዚህም የራሳቸው ሩጫ ላይ ያተኩራሉ፡፡

እንደዚህ አይነት ሰዎች የዚህች አለም ጉዳይ በደንብ የገባቸው ሰዎች ናቸው፡፡ እነሱ ካልሮጡ ማንም እንደማይሮጥላቸው፣ እነሱ ካልሰሩ ማንም እንደማይሰራላቸው፣ እነሱ ቀዳዳቸውን ካልደፈኑ ማንም እንደማይደፍንላቸው . . . በሚገባ ያውቁታል፡፡ በዙሪያቸው ያለው አለም ፍትህ-ጎደል የመሆኑን ጉዳይ በሚገባ ቢያውቁትም፣ የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ቀዳዳ የመድፈን ሙሉ ሃላፊነቱ የራሳቸው እንደሆነ በሚገባ ያውቁታል፡፡ ስለሆነም፣ በዙሪያቸው ያለው ፍትህ-ጎደል ሂደት ቢታወሳቸውም የራሳቸውን ሩጫ ከመሮጥ አይገታቸውም፡፡

ምንም ያህል ብትጠይቅ አንዳንዴ የማይመለሰ ጥያቄ ሊኖርህ እንደሚችል ይግባህ፡፡ ምንም ያህል ብትጮህ አንዳንድ ጊዜ ማንም የማይሰማው ጩኸት እንዳለህ ተገንዘብ፡፡ ምንም ያህል ቆመህ ብትጠብቅ አንዳንዴ ማንም ሰው ሊደርስልህ የማይችልበት (ወይም የማይፈልግበት) ሁኔታ እንዳለ ተረዳ፡፡ ጨዋው ሰው የራሱን ጣጣ ከጨረሰ በኋላ ወደ አንተ ዘወር ሲል ጊዜው ያልፋል፡፡ ሌላው ደግሞ ለማንም ደንታ የማይሰጠው አይነት ስለሆነ ትዝም አትለውም፡፡

ያለህ አስተማማኝ መንገድ ጠዋት ተነስተህ ልክ እንደሚዳቆዋ ሊይዝህ ከሚፈለግ ሁኔታ ለማምለጥ፣ ልክ እንደ አንበሳው ደግሞ መያዝ የሚገባህን ለመያዝ መሮጥ ነው፡፡
መልካም ምሽት
ሼር
@tebasemidea
@tebasemidea
419 views ☞net, 17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-15 22:27:45 https://telegram.me/tebasemidea
2.4K views ☞net, 19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-12 22:08:44 ዛሬ አንድ መጽሐፍ እንሆ ልበላችሁ

ባዓሉ ግርማ´´´

የበዓሉ ግርማን የፍቅርና የትዳር
ሕይወት በጨረፍታ ሲዳሰስ ደግሞ የሚከተለዉን መስሎ አግኝቼዋለዉ። ፍቅርን የሚዘምሩ ፡ ዉበትን የሚያዘምሩ ሴት ገፀባህርያትን መፍጠር የሚሆንለት በዓሉ ፣ እሱ እራሱ ተንበርካኪ ነዉ - ለፍቅር።

እሱ እራሱ እንደ ወንድ ገፀባህርያቱ ቆንጆ ሴት ካጋጠመችዉ አድናቆቱን ፊት ለፊት ለመግለፅ ቃላት የማይሰስት ነፃ ሰዉ ነዉ። በምን ይሉኝ ጠፍር ልቡንም ፡ ምላሱንም ፡ ገላዉንም ፡ ብዕሩንም ያሰረ አይደለም። ወዳጅ ነዉ ፡ ተወዳጅም ጭምር!

በተማሪነት ዘመኑ ፡ አልፎ አልፎ ፡ ከግቢ እየወጣ ይዝናና ነበር። ለማፍቀርም ፡ ለመፈቀርም ጊዜ ነበረዉ´´ ሲባል ሰምቻለዉ። ስለ ወጣትነት የፍቅር ሕይወቱ ያዉቅ እንደሆነ ብዬ ኢየሱስወርቅ ዛፉ{አሁን ላይ በፋይናንስ ዘርፍ ላይ ይሳተፋሉ እንዲሁም ህብረት ባንክ ቦርድ ዉስጥ ይሰራሉ} ጠየቅሁት :-

…ሚስት ከማግባቱ በፊት ድምፃዊት ብዙነሽ በቀለ ገርል ፍሬንዱ ነበረች ፡ በጣምም ይወዳት ነበር። እሷም እንዱሁ። ከአንዴም ሁለት ሶስት ጊዜ ጋብዞኛል እሷጋ። እና ፡ ራስ መኮንን ድልድይ ፡ ከድልድዩ ወደ አራት ኪሎ ስትሄድ ፡ በስተቀኝ በኩል ፡ ቤንዚን ማድያዉጋ ስትደርስ አንድ ግቢ ነበር- እንደ ፔንሲዮንም ፣ እንደ ሆቴልም የሚያገለግል። ብዙነሽ ብዙዉን ጊዜ እዚያ ትዉል ፡ ታመሽ ነበር - ትዝ ይለኛል ፡ በደንብ ዶሮ ሰርታ ፡ ምን ብላ ምን ብላ ጋብዛናለች።

በዓሉ ከብዙነሽ ጋር ስለነበረዉ ቀረቤታ ቀደም ሲል ሰምቼ ነበር። አንድ አንጋፋ ደራሲና ተርጓሚም ''ሁለቱ እጅ ለእጅ ተያይዘዉ ፡ እንደ ጣልያኖቹ…… በየመንገዱ ሲላፉ ፡ ሲሳሳቁ ፡ በሚያስቅና ስሜት ሆነዉ በርጋታ ወክ ያደርጉ እንደነበር ሁልጊዜ ትዝ ይለኛል - የእሷን ዘፈን በሰማሁ - የሱን መፅሐፎች ባነበብኩ ቁጥር'' ብሎኛል።


በዓሉ በኢትዮጵያ ሬድዮ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ዜና አንባቢነት ተቀጥሮ ይሰራ በነበረበት በ1950ዎቹ አጋማሽ ፡ የሬድዮ ቴክኒሽያን በመሆን አገልግሎት ይሰጥ የነበረ ፡ ኪሮስ ወ/ሚካኤል የተባለ የስራ ባልደረባዉም ፡ `እዉነት ነዉ´´ ብሎኛል።



መ ል ካ ም ን ባ ብ……

የቀረዉን ለእናንተ ትቻለዉኝ…


የመፅሀፉ ርእስ - በዓሉ ግርማ ሕይወቱና
. ስራዎቹ

የመፅሀፉ ደራሲ - እንዳለጌታ ከበደ

የገፅ ብዛት - 440 ገፆች

ዋጋ - 120 ብር



ኑ የቆምንበትን መሠረት እንፈትሽ!

የተሻለ ትውልድ ለተሻለች ኢትዮጵያ!!
348 views ☞net, 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-10 09:53:41 ያለቀጠሮ የሚኖር አለ?

ሁሉ ሰው ለነገ ያስባል፡፡ የመጨረሻው ግድ የለሽ ነኝ ባይ ነገን እያሰበ ይጨነቃል፡፡ እንቅልፍ ይነሳዋል፡፡ ዛሬ ማንም ሰው ሲተኛ ነገ እንደሚነቃ ጠብቆ ነው፡፡ እራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎች እንኳን ነገን አስበው ነው--ነገ እንደማይቀናቸው አስበው ነው--የነገውን ቀና ቀጠሮ እንደማይሰምር ተሰምቷቸው ነው፡፡ ለነብሴ አደርኩ የሚሉ ቅዱስ እንኳን ነገ ፣ ከነገ ወዲያ መምጫው የማይታወቅ እግዚያብሔር በመንግስቱ እንዳይረሳቸው ይመኛሉ......ዛሬ ደግ ይሠራሉ ፣ ዛሬ ይራባሉ ፣ ዛሬ ይጠማሉ ፣ ዛሬ ይቀድሳሉ ፣ ይዘምራሉ ፣ ዛሬ ይመፀውታሉ ፣ ዛሬ ዛሬ ደግ ይናገራሉ፡፡ ጉንዳንና ነፍሳት ዛሬ በዚህ በጋ ለፍተው ማስነው ለክረምት መኖአቸውን ይደብቃሉ፡፡ መንቆረሪቶችና ጉርጦች በጋ ሲመጣ አፈር ለብሰው ከርመው በጋ አልቆ ጠል መውረድ ሲጀምር ከተኙበት ይነሳሉ፡፡ ነገ የሚዘነጋ አደለም፡፡ ነገ ለዓለም ህዝብ ሕመም ነው፡፡ ከፕሬዝዳንት እስከ ለፕሬዝዳንት እስከሚያጨበጭበው፡፡ ከሰው እስከ እንስሳት የነገ ነገር የማያብሰለስለው የለም፡፡ ቢለያይ <<የነገዎች>> እርዝመት ነው፡፡ ቢለያዩ ሊሰየም በሚከብድ ደረጃቸው ነው እንጂ የነገ ነገር የማያስደነግጠው የነገ መምጣት የማያባባው የለም፡፡

አዳም ረታ
ግራጫ ቃጭሎች
#ሰናይ_ሰንበት

@tebasemidea
@tebasemidea
@tebasemidea
4.1K views ☞net, 06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-08 22:18:59 ሰው ምንም ቢበድልህ ፣ ቢያስከፋህ ፣ ቢጠላህ በአፈጣጠሩ ብቻ ውደደው! ምክንያቱም ሰውን የአምላኩ አምሳል እና እንዳ'ንተ ድንቅ ፍጡር ስለሆነ ብቻ ልትወደው እንጂ ከተፈጠረ በኋላ ያደረገውን መጥፎ ተግባር እያነሳህ ልትጠላው የተገባ አይደለምና!

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ሰውን ስትወድ አምላክህ ይቀርብሀል ፤ ሰውን ስትጠላ ከአምላክህ ትርቃለህ!

                                           
383 views ☞net, 19:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-05 15:15:36 #ኩረጃ
በህንድ ሲም የሚቀበል ነጠላ ጫማን ለኩረጃ ሊያውሉ የነበሩ ተፈታኞች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በህንድ ራጃስታን ግዛት ከዚህ ቀድም ከፍተኛ ጥቅም ያስገኛል የተባለውን የመምህራን ፈተናን ለመስጠት በሚል ኢንተርኔት ቢቋረጥም የኩረጃ መልኩ ተቀይሯል።ነጠላ ጫማን በብሉቱዝ በማገናኘት ፈተናውን ቀድመው ተፈትነው የወጡ ተፈታኞች ውስጥ ላሉ ጓደኞቻቸው መልስ እንዲነግሩ ተደርጎ ተመቻችቷል።

በዚህም መሰረት ነጠላ ጫማው ሲም የሚቀበል ሲሆን በአይን ለማየት እጅግ አዳጋች የሆነ ቀጭን የጆሮ ማዳመጫ በጆሮዋቸው በማድረግ ወደ መፈተኛ ክፍል ያመራሉ።አንዳንዶቹ የጆሮ ማዳመጫውን በጊዜያዊነት በጆሮዋቸው ውስጥ ለማስቀበር ሲሞክሩ እንደነበረም ተሰምቷል።ከውጪ ስልኩ ሲደወልላቸው በእግር ጣታቸው ስልኩን ያነሳሉ።

ለአንድ ነጠላ ጫማ 600ሺ ሩፒ ወይም 8ሺ ዶላር ይጠየቅበታል።በዚህ ድርጊት እጃቸው አለበት የተባሉ አደገኛ ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር ውለዋል።ህንድ ተፈታኞች ነጠላ ጫማ አድርገው ወደ መፈተኛ ክፍሎች እንዳይገቡ ከልክላለች። (ዳጉ ጆርናል/Simon Dereje)

ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://telegram.me/tebasemidea
542 views ☞net, 12:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-02 19:58:25 ከማንም ምንም ነገር አትጠብቁ፡፡ከራሳችሁ የምትጠብቁት ግን ከዳሽን ተራራ የገዘፈ ነገር ይሁን፡፡ራሳችሁን ትልቁን አላማ የሚያሳካ ሰው አድርጉ፡፡የሚጠቅማችሁን ነገር በሙሉ ተማሩ፡፡በትልቁ ለመማር ምስጢሩ በትልቁ መሳሳት እንደሆነ እወቁ፡፡ክህሎታችሁን አዳብራችሁ ተዓምር የሚሰራ ሰው ምሰሉ፡፡
የምታወሩት ነገር በስራችሁ መደገፉን አረጋግጡ፡፡በውስጣችሁ ያለውን ቆሻሻ ሀሳብ አውጥታችሁ ጣሉት፡፡ጽድት ያለ ነገር ብቻ ወደ ህይወታችሁ አስገቡ፡፡ለጊዛዊ ጥቅም ቋሚ ነገራችሁን አታበላሹ፡፡
የራሳችሁ ምርጥ ሁኑ!
@tebasemidea
@tebasemidea
@tebasemidea
765 views ☞net, edited  16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-02 13:43:58 እህታችን ላይ በህጻን ልጇ ፊት ነውረኛ… ጨካኔና… አረመኔያዊ ተግባር የፈጸሙት ፖሊሶች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውንና ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገባቸው ስለመሆኑ የሰላም ሚንስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል መናገራቸው ተዘግቧል።
347 views ☞net, 10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ