Get Mystery Box with random crypto!

ፍቅር እና ህይወት

የቴሌግራም ቻናል አርማ sura16722 — ፍቅር እና ህይወት
የቴሌግራም ቻናል አርማ sura16722 — ፍቅር እና ህይወት
የሰርጥ አድራሻ: @sura16722
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 607
የሰርጥ መግለጫ

እንኳን ደና መጣቹ ወደ አስተማሪ ታሪኮች ብዙ ትምህርታዊ ነገሮች አባባሎች ልብ ወለዶች ቀልዶች ዘፈኖች ብዙ ብዙ ይገኙበታል ። እናም ከአነበባቹ በኃላ ከተመቻቹ share ካልተመቻቹ comment አድርጉ ይመቻቹ ። ፈታ በሉ😁😁😁
ግን leave ማለት አይቻልም ከደበራቹ Comment ብቻ እናስተካክላለን ።
ለሰው ለማጋራት
@Sura16722
Call
0988145369
Comment
@Komose22

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-04 21:43:57 #ግሩም_የሆኑ_አባባሎች

ለልጆህ እንዴት ሀብታም መሆን እንደሚችሉ ሳይሆን እንዴት ደስተኛ መሆን እንደሚችሉ አስተምራቸው። ሲያድጉ የነገሮችን ሂሳብ ሳይሆን ዋጋ ያውቃሉ።

ምግብህን እንደ መድሃኒት ብላ ። አለበለዚያ መድሃኒት እንደ ምግብ ትበላለህ።

የሚወድህ ሰው በፍፁም አይለይህም። የሚያለያያችሁ ሺህ ምክንያት እያለም አንድ የሚያደርጋሁን አንድ ምክንያት ይፈልጋል።

በሰው ልጅነትና ሰው በመሆን መካከል ሰፊ ልዩነት አለ። ይህንን ሚረዱት ግን ጥቂቶች ናቸው።

ስትወለድ ሁሉምይወድሃል። ስትሞትም ሁሉም ይወድሃል።በመካከል ግን ራስህን ቻል።

በፍጥነት ለመሄድ ከፈልግክ ብቻህን ተራምድ።ብዙ
ርቅት ለመጓዝ ከፈልግክ ግን ከሰዎች ጋር ተራምድ።

በአለማችን የሚገኙ 6 ምርጥ ሀኪሞች።
የፀሃይ ጮራ
እረፍት
የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ምግብ
በራስ መተማመን
ጓደኞች
ጨረቃን ስታይ የእግዚአብሔርን ውበት ታያለህ።

ፀሀይን ስታይ የእግዚአብሔርን ሀይል ታያለህ። ራስህን በመስታወት ስታይ ግን የእግዚአብሔርን ምርጡን
ፍጥረት ትመለከታለህ።

በራስህ እምነት ይኑርህ።

መልካም ምሽት ይሁንላቹ

@Sura16722
432 views18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 21:13:15 እባክሽን ስጪኝ


እባክሽን ስጪኝ አትከልክይኝ ብሎ
እጇን እያሻሸ ጠየቃት አባብሎ
እሺ ልስጥህ ብላ አልጋው ላይ ቁጭ አለች
ከላይ ጡት ማስያዣ ወድያው አወለቀች
ወደታች ሳትለው የሚያምር ቀሚሷን
ተንደርድሮ ያዘው የናፈቀው ጡታን
.
.
.
እናት እምቢ አትልም ከጠየቃት ልጇ
ሁሌም ይዘረጋል ደግ አድራጊዉ እጇ።።



ሁልሺም እያንዳንድሽ ምን አስበሽ ነበር .....


@Sura16722
398 views18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 21:10:54 ፅናት

ክፍል
.
.
፨ ማን ያንሳቸው በወደቁበት ቦታ ሰአታት ተቆጠሩ ከወደቁ ከ 3 ሰአት በኋላ
ፅናት ነቃች። አይኗን ጨፈገጋት እንደምንም ተነሳች ደረቷ ላይ የበፀሎት እጅ
አለ። ድንጋጤው እብደትን ደምሮባት ባነነች። በፀሎት ወድቃለች ፅናት ብድግ
አለች እጇን በአፏ ጭና ቀረች። የምታደረገው ሁሉ ግራ ገባት ብቻ ግን አይኖቿ
እንባ አቅረርዋል። ተንበረከከች በፀሎትን ልታነሳት ከ ጭንቅላቷ ብድግ
ልታረጋት ስትሟክር የበፀሎት የጭንቅላቷ ደም እጇን ተነካካት ። ፅናት ፈራች
አታነሳት ነገር አትችላትም
፨ ፅናት እንደምንም ጥራ እና ተጣጥራ ጭንቅላቷ ላይ ባስረችው ሻሽ የፅናትን
ጭንቅላት አሰረችላት።ብትጮክም የሚደረስላት እንደሊለ አውቃ የበፀሎትን
መንቃት መጠባበቅ ጀመረች። እጇን አንጠራርታ በጆግ ያለውን ውሀ ካመጣሽ
በኋላ ለበፀሎት አስራላት ከጫፉ በተረፈው ሻሽ የጆጉን ውሀ አድረጋ ጭንቅላቷ
ላይ እያደረገች ማልቀስ ጀመረች።ፅናት በፀሎትን አቀረቅራ አየቻት የፅናት የእንባ
ዘለላ የበፀሎት የአይን ቆብ ላይ አረፈ በድጋሜ ጠብ አለ። የበፀሎት የእጆቿ
ጣቷች መንቀሳቀስ ጀመሩ።
፨ ፅናት ግን አላስሰተዋለችም ፅናት ከወገቧ ታጥፋ በፀሎትን አቅፋት
እያለቀሰች ነው። ፅናት የበፀሎት ትንፍሽ ሙሉ በሙሉ አንገቷ ላይ እያረፈ ነው።
ትግስት ሹክሹክታ በሚመስል ድምፅ እና ደሞ በደከመ ድምፅ ፅናቴቴ አለቻች።
ፅናት እህቴ ብላ ከ አንገቷ ቀና ልትል ስትል በፀሎት የቀኝ እጇን ፅናት አንገት ላይ
አሳረፋ ግጥም አድረጋ አቀፈቻት። ፅናት "እህቴ በፀሎቴ ደና ነሽልኝ" አለቻት
በፀሎትም ደና ነኝ አለቻት።
፨ረዥም ሰአት ተቃቅፈው ቆዩ። ከዛም በፀሎት ስትረጋጋ ፅናት ሄዳ ፍራሻቸውን
እየጎተተች በፀሎት ያለችበት ጋረ አደረሰችውና "በፀሎቴ ፍራሹን
አምጥቼልሻለው ቆይ ትንሽ ላግዝሽና ፍራሹ ላይ ውጪ" አለቻት። በፀሎትም
"እሺ ፅናቴ" አለችና ተንጠራታ ፍራሹ ላይ ሆነች። ፅናት አመቻችታ
አስተኛቻት።ፅናት "አየሽ እህቴ ብንሞትም ማንም አይደረስልንም ይህ ሁሉ
የአባታችን ጥፋት ነው። እሱ ክፉ ነው በጣም" አለችና አለቀሰች ስቅስቅ
እሪሪሪሪሪ አለችና በፀሎት ደረት ላይ ተደግፋ ማልቀስ ጀመረች።
፨ በፀሎትም ድምፅ ባታወጣም ስቅስቅ ብላ ነው ያለቀሰችው። በፀሎት ክንዶን
ዘረግታ "ነይ ክንዴ ላይ ደገፍ በይ" አለችና ፅናትን አስደገፈቻት። ፅናት
ሳታስበው እንቅልፍ ጣላት። ለጥጥጥ አለች። በፀሎትም በተመሳሳይ። ግን ደም
መፈሰሱን ሳያቆረጥ ትራሱን ማረጠብ ጀምሯል በፀሎት አቅም እያጣች ነው።
አልቻለችም ደክማለች በጣም ደክማለች።
፨ ፅናትም ተኝታለች ፅናት በእንቅልፍ በፀሎት ደሞ በሞት እና በህይወት
መካከል ሆነው ደቂቆች ለጉድ ሄደው ሰአታት ተተካ በፀሎት የጣር ድምፅ
አወጣች "ፅናቴቴቴቴ እህቴቴቴቴቴ ህይወቴቴቴቴቴቴ ልዩዬዬዬ" ፅናት
አልሰማችም። ተኝታለች በፅናትም አቅሏ ተሞጦ እራስዋን ስታለች። ከ30 ደቂቃ
በኋላ ፅናት ውሀ ጠምቷት ተነሳች። የተፈጥሮ ነገር ግን አይገረምም? ውስጣችን
ያለው ስሜት ስአቱን ጠብቆ ከሞት ታናሽ ወንድም ሲያነቃን እና ሲያባንነን ሊላ
ሰው ግን ጭንቅ ላይ ሲሆን አለመንቃታችን።
፨ፅናት አይኑዋን ስትገልፅ ያየችውን ማመን አቃታት ህልምም መሰላት።
የቤታቸው አነስተኛ ዱካ ላይ ሊባኖስ ተቀምጣ ነበር። ተፈናጥራ ተነሳች አይኖቿን
በእጆቾ አሻሽታ በድጋሜ ለማየት ሞከረች እውነት ነው ሊባኖስን በአይኗ እንጂ
በምናቦ አላየቻትም። ልትጠጋት ብላ ፈራች ግን ደሞ ውጧ እቀፊያት እቀፊያት
ይላታል የእዛ ሊባኖስን አውቃታለው ባይ ስው ንግግረም ያቃጭልባታል።
ግን ሊባኖስ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ከልቧ ላትወጣ በፅናት ልብ ውስጥ
ተቀረፆለች።
፨ከፈራሿ ብድግ ብላ ፈገግ ብላ ከምታያት ሊባኖስ ጋር ተጠምጥማ እንባዋ
ይፈስ ጀመረ። የበፀሎትም ደም እየፈሰሰ ነው። ፅናት በፀሎትን ለመቀስቀስ ወደ
እሷ ተጠጋች ፈገግ እያለች። የበፀሎትን እጆች ያዘቻቸው።"እህቴ በፀሎቴ ማን
እንደመጣ ብታይ??"አለች በፀሎት ግን በተራዋ ፅናትን አልስማቻትም ፅናት
አሁንም ፈገግ ብላ በፂ እናቴቴቴ አልስማሽኝም ሊባኖስ መጥታለች መልስ
የለም።
፨ ፅናት ግራ ገባት የበፀሎትን እጅ ብድግ አደረገችው ዝሏል የፈጣሪ ያለ ፅናት
ክው አለች። እጆቿን ለቀቀቻት እጆቿ ተልፈስፈሰው ውድቅቅ አሉ። ሊባኖስ ፈጠን
ብላ ወደ እነሱ ተጠጋች።
ሊባኖስ የበፀሎትን ጉንጭ እና ጉንጭ ይዛ ከግራ ወደ ቀኝ ከቀኝ ወደ ግራ
አዘዋወረችው ፅናት እና ሊባኖስ ተያዩ ደነገጡም።ፅናት በፀሎትን ከጭንቅላቷ
ቀና ለማድረግ እጆቿን ከትራሱ እና ከበፀሎት ጭንቅላት ስር ሰረስራ
አስገባቻቸው እጆቿን እረጠባት ደነገጠች። ፈጠን ብላ አወጣቻቸው እጆቿ በደም
ተለውሰዋል።ፅናት ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ግራ ገባት ሊባኖስ የፅናትን እጆች
ስታየው ጣረ ሞት ያየችም ትመስል ነበር። "ምንድነው ሚጢጢዋ" አለቻት
የድንጋጤ ፊት እያሳየች። ፅናትም " እኔ ለእራሱ ምንም አላውቅም"። አለችና
"ቆይ ቆይ" ብላ የተፈጠረውን ነገረቻት። ሊባኖስ በፍጥነት ስልኳን አንስታ
ደወለች።" ሄሎ የት ነክ አሁኑኑ ዛሬ ያደረስከኝ ቤት ና" ስልኩን ዘጋችው።
፨ ፅናት እየተንቀጠቀጠች ነው። በሲኮንድ ፍጥነት ሰውየው ደረሻለው ብሎ
ሊባኖስ ጋር ደወለ። ከዛም ተቀበለችውና በፀሎትን አብረዉት ከመጡት
ግብራበሮቹ ጋር መጥተው ከ እነ ሊባኖስ እና ፅናት ጋረ ጭኗቸው አንፖላንሱን
እያስቦረቀ ነዳው።"ደረሰናል" አለ ሹፌሩ ፅናት ግራ ገባት። ምንም አይነት
የህክምና ጣቢያ ስላላየች። ጋቢና የተቀመጠችው ፅናት ወደ ኋላ ዞራ እህቶን
ማየትም አልቻለችም። ፅናት ፈራች "እንውረድ" አለና ሹፌሩ ወረደ ከዛም
ሲወረዱ ፅናት ፈጠን ብላ ወደ ኋላኛው የህሙማን መጫኛ ቦታ የመኪናውን
ሻተር ከፍታ ስታይ ከቦታው ላይ ሊባኖስም ሆነ እህቷ በፀሎት እንዲሁም እነዛ
ሰዎች በቦታው የሉም ።
፨ ፅናት ያ ሊባኖስን በደንብ አውቃታለው ያለውን ስው ንግግር አንድ በአንድ
አስታወሰች። በሀዘን እና በድንጋጤ ጊዜ ጭንቅላቶ ፈፅሞ መቆቆም የማይችለው
ፅናት ልክ እንድ ሁል ጊዜው እራዋን ልትስት ሲያንገዳግዳት ሹፌሩ ተሯሩጦ
ደገፋት ከዛ ፅናት የሹፌሩ ክንድ ላይ ወደቀች።

ይቀጥላል...

@Sura16722

♡ ㅤ  ❍ㅤ    ⎙ㅤ  ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
--------------
286 views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 17:42:27 ነበር። ፅናት ለእራስዋ እሷን አበረትታ እህቷን ማበረታት እንጂ ማስነፍ
እንደሊለባት ተረዳች። ከዛም የምትሸጣቸውን ምግቦች በብዛት እየሰራች ለቀን
ሰራተኞች ለመሸጥ ወሰነች ለእህቷም አማክራት ተስማሙ።ከዛም ሄዳ የሄለን
ኪለርን መፅሀፍ በቅናሽ ገዛች።
፨ ከዛም እህቷን መጥታ እህቴ እኛ ጠንካሮች መሆን አለብን ከእኛም የባሰ አለ
እኮ እየውልሽ ዛሬ ስለ ሄለን ኪለር አነብልሻለው በቃሌ ከነገርኩሽ ይበልጥ
እንድታውቂው ነው። በፀሎት የፅናት በአንድ ጀንበር መቀየር አስገርሞት። እሺ
ፅናቴ የእኔ ፅናት አለቻት። ፅናት የበፀሎትን እጆች እየዳበሰች። እና ደሞ አሁን
እረፍት ስለሆንኩኝ ሁሌም ቤተክረስቲያን እንሄዳለን ልክ እንደ ድሮዋችን አባባና
እማማንም እንጎበኛቸዋለን አሁን ምግብ የመሽጫ ሰአቴ ሳይደረስ ስለ
ጠንካራዋ ሄለን ኪለር አስታውሺ እህቴ ይህቺ ሴት ማየትም መስማትም
መናገርም ጭራሽ የማትችል ሴት ናት ግን ደሞ ጠንካራ ናት። አየሽ እህቴ
ያለንን እናመስግን የሚመጣውን ፈጣሪ ያውቃል ሊላው ደሞ መፅሀፍ ቅዱስም
አነብልሻለው ሀይምሮዋችን ከጠነከረ ሊላው ትርፍ ነው።
፨ ያቺ የጫት ቤቱ አያት ጠንቋይ ናቸው ብላ ለሰፈሩ ተናግራ ከዛም ይሄው
የማይሉት ነገር የለም እህቴ ግን እንጠንክር አለቻት።በፀሎት ለፅናትን ማደግን
በአንደበቷ አስተውላ እጅግ ተደሰተች እና ነይልኝ ብላ እጆን ዘረጋችላት ፅናትም
ብድግ ብላ ልታቅፍትወደፊቷ ተጠጋች ነገር ግን ከፊቷ የሚታየው ድንግዝግዝ
የሚል ነገር ነው ሰውነቷ እንደመዛል አረጋትፅናት እራስዋን ሳተች። በፀሎት
ደንግጠች ከዊልቸሩ ልትወርድ ስትሞክር አብራት ወደቀች።
፨ማን ያንሳቸው? መራመድ የማትችለው በፀሎት ወይስ እራስዋን ስታ
የወደቀችው ፅናት መንቀሳቀስ የማትችለውን በፀሎት ማንም ማንንም ማንሳት
አለቻለም። ጮሀውም ጎረቤት መጥራት አልቻሉም ምክያቱም ፅናት ራስዋን
ስታለች በፀሎትም ስትወድቅ ጭንቅላቶን የመታት ዘነዘና ጭንቅላቷን አድምቷል
በፀሎት እንየፅናት ራሷን ሳተች። ማን ይድረስላቸው ታዲያ..

ይቀጥላል

@Sura16722
♡ ㅤ  ❍ㅤ    ⎙ㅤ  ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
----------------------------------------
311 views14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 17:42:27 ፅናት

ደራሲ ቤዛዊት ፋንታዬ (የሸዋ ልጅ)

ክፍል
.
፨ ፅናት በዛ ሰአት እራሷን አልነበችም ውስጧ ዝብርቅርቁ ወጥቶ ነበር። ደረቃ
ቀረች በቆመችበት የያዘችውን ትኩሱ ቡና እግሯ ላይ ቢደፍም አልተሰማትም።
በፀሎት ቡና ወደወደቀበት እጆቿን በመዳበስ አይኖቿን ወደ ጣሪያ
ወረወረቻቸው። በፀሎት ለስለስ ባለ ድምፅ "ምንድነው ምን ተፈጠረ?" አለች።
ፅናት አይሆንንንምም ብላ ጫከች።
፨ ያኔ ሊባኖስ በፍጥነት በሩን በርግዳ ገባች። ሁሉም ፅናትን ለማረጋጋት
ቢሞክርም አልቻሉም ፅናት አንዴ ነቃ ብላ "አይ አይ ሊሆን አይችል" ትላለች
ከዛም ፍዝዝ ብላ ትቆያየች። ሊባኖስ ፅናትን ደግፋ ፍራሽ ላይ ጋደም አደረገቻት።
ፅናት ግን በጭራሽ ውስጧ አላረፈም ። መንቀጥቀጥ ጀመረች። ሊባኖስ በጣም
ደነገጠች አቶ ኪዳኔም እንደዛው በፀሎት ምን እንደተፉጠረ ብትጠይቅም ምላሽ
አላገኘችም። ከዛም ቀዝቀዝ ባለ ድምጿ "ፅናቴ ፅናቴ ደና ነሽ እህቴ"አለች።
መልስ አልተሰጣትም ከዛም "ሊባኖስ እህቴ ደና ነች?" አለች አሁንም ዝም
ከዛም ጮክ ብላ መልሱልኝ ብላ ጮከች።
፨ሊባኖስ ፈጠን ብላ ወደ በፀሎት ቀረባ "ደና ናት አትስቢ እንዲ ሆነሽ ማየት
ከብዷት ነው የሚወዱት ሰው በእዚህ መልኩ ተጎድቶ ማየት ያማል" አለቻት።
በፀሎትም የሊባኖስ ንግግር የገባት ትመስላለች "ልክ ነሽ"ብላ ኡፍፍፍ አለች።
ሊባኖስ ፅናትን ለማረጋጋት ወደ ፅናት ሄደች። ፅናት አሁንም አልተረጋጋችም ይህ
ነገሯ ለቀናት ዘለቀባት ከዛም በሂደት እየለመደችው መጥታ እህቷን መንከባከብ
እና ማገዝ ጀመረች።
፨በጊዜ ሂደት በፀሎት ማየት ባለመቻልዋ ተስፍ ቆረጠች። ፅናት ግን ተስፍ
እንዳትቆረጥ የሚቻላትን ሁሉ ታረጋለች ለእሷ ብላ ማየት መስማትም የማይችሉ
ስዎችን ታሪክ አፈላልጋ ታነብላታለች ለምሳሌ ስለ ሄለን ኪለር። ሄለን ኪለር
ለበፀሎት ብረታትን ለፅናት ደሞ ድልን ሰጥታቸዋለች። ፅናት ትምርቷን
አላቋረጠችም ምክንያቱም ሊባኖስ ታግዛታለች። የፅናት የቀን ተቀን ድረጊቷ
ሌሊት ተነስታ ለእሷ እና ለእህቷ ሊባኖስ ቤታቸው ካደረችም ለእሷ ቁርስ ሰረታ
ቤትም አፅድታ ትምህረት ቤት ትሄዳለች ሄዳ 6:30 ትመጣለች። ከትምህርት
ስትመለስ 30ደቂቃ ያክል ተኝታ በድጋሚ ተነስታ ታጠናለች። አጥናታ ስጨረስ
9:30 ይሆናል። ከዛም ማታ ማታ የምትሸጠውን ምግብ በሊባኖስ እርዳታ
ትስራለች። በራቸው ላይ በዳቦ የሚበሉ ቀለል ያሉ ምግቦችን እንሸጣለን ብለው
እሷና ሊባኖስ ካርቶን ላይ ፅፈው ነው የለጠፉት። ፅናት የቤቱን ስራ ስትስራ
ሊባኖስ እና በፀሎት ከ ሊባኖስ መኖሪያ ያመጣሉ ሊባኖስም የደረሰችበትን
ታግዛታለች። አቶ ኪዳኔ በፀሎት ለህክምና የተጠየቀችውን ብር መክፍል
ስላቃታቸው በሶስተኛው ወር ነበር ከነ ቤተሰቧቻቸው ድርሻቻው
የጠፋው።ገፍታሪው ልጅም ያን ቀን ነበር የተሰውረው። የሰፈሩ ሰው የቡና ቁርስ
መሆናቸውም ቀጥሏል እና ደሞ ፅናት በክፍል ከፍ ባለች ቁጥር በውበቷ
ያልተማረከ እና ያልጠየቃት እኩያ ወንድ የለም ውበቷ በጣም ሲጨምር ቤቷ
ድረስ ዱረየውም ጨዋውም እየመጣ የአብረሽኝ ሁኒ ማመልከቻውን ያስገባል።
በሊላ በኩልም ቆንጆ ቡዳ ነው ቡዳ ቆንጆ ነው እያሉ የተቀሩት የሰፈሩ ኑዋሪዎች
ያበሽቆት ጀመር።
፨ፅናት ሁሌም ይህ ነገር ስሚ ሰለቻት ታለቅስ ነበር ገና ሳታድግ በቅጡ እንዲ
መባልዋ ምቾት ነስቷታል በየ መንገዱ የሚስሟት አሮጊቶችም ጭምር ስለቿት።
ከዛም ሊባኖስ አንድ ሀሳብ አመጣች ቤት መቀየር በእዚህ ተስማምተው ሊባኖስ
ቤት መፈለግ በጀመረች በሳምንቱ አገኘች። ይህን ዜና ለእነ ትግስት እንዲ ስትል
ነገረቻቸው "ቤት አግኝቼላችዋለው ያው ሰፈሩ ከእዚህ የባሱ ስዎች ነው ያሉበት
ነው ግን ይሁን አለቻቸው ስትነግራቸው ፅናት ቡና እያፈላች ነበረ ከቡናው ተነስታ
ፍራሹ ላይ የተቀመጠችውን ሊባኖስን እና ዌልቸር ላይ የተቀመጠችውን
በፀሎትን ሳመቻቸው።
በነጋታው ሊባኖስ የነገረቻቸውን ሁሉ አድረገው ወደ አዲሱ ሰፈር ወደ አዲሱ ቤት
ተቀላቀሉ ይህ ሲሆን ፅናት 10 ክፍል ደረሳ ነበር።
፨ እነ ፅናት ያን ጊዜ ኑሮም በጣም ከበደባቸው ከቤታቸው ሽያጭ የተረፈውን
አንድ በአንድ ለትግስት መታከሚያ እና ለኪራይ ካደረጉት ወራት ተቆጠሩ እንኳን
ብር የሰው ልጅም አካል አልቆ እና እረግፎ መንምኖ ያልቃልና እጃቸው ላይ
ያለው ብር አንድ በአንድ ለቤት ኪራይ እና ለበፀሎት ህክምና ወጥቶ አለቀ።
አሁን ከድሮ በበለጠ ህይወት ከበደች ፊቷንም አዞረች በይበልጥ እና ደሞ
በእጥፉ ችግራቸው ልክ እንደተቦካ እና ኩፍ እንደሚል ሊጥ ወደላይ ወጥቶ
ተስፋቸው ደሞ ሊጡ ሲመለስ ያለው አይነት መመለስ በቀስታ እንደመተንፍስ
በቀስታ እንደመቀነስ በቃ ኑሮም እንዳልቦካ ሊጥ እንደመቆምጠጥ ሆነ።
፨ታዲያ ይህንን ኑሮ መኖር ለማነው ቀላል ለትንሿ ፅናት ነው ወይስ የአይን
ብረሀኗን እና የመራመድ ፀጋዋን ለተገፈፈችው በፀሎት እ እህ መልስ የለም።
ፅናት ከትምህርቷ ስትመለስ እንፖቴቶ እና ፓስቲ በመስራት እና በመሽጥ ከዛም
ብር በማጠራቀም ለሆዳቸው ተርፍለች። ሊባኖስ አትረዳቸው ነገር ግን እሷም
እረጋፊ ሳንቲም የሊላት ደሀ ነች።
፨ ፅናት መጀመሪያ ሰሞን ለአንድ ቀን የሊባኖስን ስፈር አይታውዋለች
በመጀመሪያ ቀን ግን ሊባኖስ ፅናት እንድትገባ አልፈቀደችላትም። ሁሌም ቢሆን
የሊባኖስን ቃልን መቼም አትረሳም። ሊባኖስ ለፅናት ብረታት ሆናታለች።
፨ሊባኖስ አሁን የት እንዳለች ሳትናገር ድራሿ ጠፈቶል።ይህ ነገር ፅናት እና
በፀሎትን ቢያሳስባቸውም መፍትሄ አላገኑም ፅናት ትኖራለች ብላ የምታስብበት
ቦታ ሁሉ ፈለገቻት ነገር ግን ሁሉም ሊባኖስ ቋሚ መኖሪያ እንደሌላት እና
ባገኘችበት እንደምታድር ከመንገር ውጪ ማንም ምንም አላለም። እንደውም ስለ
ሊባኖስ ስትጠይቃቸው ፍረሀት እና ድንጋጤ ከፊታቸው ይነበባል። ፅናት ለምን
ስለ ሊባኖስ ሲነሳ እንዲህ እንደሚሆኑ ግራ ገባት።
፨ ሊባኖስ ከጠፋች ወራት ተቆጥሯል በእነዚህ ወራት ውስጥ ግን አንድ ስው
አግኝታ ነበር። ሰውየው ሊባኖስን በደንምብ እንደሚያውቃት እና ሊባኖስ ማለት
የመስቀል ወፈ እንደሆነች ማንም እሷን ፈልጎ ማግኘት እንደማይችል እና ተመልሳ
ብትመጣ እንኳን ከእሷ እንድትረቅ ሊባኖስን በደንብ እንደሚያውቃት እና
መጀመሪያ ሰውን መላክ ሆና ቀረባ ከዛም በአይኗ ሀይል ደም ግባት ውስጥ
ገብታ ሞትን የሚያስመኝ ስቃይ እንደምታሰቃይ ፤ ውሎዋ የመቃብር ቦታ ላይ
እንደሆነ የሞቱ ሰዎችን እንደምትወድ በቁም ያለውን ሰውም ገድላ ወደ እሪሳነት
መቀየር ለእሷ በቁም ላለው ሰው ውለታ እንደሰራች አንደምትቆጥረ ነገራት።
ፅናት አማተበች በጣምም ፈራች ሰውየው የሚነግራት ፊልም ይሁን እውነት
ቀልድ ይሁን ውሸት ግራ ገብቷታል ግን ደሞ ጨንቋታል።
፨ ሊላው ፅናትን ሰላም የነሳት ከድሮ ሰፈራቸው አንዲት ሴት መጥታለች ሴቲቶ
የእነሱ ሰፈር ባለ ጫት ቤት ሰውዬ አያት ናት ድሮ ሰፈራቸው የሚያወሩትን ሁሉ
ለባለ ጫት ቤቱ ስትነግረው ጫት ቤቱ ለደንበኖቹ ደንበኞቹ ለሴተኛ አዳሪዎች እና
ለሚስቶቻቸው ተናግረው ወሬውን ነዙት።
፨አንድ ቀን ፅናት በአንድ ጀንበር እራስዋን ጠንካራ ውስጧንም ጠንካራ አድርጋ ተነሳች። ጊዜው የ10ረኛ ክፍልን ፍተና ተፈትና በጥሩ ውጤት አልፋ ክረምት ላይ
297 views14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 11:41:41 ➲ ፍቅር በ 17 ዓመት

እሱ፦ ሃይ ቤቲ አቤት ዉበት…በጣም አምሮብሻል!

እሷ፦ ቴንኪዉ ሚኪ ፎር ዩር ሪስፔክት

እሱ፦ ኧረ ላንቺ ያለኝ ፍቅር ጨምሮ ጨመሮ ላብድ ነዉ…በጣም ወድጄሻለሁ….

እሷ፦ ምን!!ትምርቴን ልማርበት ላሽ በል….!

እሱ፦ ኧ…

️➲ ፍቅር በ 25 አመት

እሱ፦ ሃይ ቤቲ አቤት ዉበት ፓ!

እሷ፦ አመሰግናለሁ (እንግሊዝኛዉ ቀንሷል)

እሱ፦ አንድ ነገር እያብሰለሰልኩ ብዙጊዜ ቆየሁ…

እሷ፦ ምነዉ በደህና እስቲ አጫዉተኝ

እሱ፦ ወድጄሻለሁ…በጣም! በናትሽ አብረን እንኑር..

እሷ፦ ኧ……..እኔን?……አታዉቅም እንዴ?

እሱ፦ ምኑን?

እሷ፦ ፍቅረኛ እንዳለኝ

እሱ፦ እውነት!;ታዉሬ ይሆናል…..ሶሪ

እሷ፦ ምንም አይደል…ግን አንተ እንዴት ነህ?

እሱ፦ ….እእ…..

️➲ ፍቅር በ 36 አመት

እሱ፦ ሃይ ቤቲ

እሷ፦ ሃይ ሚኪ ዛሬ ደሞ ዘንጠሃል ባክህ

እሱ፦ ምን ይደረግ ብለሽ ነዉ….ሙሽራ መስለን እንደዉ ሚስት ካገኘን ብለን ነው…ይገርማል ሚስት አጣንኮ!

እሷ፦ ምን ሀገሩን የሞላዉ ቆንጆ ብቻ ነዉ…

እሱ፦ እዉነትሽን ነዉ ከተማዉ በፎቅ ጎጆ ተሞልቷል ቆንጆዎቹን የት እንድረስባቸዉ ፎቅ ሆነዉብን ሆዳቸዉ እንደካንጋሮ ልጅ ሳይሆን ብር እያሰቀመጠ ንግድ ባንክን አስንቋል!

እሷ፦ አትቀልድ ባክህ!እኛ አለን እንጂ በናንተ በወንዶች የፍቅር ቁማር ስንበላ እድሜያችንን የፈጀን!

እሱ፦ ይልቅስ አንቺ አግቢ እንጂ አረጀሽ እኮ

እሷ፦ ባል እንዲህ በቀላሉ የት ይገኛል ብለህ ወንዶቹ እንደዉ ማግባት ማለት…መታገት ነዉ ብለዉ ዝርም አይሉ… ይልቅ አንተ ለምን አታገባኝም?

እሱ፦ ቤት ላስገባሽ? አይይይ አልታይ አለሽ መሰል..በይ እግርሽን ከፍ አርጊዉ…የበሩ ደፍ እንዳይመታሽ!

እሷ፦ ዉይ አንተ ደሞ! ከምሬን እኮ ነዉ!

እሱ፦ ትምርቴን ልማርበት(ኪኪኪኪ)!

እሷ፦ ማሾፍህ ነዉ ባንተቤት ምናገባኝ ቆመህ ከምትቀር ብዩ ነዉ

እሱ፦ እኔማ ነገሩ ሊጥ እያለ ስጠይቅሽ ልብሰል ስትይኝ..ተቦክቶ ስጠይቅሽ እርሾ ይግባበት ስትይኝ…በስሎ እንኳን ስጠይቅሽ ቆራሽ አለ ስትይኝ…ይኸዉ ዳቦዉ አልቆ የሻማ ሲወረወር እንኳ የሚቀልብ ጠፋ! አይ ጊዜ!!!

እሷ፦ እእ…


@Sura16722
481 views08:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 10:28:49 ያረጁ ሰዎች ሁሌም ሰርግ ላይ መታ መታ ያረጉኝና ቀጣይ አንተ ነክ ይሉኛል

ከዛ እኔም በየቀብሩ እነሱ ላይ ተመሳሳይ ነገር ማድረግ ጀመርኩ

@Sura16722
289 views07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 10:28:03 ❝ምናልባት የሂወታቹህ ታሪክ አጀማመር አስደሳች አልነበረም ይሆናል ግን ያ እራስነታቹህን አይገልፅም...ዋናው የቀረው ህይወታቹህ ነውና መሆን የምትፈልጉት ምረጡ።❞

@Sura16722
301 views07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 20:56:33 ፨ፅናት ጨነቃት ሁለቱንም በተራ አይታቸው አይኗን መለሰች። ፅናት ጀበናው ላይ
ውሀ እና የቡና ዱቄት ጨምራ ጣደችው። ቡናውን ጥዳ እስኪፈላ ፈልቶ
እስኪሰክን ሁሉንም በተራ አየቻቸው። በፀሎት ምንም ቃል ቤት ከገባች በኋላ
አላወጣችም። ቡናውን ቀድታ ልትስጥ ስትል ሊባኖስ ቆይ እኔ እስጥልሻለው"
ስትል። ፅናት "አይ እኔ እሰጣለው" አለች። ሊባኖስ "ቁጭ በይ አልኩሽ" አለች
እና ተቆጣቻት። ፅናት ግራ ተጋብታ "እሺ" አለች።
ሊባኖስ ቡናውን በፀሎት በእጇ "እንኪ ያዢ ቡና" ብላ ስጠቻት በፀሎትም
በዳበሳ መልክ ተቀበለቻት ጠጥታ ስትጨረስ ሊባኖስ ተቀብላ ለፅናት
ስጠቻት።ፅናት ይበልጥ ግራ ገባት ሳታስበው "እንኪ ያዢ ቡና"አለች። አንደኛው
ተፈልቶ ሁለተኛው ሊቀዳ ሲል ሊባኖስ ስልኳ ጠረቶ ወጣች።
፨ ፅናት ቡናውን ቀድታ ለጋሽ ኪዳኔ ልትሰጣቸው ስትል ቆይ እኔ እስጥልሻለው
ሲሉዋት ፅናት ብስጭት ብላ "አይ ምንድነው እኔ እስጣለው ምናምን ምትሉት"
አለችና ለእሳቸው አቀብላችው ከዛም ለሊባኖስም አስቀመጠችላት። አቶ ኪዳኔ
ፊት በፍራቻ ተውጧል። ፅናት ሌላኛውን የበፀሎትን ቡና አንስታ ለመስጠት
በፀሎት ፊት ቆመች። ቡና የያዘውን እጇን ወደ በፀሎት ዘረጋችው በፀሎት ግን
እጇን አልዘረጋችላትም። ፅናት በፀሎት ላይ ማየት የተሳነው ሰው ፊት ስታይ በእጇ
የያዘችውን ብና በቁሟ ለቀቀችው....


ይ ቀ ጥ ላ ል
@Sura16722
214 views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 20:56:33 ፅናት

ደራሲ ቤዛዊት ፋንታዬ (የሸዋ ልጅ)

ክፍል
.
.
፨የሊባኖስን ድምፅ የሰሙ ሁሉ ተሰበሰቡ ፅናትን ወደ ህክምና ክፍል ወሰዷት።
ሊባኖስ ደንግጣለች። "የፈጣሪ ያለ አሁን ደና አልነበረች እንዴ?" አለች ድምፅ
አውጥታ ለእራስዋም አልገባትም ከዛም ወዲያውኑ "ለነገሩ ተረብሻ ነበር"
አለች። ሊባኖስ በራስዋ አለም ውስጥ ሆና ፅናትን ሊረዱዋት የሚረባረቡትን
ሰዎች እረስታቸዋለች። አንድ ነርስ "ነይ እህቴ እዚህ ተቀመጪ እና ተረጋጊ ምኗ
ነሽ?" አለቻት።
፨ሊባኖስ ምኔም ናት ማለት አልፈለገችም ፤ ግን ደሞ እህቴ ናትም ብላ መዋሸት
አልፈለገች፤ ከዛም "እኔም ዛሬ ነው ያወኳት" አለች። ነርሷም "እሺ እንደዛ ከሆነ
በቃ ተረጋጊ" አለችና ጥላት ሄደች። ሊባኖስ ደብተሯን ካስቀመጠችበት አግዳሚ
ወንበር አምጥታ ገለፃ ከ ጉያዋ እራስ አውጥታ ለመፅፍ ጣቷቾን አዘጋጀች ።
፨ ደብተሩን ገለጠችው ስትገልጠው የፃፈችው ፅሁፋ ላይ የበሰበሰ ቦታ አየች
የበሰበሰው ሉክ ከእስኪብረቶ ቀለም ጋር ሆኖ አንድ ፈዛዛ ነገር ሰረቷል። ሊባኖስ
ይህንን ስታይ የፅናት እንባ ደብተሩን እንዲህ እንዳረገው መገመት
አልከበዳትም። "ይህቺ ብላቴና ለምን በእዚህ ፅሁፋ አለቀስች? ለምንስ ነው
ይህ ፅሁፍ የረበሻት?" አለች። ግን ይህንን ለማወቅ የግዴታ ፅናት ወደ እራስዋ
እስክትመለስ መጠበቅ አለባት።
፨ ሊባኖስ ስልኳን አውጥታ ደወለች።"ሄሎ" አለች። አንድ ሰው "አቤት" አላት።
"በቃ እኔ ወደ ሰላማዊያን ልሄድ ነው" አለችው። "አሁን የት ነሽ?" ሲላት
አሁንም "እዚሁ ነኝ ግን በቃ ልሄድ ደክሞኛል" አለችው። ሰውየውም "አይ
ሊባኖስ በቃ ስትረበሺ እና ማሰብ ስትፈልጊ እነሱ ጋረ ነው አደል የምትሄጂው?"
አላት።
ሊባኖስም'' አዎ ልክ ነክ ዛሬ የሚመጣ ሰላማዊ የለም?" አለች። ሰውየውም
"አለ ቦታ አለ እንዴ አንቺ ጋረ" አላት። ሊባኖስም "አዎ 5 የተለቀቀ ቦታ አለ"
አለችው። ሰውየውም "እሺ ጥሩ በቃ እዚህ 4 አሉ አመጣቸዋለው"። አለና
ተስናብቷት ስልኩን ዘጋው።ሊባኖስም ደብተሯን ይዛ ከሆስፒታሉ ውልቅ አለች።
ወደ ሰላም የምታገኝበት ቦታ ውልቅ
*@ከ2ወር ከ15 ቀናት በኋላ@***
ሁሌም በእነዚህ የህክምና ቀናት ውስጥ ፅናት ሲርባት የምታበላት ፤ሚስጥሯን
ለምትነግራት ፤እና እራስዋን ያካፈለቻት ሴት ሊባኖስ ነበረች። ፅናት ለሊባኖስ
ስለ እራስዋ እና ስላሉባት ችግሮች እንዲሁም ስለምትወዳት እህቷ ለምን ያንን
ወረቀት ስታነብ እንደከፋት ሁሉንም ባለፉት ሀኪም ቤት በቋዩባቸው ጊዜ
ነግራታለች።
፨ ሊባኖስ ግን ለጭንቅላቷ ይከብዳታል በማለት ሙሉ ህይወቷን አላካፈለቻትም
አልነገረቻትም ።
ሊባኖስ ለፅናት በህይወቷ ውስጥ የሚፈጠሩት ነገሮች ሁሉ እሷ ምንም ያህል
ብትታገል መሆናቸው እና መፈፀማቸው እንደማይቀር ብርታት ያለውን ቃል
እየነገረቻት ውስጧ እንዲቀረፅ አድረጋታለች። በተጨማሪም እራሷን ስታ ከነቃች
በኋላ በነጋታው መጥታ ብዙ ምክሮችን መክራት እና ከ ተሻላት በኋላ ሙሉ
በሙሉ ትምርቷን እንድትማር ወላጅ በተባለ ቁጥረ እሷ እንደምትመጣላት
አስረግጣ ነግራት ነበረ። ያኔ ፅናትም መልሷ እሺ ነበር ምክንያቱም ፅናት ያኔ
ለሊባኖስ በህይወቷ ስለተፈጠረው ነገር ስትነግራት ሊባኖስ ለፅናት ብረታት
ሆናታለች እንዲህ ነበረ ያለቻት "እየውልሽ ፅናትዬ እንዳልኩሽ ትምርትሽንም
ቀጥይ በፍፁም ትምህርትሽን ማቋረጥ የለብሽም እህትሽ ደካማ ብትሆኚ
ብትሰማ በጭራሽ ደስ አይላትም ደስ የሚላት ጠንካራ ስትሆኚ ነው እንጂ ደካማ
ስትሆኚ አደለም እህትሽ በእሷ ምክያት ትምረትሽን እንዳቋረጥሽ ብታውቅ
ይፀፅታል" ነበረ ያለቻት።
፨ ዛሬ ይህ ሁሉ አልፎ በፀሎት ልትመጣ ነው። 2ወር 15 ቀን ፅናት ትምህረት
ቤት ስትሄድ ሊባኖስ ሆስፒታል እህቷን እየተመላለሰች እየጠበቀችላት የ15ቀን
ረፍቷ ሲያልቅ ለ ወር ትምረቷን ሳታቋረጥ ቀጥላለች። ሊባኖስ ፅናት እንድታጠና
እና የእሷን እና የእህቷን ህይወት ትልቅ ደረጃ ደረሳ እንድታሻሽል ብርታት
ስለሆነቻት ትምህረቷን ጥሩ አድረጋ ይዛዋለች ። በፀሎትም ከህክምና ስትወጣ
ከሊባኖስ ጋር ዶክተሩ አስተዋውቋታል "እህትሽ ጎን የነበረችው ሴት ናት"ብሎ።
ዛሬ የፌሽታ ቀን ነው በፀሎት ወደ ቤቷ ልትመጣ ነው ፅናትም ቤቱን በእሷ እና
በቤቱ አቅም ፏፏ አረጋዋለች። እህቷን ቤቷ እስክታያት በጣምምምምምም
ጓጉታለች።
፨ ፅናት ቤቱን አዘጋጅታ ጨረሳለች እና ሊባኖስ እና የአላዛር አባት አቶ ኪዳኔ
በፀሎትን ይዘዋት እስኪመጡ እየጠበቀች ነው። እየተቁነጠነጠች ቁጭ፣ ከዛ
ብድግ፣ እቤቷ ወጥታ አየት፤ ከዛ መለስ። በጣም ጓጉታለች። በጣምምምም
ፍራሿ ላይ ጋደም አለች።
ወዲያው በረ ተንኳኳ ፅናት ተስፈንጥራ ተነስታ ከፈተችው ዊልቸረ ላይ
የተቀመጠችውን የእህቷን የዊልቸር መግፊያ እጀታ አቶ ኪዳኔ ይዘውታል።
ሊባኖስም የበፀሎትን ህክምና ላይ እያለች የምትገለገልበትን እቃዎች በአነስተኛ
ሻንጣ ተጠቅጥቆ ይዛዋለች።
፨ ፅናት በሩን እንደከፈተችው አይኗ እህቷ ላይ አረፈ "እህቴ" አለች።በፀሎትም
"ፅናትዬ ብላ እጆቿን ለማቀፍ ዘረጋቻቸው" ፅናት ጎንበስ ብላ በፀሎት እቅፍ
ውስጥ ገባች። በፀሎት ሳግ እየተናነቃት "ይህ ጠረንሽ በጣም ናፍቆኝ
እንደነበረ ታውቄያለሽ?" አለቻት። ፅናትም ሲቃ ባዘለ ድምፅ "እኔ ለእራሱ
በጣም ናፍቀሽኛን" አለችና ሳመቻት። ሊባኖስ ከት ብላ ስቃ "አይ ፅናቴ በቃ
አንቺ ናፍቀሽኛል ለማለት ናፍቀሽኛን የምትይው የኔ ቆንጆ ቆይ መቼ ነው ቃሉን
በስነ ስረአቱ ጠረተሽ ማረግ የምታሳያት ደሞ አልናፈኩሽም እንዴ ትናት እኮ ነው
የተገናኘነው አለችና እጇን ዘረጋችላት።
ፅናትም ከበፀሎት እቅፍ ወጥታ ወደ ሊባኖስ ተጠግታ እቅፍ አረገቻትና "አንቺም
ናፍቀሽኛን ያላንቺ እማ መች ይሆልኛን" አለቻት።
፨ ሊባኖስም "እውነት ነው ሚጢጢዋ" አለችና ሳመቻት። ፅናት አቶ ኪዳኒን
አየት አድረጋ እጇን ዘረጋችላት እሱም እጁን ዘረጋላት፡ተጨባበጡ እጁን ወዲያው
ኑ ግቡ አለቻቸው። ከዛም ተከታትለው ገቡ። ፅናትና ሊባኖስ ምግብ ማቀራረብ
ጀመሩ። ፅናት የቆረጠችውን የቁርጥ እንጀራ ልታስይዝ ስትል ሊባኖስ "ቆይ እኔ
አስይዛለው አንቺ ቡናውን አፍይው" አለቻት። ፅናትም "እሺ ሊቦዬ" አለችና
ቡናውን ለማፍላት ቁጭ አለች።
፨ ፅናት በፀሎትን አየቻት በፀሎት አይኖቾን ወደ አንድ አቅጣጫ አድረጋ
ታረገበግበዋለች። ፅናት ግራ ገባት ግን ዝም አለች። ምን እየተፈጠረ እንደሆነ
ግራ ገባት። ሊባኖስን አየቻት አይናቸው ሲገጣጠም ሁለቱም አይናቸውን መለሱ
ፅናት ምሳቸውን ከበሉ በኋላ ቡና መቁላት ጀመረች። አሁንም በድጋሜ በፀሎትን
አየቻት ካፈጠጠችበት አይኖቾን መለስም አላረገችም። ሁሉም በልተው
ጨረሰዋል ሲበሉ በፀሎትን ሊባኖስ ነበረ ያጎረሰቻት።
፨ፅናት ግራ ገባት ወደ ሊባኖስ ዞራ ሊባኖስን በጥያቄ አስተያየት አፋጠጠቻት
ሊባኖስ ግን ዝም ብላ ከአቶ ኪዳኔ ጋር ማውራቷን ቀጠለች። ፅናት አቁነጠነጣት
ቡናውን ቆልታ ስትጨረስ ልትወቅጥ ውጪ ወጣች። ቡናውን እየወቀጠች
ጆሮዋን ወደ ቤት ጣለች። የሽኩሹክታ ድምፅ ይስማታል ምን እንደሚሉ ግን
አልተሰማትም። ቡናውን ወቅጣ ወደ ቤት ስትመለስ ሊባኖስ እና አቶ ኪዳኔ ዝምአሉ።
213 views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ