Get Mystery Box with random crypto!

ጥበብ በእርስው

የቴሌግራም ቻናል አርማ tebabbeafetary — ጥበብ በእርስው
የቴሌግራም ቻናል አርማ tebabbeafetary — ጥበብ በእርስው
የሰርጥ አድራሻ: @tebabbeafetary
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 165

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-11-15 04:42:57 .        ህዳር 6 ቁስቋም__ማርያም

    እንኳን እመቤታችን ከስደት ተመልሳ ቁስቋም የገባችበት በዓል ቀን በሰላም አደረሳችሁ

   ህዳር 6 ፦ በዚህች ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ አንዲሁም ከዮሴፍና ሶሎሜ ጋር 3 ዓመት ከ 6 ወር በስደት ከተንገላታች በኋላ ወደ አገራቸው የተመለሱበት ቀን ነው፤

    ከግብጽ ሲመለሱ ጌታችን በእመቤታችን ጀረባ ላይ ሆኖ እነዚያ እውራንን ባበሩ ጣቶቹ ወደ ኢትዮጵያ ይጠቁም ያመለክት ነበር፤ እመቤታችንም ልጄ ሆይ ለምንድነው ጣትህን የምታመለክተው ብትለው "ያቺ የተባረከች አገር ናት እኔን የሚያመልኩ አንቺን የሚማልዱ በፍቅርሽ የነደዱ ቅዱሳን መነኮሳት የሚፈልቁባት አገር ናት፤

    ያንቺ ዘመዶች ሰቅለው ይገድሉኛል በዚህች አገር ያሉ ግን ሳይዩኝ ያመኑኛል፤ አስራት በኩራትሽ ትሁን ብሎ ሰጥቷታል፡፡

    በኪደተ እግራቸውም ጣና ሐይቅን፤ ዋልድባንና ሌሎችንም ቦታዎች ዞረው እንደባረኩ ድርሳነ ኡራኤልና ተአምረ ማርያም ላይ በስፋት ተጽፏል፡፡

    እመቤታችንን ከሐና ማህጸን ፈጥሮ ከፍጥረተ ዓለም ለይቶ ከሁሉ አልቆ የእናት አማላጅ ትሁናችሁ ብሎ የሰጠን እግዚአብሔር ይመስገን።

    ዳግመኛም በዛሬዋ ቀን በኢትዮጵያ ምድር ታላቅ አምድ ወደቀ ይህም የመናገሻው ባህታዊ አባ ኤልያስ ነው፤ በ 400 ዓመት እድሜው ህዳር 6 1874 ዓ/ም አረፈ፤ በአጼ ምኒሊክ ዘመነ መንግስት ማለት ነው፤ የቅርብ ጊዜ ነው፤ ይህ አባት በግራኝ መሐመድ ወረራ ጊዜ የነበረ ነው፤ በዚያን ጊዜ በተለይ ኦሮሞዎች "አያና ውቃቢ" እያሉ በጣም ያከብሩት ነበር፤ ከመናገሻ እንጦጦ ኪዳነምሕረት እየተመላለሰ ሱባኤ እየገባ ጸሎት ያደርግ ነበር፤ በዛሬዋ ቀን ይህ አባት ሲሞት በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ከዋክብት ሲበታተኑ ሲራወጡ ታየ የተጉለቱ አባ በላይነህም ይህንን ምልክት አይቶ የአባ ኤልያስን መሞት ተረዱ ወደ መናገሻ ቢመጡ ሞቶ ተቀብሮ አገኙት፤ጎንደር ላይም በተመሳሳይ ከዋክብት ሲበታተኑ እነ አለቃ ወልደ ቂርቆስ በአይኔ አየሁ ሲሉ መስክረዋል ይላል መርስሄ ሐዘን ''ትዝታዬ ስለራሴ የማስታውሰው" በሚለው መጽሐፋቸው የከተቡልን።

    የሚገርመው ይህ አባት ከቤተመንግስት ወገን ሲሆን ተድላ ደስታን ንቆ 400 ዓመት በቅድስና በተጋድሎ የኖረ መናገሻንና እንጦጦ ኪደነምሕረትን በጸሎቱ የባረከ ይህንን የመሰለ ቅዱስ አለመዘከሩ ታሪኩ አለመጻፉ የታሪክ ጸሐፍት ወዴት አሉ ሊቃውንቱስ ወዴት ተደበቁ ያሰኛል፤

    ከእመቤታችንንና ከመናገሻው አባ ኤልያስ በረከት ያሳትፈን። አሜን !!!
25 views01:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-13 23:26:27 ☞ወር በገባ በ4 የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሙሴ(ዘዲባ) ወርሐዊ መታሰቢያቸው
ነው፡፡
☞አቡነ ሙሴ ዘድባ የትውልድ አገራቸው እስራኤል ልዩ ቦታው ቃና ዘገሊላ ነው፡፡
☞ወደ ግብፅም መጥተው በታላቅ ተጋድሎና በንግሥና ኖረው እንደ ሄኖክና
ኤልያስ በምድር ላይ ሳይሞቱ በሞት ፋንታ የተሰወሩ አባት ናቸው፡፡
☞ብፁዓዊ አቡነ ሙሴ በአባታቸው የእመቤታችን ጠባቂ የሆነው የአረጋዊው
የቅዱስ ዮሴፍ የልጅ ልጅ ሲሆኑ ፡፡
☞በእናታቸው በኩል ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር በቃና ዘገሊላ ሰንግ
የተገኙበት የዮካን ልጅ የዶኪማስ ልጅ ናቸው፡፡
☞የአባታቸው ስም ቅዱስ ዮስጦስ ሲባል የእናታቸው ስም ጵርስቅላ ይባላል፡፡
☞ሁለቱም መካኖች ሆነው ከኖሩ በኃላ በቅዱስ ገብርኤል አብሣሪነት ታህሳስ 8
አቡነ ሙሴ ተወለዱ፡፡
☞በዚህች ቀን ከእናታቸው እቅፍ በመውረድ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ
ምስጋና ይሁን ከጨለማ ወደ ብርሃን ላወጣህኝ አምላክ ብሎ ፈጣሪያቸውን
አመግነዋል፡፡
☞40 ቀናቸው ሐዋርያ ጴጥሮስና ያዕቆብ ፊሊጲስ እንድርያስ ሆነው ጥር 17ቀን
ክርስትና አነሷቸው፡፡
☞ወላጆቻቸው ለቤተክርስቲያን ሰጧቸው ቅዱስ ፋኑኤል ቅዱስ ዮናኤልም
ሰማያዊ ኅብስት እያመጡ ይመግቧቸው ነበር፡፡
☞ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ የቤተክርስቲያን ትምህርት አስተምሮ ድቁና
የሾማቸው፡፡
☞ብፁዓዊ አቡነ ሙሴ ወገባቸውን ከጠጉር በተሠራ መታጠቂያ በመታጠቅ
አቡነ ዘበሰማያት በጀመሩ ጊዜ ሰባቱ ሰማያት ተከፍቶላቸው ከአጋዕዝተ ዓለም
ሥላሴ ጀምሮ ሁሉንም ቅዱሳን በግልፅ ያያሉ ፡፡
☞በግብፅ 40 ዘመን ነግሠው ሳለ ንግሥናቸውን ትተው በመመንኮስ እልፍ
መነኮሳትን አስከትለው ወደ ሀገራችን ኢትያጵያ መጥተው እንደ ላሊበላ ያሉ 16
አሰደናቂ ፍልፍል ቤተ መቅደሶችን አንጸዋል፡፡
☞ወደ ኢትያጵያ ይዘው ከመጡት ብዙ መጻሕፍትም ብዙዎቹን ከአረብኛ ቋንቋ
ወደ ግእዝ ቋንቋ ተርጉመው ጽፈዋል፡፡
☞በአጠቃላይ በመላው ዓለም ዐሥር ሺህ ቤተክርስቲያን በኢትያጵያ ከአምስት
መቶ በላይ የዋሻ የሕንጻ ቤተክርስቲያን ሠርተዋል፡፡
☞በአቡነ ሙሴ በኢትዮጵያ ከታነጹ የዋሻ ቤተ መቅደሶች ውስጥ የድባ መቅደስ
ማርያም አቡነ ሙሴ አንድነት ገዳም አንዱ ነው፡፡ የዚህ ገዳም መሥራች
ብፁዓዊ አቡነ ሙሴ ናቸው፡፡
☞ጻድቁ የድባ መቅደስ ማርያም ሲደርሱ ድባ የምትባል አውሬ ያገኛሉ ልክ
እንደሰው አውርተው ይህ ቦታሽ አይደለም ሲሏት ቦታውን ትታ ወጥታ ሄደች
የቦታው ሥያሜም ያገኘው ከዚህ አንጻር ነው፡፡
☞የቤተ መቅደሱን የዋሻ ቤተክርስቲያን መስከረም 20 ቀን በሦስት ሰዓት
ውስጥ ተሠርቶ ተጠናቆ መስከረም 21 ቀን ሥሉስ ቅዱስ ባርከውላቸው
ተቀድሷል፡፡
☞በዚሁ ገዳም ውስጥ አባታችን ከጌታችን ቃል ኪዳን ከተቀበሉ በኀላ
መስከረም 4ቀን ተሰውረዋል፡፡
☞ይህ የጻድቁ አባታችን ከዳም ከተመሠረተ ከአንድ ሺህ ስድስት መቶ ዕድሜ
በላይ ያስቆጠረ ሲሆን በዚህ ዋሻውጥ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሙሴ የእጅ
መስቀላቸው በትረ ሙሴአቸው፤ ጥንታዊ የብራና መጻሐፍት ይገኛሉ፡፡
☞ጻድቁ አቡነ ሙሴ በኢትዮጵያ ካነጿቸው ውስጥ☞ ዋሻ ማርቆስ ከመቅደሱ
ጸበል የሚቀዳ(መቄት) ፤ደብረ ናዙኝ ማርያም (መቄት)፤ አዲስ አምባ
መድኃኒዓለም(መቄት)፤ ዶቃ ደብረ ሲና ሚካኤል (ደቡብ ዉሎ ማሻ ወረዳ) ፤
ወልደ ነጓድጓድ ቅድስ ዮሐንስ(ዋድላ) ፤ጠርጠሪያት ቁስቋም ማርያም( ሰሜን
ወሎ ዳውንት)፤ አርባዕቱ እንስሳ (ሰሜን ወሎ ዳውንት) ውቅሮ ቅዱስ ጊዮርጊስ
(ጋይንት) ከብዙ በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
☞ጸሎቱና በረከቱ ከእኛ ጋር ይሁንና ብፁዓዊ አቡነ ሙሴ ያደረገው ተአምር ይህ
ነው፡፡ ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ጋር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
☞በአንዲት ዕለት እንዲህ ሆነ በአባታችን በአቡነ ሙሴ መቃብር ቦታ ከዕለታት
በአንድ ቀን ከላዩ ከቤተ ክርስቲያኑ ከዋሻው ተልጦ ትልቅ ድንጋይ ወረደ፡፡
☞የጻድቁን ዝክር የሚዘክሩበት አንድ ቤተ በቤተክርስቲያኑ ስር ነበር፡፡
በውስጡም ለአቡነ ሙሴ የበዓል ዝክር የተጠመቀ በጋን የሞላ ጠላ ነበር፡፡
☞ድንጋዩም ከላይ ወርዶ ቤቱን ሁሉ አፈረሰው፡፡ ለበዓሉ መታሰቢያ ያዘጋጁበትን
ጋኑ ግን ለምልክት ይሆን ዘንድ ጆሮውን ከመሽረፋ በስተቀር አልተሰበረም፡፡
☞ያ ታላቅ አዳራሽ የሚያህል ቋጥኝ ድንጋይ በሱ ላይ አርፎ እሱንም አብሮ
በሰበረው ነበር ተአምምራቱ ለመግለጽ ነው እንጂ፡፡
☞ይልቁንም በውስጡ ያለው ጠላ ሳይፈስና ጋኑም ሳይሰበር መገኘቱ ለአባ
ሙሴ ለተአምራት ነው እንጂ አንዲት የእሳት መጫሪያ ገልስ እንኳ ባልተገኘም
ሰብሮ አፈር ትቢያ ባደረገው ነበር፡፡
☞በአባ ሙሴ በተአምራቱ ኃይል አዳነው እንጂ፡፡
☞የአቡነ ሙሴ ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን፡፡
☞(ገድለ አቡነ ሙሴ)
10 views20:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-13 01:32:24 01-ልደታ/ራጉኤል/በርተሚዮስ/ኤልያስ
02-ታዲዮስ ለዋርያ/እዮብ/አቤል
03-በአታ/ነአኩተለአብ/ፋኑኤል/ዜና ማርቆስ/አባ ሊባኖስ
04-ዩሀንስ ወ.ነጎድጓድ/እንድርያስ/አባ መልከ ጻዲቅ/አብርሀ ወአጽብሀ
05-ገ.መንፈስ ቅዱስ/ጴጥሮስ ወጳውሎስ
06-እየሱስ/ማርያም መቅደላዊት/አርሴማ/ቁስቋም
07-ስላሴ/ኢያቄም/ዲዮስ ቆሮስ/አትናቲዮስ
08-አርባአቱ እንስሳ/አባ ኪሮስ
09-እስትንፋሰ ክርስቶስ/ቶማስ ዘመርአስ
10-ጸደንያ ማርያም/መስቀለ እየሱስ/ተቀጸል ጽጌ
11-ቅዱስ ያሬድ/ቅድስት ሀና
12-ቅዱስ ሚካኤል/ቅዱስ ላሊበላ/ማቲዎስ/ዩሀንስአፈወርቅ/ማቲዎስ/አባ ሳሙኤል/ዲሜጥሮስ
13-ቅዱስ ሩፋኤል/እግዛቤር አብ/አቡነ ዘርአ ብሩክ
14-አቡነ አረጋዊ/ገብረ ክርስቶስ
15-ህጻን ቂርቆስ ሰመአት/ናትናኤል ሀዋርያ/ኤፍሬም ሶርያዊ
16-ኪዳነምህረት/ቅድስት እየሉጣ
17-አባ ገሪማ/ቅዱስ እስጢፋኖስ
18-ፊሊጶስ ሀዋርያ/ሰበር አጽሙ ለጊዮርጊስ
19-ቅዱስ ገብርኤል
20-ህንጸተ ቤ.ክርስትያን/ዩሀንስ ሀጺር/ኤልሳ ነብይ
21-ቅድስት ድንግል ማርያም/እዝራ ሱቱኤል
22-ቅዱስ ኡራኤል/ሉቃስ/ደቀስዮስ
23-ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰመአት
24-ተክለ ሀይማኖት/ሙሴ ጻሊም/ክርስቶስ ሰምራ/አባ ጎርጎርዮስ/24ቱ ካህናተ ሰማይ
25-ቅዱስ መርቆርዮስ/
26-ዮሴፍ የእመቤታችን ጠባቂ/አቡነ ሀብተ ማርያም
27-መድሀኒያለም/አባ መባ ጺሆን
28-አማኑኤል/አብርሀም/ይስሀቅ/ያዕቆብ
29-በአለ ወልድ/ተፈጻሜ ሰምአት ጼጥሮስ
30-መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዩሀንስ/ማርቆስ ወንጌላዊ

    ቤተሰቦች ሆይ እነዚህ ከተዘረዘሩት ውጪ ሌሎች ድርብ በአላት አሉ።

(የጻድቃን_መታሰብያ_ለበረከት_ነው) ምሳሌ 10;17
(የጻድቃን_መታሰብያ_ለዘላለም_ይኖራል) መዝሙር111
30 views22:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-11 20:15:36
26 views17:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 21:28:29
27 views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 21:28:19
27 views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 07:07:05
57 views04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 07:07:02
53 views04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 07:06:58
49 views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 07:06:54
46 views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ