የአማራ ብሄርተኞች ተከፋይ ተሳዳቢ አቶ ታዲዮስ ታንቱ ══════ . በአማራ ብሄርተኞች ❝እውነተኛ የታሪክ ምሁር❞ ተብለው የሚወደሱትና ኢትዮጵያውያንን እንዲሳደቡ ገንዘብ ተዋጥቶላቸው በየመድረኩ የሚጋበዙት ነውረኛው አቶ ታዲዮስ ታንቱ በምኒልክ ቲቪ ባቀረቡት አንድ ፕሮግራም ለጋዜጠኛ አዲሱ ደረበ ኢትዮጵያን ከሀ እስለ ፐ የሠራት አማራ እንደሆነ ካስረዱት በኋላ ሌሎችን ሲያጥላሉ እንዲህ አሉት… . ——— ❝በዓመት አንድ ጊዜ ገላቸውን የማይታጠቡ አያት ቅድም አያቶቻቸው ተስማምተው የኖሩባት ኢትዮጵያ እነሱ ዛሬ በቀን ሁለት ጊዜ ሻወር ስለወሰዱ መበታተን አለባት?❞ ——— . አስቡት እንግዲህ ከአማራ ውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ❝በዓመት አንድ ጊዜ ገላቸውን የማይታጠቡ❞ ሲሉ መውረፍ ምን ያክል አሳፋሪ እንደሆነ? . እርግጥ ሰውየው በሚዲያ ቅሌት የሚታወቁ በመሆናቸው ከዚህም የባሰ ሲናገሩ ኖረዋል። የሚገርሙኝ ይህ አቅጣጫ የሚጠቅም ይመስል ፀያፍ ስድብ እና ብሽሽቅ ስፖንሰር በማድረግ የፖለቲካ ዋልጌነታቸውን የሚያስመሠክሩት የአማራ ብሄርተኞች ናቸው። . ምከሯቸው… ❝እኛ ለመናገር ያልደፈርነውን ይናገሩልናል ይሳደቡልናል❞ በሚል አጉል አራዳነት የእኒህን ዕኩይ አዛውንት ያልተገራ አንደበት ማግዘፍ፣ እንደምሁር ቆጥሮ ማሸለምና በየሚዲያው እያቀረቡ መርዛቸውን እንዲረጩ ማድረግ ለማንም አይጠቅምም! . በቴሌግራም ➤ t.me/TalkEthiopia . #ታዲዮስታንቱ #የአማራብሄርተኝነት #ፋኖ #አሐዳዊነት #ልሙጣዊነት #ትምክህት #የብሄርፖለቲካ #ኢትዮጵያ 1.4K viewsedited 11:18