Get Mystery Box with random crypto!

ምርጥ ምርጥ ሀዲሶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ subhanela1 — ምርጥ ምርጥ ሀዲሶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ subhanela1 — ምርጥ ምርጥ ሀዲሶች
የሰርጥ አድራሻ: @subhanela1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 411
የሰርጥ መግለጫ

አሠላሙ አለይኩም ወራህመቱላሒ ወበረካቱ ውድ የቻናላችን ተከታታዮች ለዑማው ይጠቅማል ያልናቸውን ነገሮች በአላህ ፈቃድ እንለቅበታለን ብዙ ሀሳቦች አሉን እንዲያሣካልን ዱዐቹ አይለየን
☞ነሺዳዋች(መንዙማ)
☞ሀዲሶች
☞የተለያዮ ትምህርት ሰጪ ፅሁፎች ታገኛላቹ
ሀሣብ አስተያየት ካላችሁ @Mishkiya ላይ ይጠቁሙን
Leave channal ከማለትዎ በፊት ያልተስማማችሁ ነገር ካለ አሣውቁን

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-05-01 20:29:28 የኢድ ተክቢራ

የኢድ ተክቢራ

የኢድ ተክቢራ




اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ،
اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
وللَّهِ الحمد


اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ،
اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
وللَّهِ الحمد



اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ،
اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
وللَّهِ الحمد


اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ،
اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
وللَّهِ


اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ،
اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
وللَّهِ الحمد


اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ،
اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
وللَّهِ الحمد

Allahu Akbar Allahu Akbar Allahu Akbar, There is no god but God and God is greater God, praise be to God.

Allahu Akbar Allahu Akbar Allahu Akbar, There is no god but God and God is greater God, praise be to God


https://t.me/subhanela1
475 viewsሚ , 17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 20:27:31 #ከዒድ_እለት_ሱንናዎች_መካከል

1-      ከዋዜማው ጀምሮ ተክቢራ ማብዛት፣
2-     ገላን መታጠብ፣
3-     ቆንጆ ልብስ መልበስና ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
4-     ለዒድ ሶላት ከመውጣት በፊት ተምር ይሁን ሌላ ምግብ መቅመስ፣
5-     ወደ ሶላት ሲሄዱ ድምፅ ከፍ አድርጎ ተክቢራ ማለት፣
6-     ወደ ዒድ መስገጃ ቦታ በእግር መሄድ፣
7-     በዒድ ቦታ ላይ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል መገኘት ልጆችን ጨምሮ፣
8-     የእንኳን አደረሣችሁ መልዕክት መለዋወጥ፣
9-     ከዒድ ሶላት በፊት ዘካተልፊጥር መስጠት፣
10-    የዒድ ሶላት መስገድ፣
11-     ከሶላት በኋላ ኹጥባ ማዳመጥ፣
12-    በሄዱበት መንድ አለመመለስ፣
13-    በዒድ ቀን መደሠት፣
14-     ችግረኞችን መርዳት፣
15-    ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ዑለማን መዘየር
373 viewsሚ , 17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 07:10:30 ምርጥ ምርጥ ነሺዳዎችና ውብ ታሪኮች pinned «የትኛውን ነሺዳ እንጋብዛቹ»
04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 07:06:20 #ዘካተል_ፊጥር_የተደነገገበት_ጥበብ


➊ኛ ፆመኛ አካል በፆሙ ሰዓት ያስገኛቸው #ጉድለቶች ያጠራለታል። አንድ #ፆመኛ ሙሉ ለሙሉ ከጉድለት የፀዳ አይሆንምና #በፆሙ ሰአት የተከሰቱበትን ውድቅ ንግግሮች፣ ብልግናዎች፣ አላስፈላጊ ድርጊቶችና ሀራም ንግግሮች ሁሉ #ያፀዳለታል።

➋ኛ ለምስኪኖች ምግብ ይሆን ዘንድ ይሰጣል። ድሆች በአመት በዓል በደስታው ቀን እንዳያዝኑና በዚህ ቀን ለልመና እንዳይወጡ አመት በዓሉ ለሁሉም እኩል የደስታ ቀን ይሆን ዘንዳ እንዲወጣ የተደነገገ ነው።

➌ኛ በሙስሊሞች መካከል መተባበር፣ መዋደድ፣ መተጋገዝና መተዛዘን እንዲኖር የሚያደርግና አንድነታቸውን በተግባር የሚያሳዩበትም ጭምር ነው። በዚህ ተግባራቸው ምስኪኖችን መውደዳቸውና ቸርነታቸውን የሚያሳዩበት ነው።

➍ኛ ለሙእሚኖች አላህ በዚህ ትልቅ ወር ላይ የዋለላቸው ኒእማና ፀጋ የሚገልፁበትም ጭምር ነው። በዚህ በተከበረው ወር ቀኑን እንዲፃሙ፣ ሌሊቱን እንዲቆሙ እንዲሁም የተለያዩ ኢባዳዎች ላይ ሆነው በሰላም እንዲያሳልፋ ስላደረጋቸው ለዚ ትልቅ ውለታ ሰደቃ በመስጠት ለጌታቸው ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው።

--------------------
mohammed ebnu seid
-----------------------------

በቴሌግራም ይ ላ ሉን!



@subhanela1
389 viewsሚ , 04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 15:45:16
የትኛውን ነሺዳ እንጋብዛቹ
Anonymous Poll
44%
የሩህ መስከረም
19%
ማን ባሻገረኝ
38%
ፊዳከ 2
64 voters454 viewsሚ , 12:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-23 09:52:41 በለይለቱል ቀድር ጊዜ የሚባለው ዱዓ፦

አላህ ሆይ! አንተ ይቅር ባይ ነህ፤ ይቅርታንም ትወዳለህ፥ ይቅር በለኝ” ነው፦ ጃሚዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 48 ሐዲስ 144

ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ እኔም፦ *”የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ሆይ! የትኛው ሌሊት ለይለቱል ቀድርን እንደሆነ ባውቅ ምን ማለት እንዳለብኝ ንገሩኝ” ብዬ ጠየኳቸው፥ እርሳቸውም፦ “አላህ ሆይ! አንተ ይቅር ባይ ነህ፤ ይቅርታንም ትወዳለህ፥ ይቅር በለኝ” የሚል ነው”*። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قُلْتُ يَا رَسُولَ اللَّهِ أَرَأَيْتَ إِنْ عَلِمْتُ أَىُّ لَيْلَةٍ لَيْلَةُ الْقَدْرِ مَا أَقُولُ فِيهَا قَالَ ‏ “‏ قُولِي اللَّهُمَّ إِنَّكَ عَفُوٌّ كَرِيمٌ تُحِبُّ الْعَفْوَ فَاعْفُ عَنِّي ‏”‏ ‏.‏ قَالَ هَذَا حَدِيثٌ حَسَنٌ صَحِيحٌ ‏

https://t.me/Subhanela1
466 viewsሚ , 06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-25 20:26:25 ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ተናገሩ"አንድ ሰው በሞተ ጊዜ ዘመዶቹ በቀብር
ሥነስርአቱ ላይ ሲጨናነቁ አንድ እጅግ ያማረ ቆንጆ ሰው
በጭንቅላቱ በኩል ይቆማል።ጀናዛውም እንደተከፈነ ያ ሰው
በከፈኑ እና በሞተው ሰው ደረት መሀል ይሆናል።ከቀብር
ሥነስርአቱም በህዋላ ቀባሪ ቤተሰቦቹ ወደ ቤት ሲመለሱ ሁለት
ሙንከር እና ነኪር የተባሉ ምላኢኮች ወደ ቀብሩ በመምጣት
ጀናዛውንና ያንን ቆንጆ ሰው በመለያየት ያንን የሞተውን ሰው
በእምነቱ ጉዳይ ብቻውን በጥያቄ ሊያፋጡት ይሞክራሉ ። ሆኖም
ያ ቆንጆ ሰው ይናገራል "ይህ ሰው አጋሬም ጋደኛዬም ነው
ብቻውንም ልተወው አልችልም። እናንተ እንድትጠይቁት
ከተመደባቹ ስራችሁን መሥራት ትችላላቹ እኔ ግን ወደ ጀነት
መግባቱን ሳላረጋግጥ ትቼው እልሄድም"። ከዝያም ወደ ሞተው
አጋሩ በመዞር እንዲህ ይለዋል "እኔ አንዳንዴ ድምፅህን ከፍ
አርገህ ሌላ ጊዜ ደግሞ ቀስ ብለህ ስታነበኝ የነበርኩት ቁርአን
ነኝ ምንም አትጨነቅ፤ ከሙንከርና ነኪር ጥያቄና መልስ በኃላ
ምንም ጭንቀት አይኖርብህም"፤ጥያቄና መልሱም ካለቀ በኃላ ያ
ቆንጆ ሰው አል ማሉል አላ በተባሉ የጀነት መላኢኮች የተዘጋጀ
በመልካም ሽታ የሚያውድ እና ከ ሀር በተሰራ ልብስ የተዘጋጀ
አልጋ ያዘጋጅለታል።
2. ረሰል(ሶ.ዐ.ወ) እንደተናገሩት በቂያማ ቀን በአላህ ሱ.ወ ፊት
ስንቆም ከቁርአን የበለጠ ለኛ ሚከራከርልን አይኖርም
ከነብይያትም ከ መላኢኮችም በበለጠ።
3. እባክዎን ይህን መልእክት የቻሉትን ያህል ያስተላልፉ። ረሱል
(ሶ.ዐ.ወ) እውቀትን ከኔ ለሌላው አስተላልፉ አንድም አረፍተ ነገር
ብትሆን እንኩዋን ብለዋል።
4. ይህ መልእክት በ አላህ ፍቃድ በቀጣይ 7 ቀናት ቢያንስ 5
ሚልዬን ሰዎች እንዲዳረስ ዱአ እያደረግን ነው።
እባክዎን ይህን መልእክት ለ ቤተሰብዎ፣ ለዘመድዎትና
ላሚያውቅዋቸው ሁሉ በማስተላለፍ ከተትረፈረፈው የአላህ ምንዳ
ተጠቃሚ ይሁኑ።

@finding_hubullah
1.7K views(。 ‿ 。), 17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-19 23:00:12 ምርጥ ትውልዶች
============

በዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ዘመን ሶስት ወጣቶች አንድ ስውዬን ጎትተው
በማምጣት ያዐሚረል ሙእሚኒን ይህ ሰው አባታችንን ገድሏል ሀድ/
ቅጣት/ እንደትወስንበት እንሻለን በማለት ተናገሩ።
‌‌
ለምን ገደልክ ? ሲሉ ዑመር ጠየቀ
‌‌
‹‹ እኔ የግመል እረኛ ነኝ አንደኛው ግመሌ የአባታቸው መሬት ላይ ካለ
ዛፍቅጠል ቀንጥሶ ሲበላ አባታቸው ድነጋይ ወርውሮ ሲመታው ግመሌ
ሞተ እኔም እሱ የወረወረውን ድንጋይ አነስቼ ስወረውር መታሁትና ሞተ…
ሲል ተናገረ።
‌‌
‹‹እንደዛ ከሆነ ቅጣት እወስንብሃለሁ! አሉ ዑመር ።
‌‌
‹‹እሺ ሦስት ቀናትን አቆየኝ …… አባቴ ሲሞት ለኔና ለወንድሞቼ የተወው
ከንዝ/የተደበቀ ሃብት/አለ እኔ አሁን እዚሁ ከሞትኩ ከንዙም ይጠፋል
ወንድሞቼም ይጠፋሉ (ይቸገራሉ) ስለዚህ
ፍቀድልኝና ሄጄ ልምጣ አለ።
‌‌
ታዲያ እሰክትመለስ ዋስ የሚሆንሀ ማነው? በማለት ዑመር (ረድየሏሁ
አንሁ) ጠየቁ።
‌‌
ሰውዬው የተሰበሰቡትን ሰዎች ተመለከተ የሚያውቀው የለም……
የእያንዳንዱን ፊት ተመለከተ እና ያ ሰውዬ ሲል ጠቆመ።
‌‌
ያ አባ ዘር ለዚህ ሰው ዋስ ትሆናለህ? በማለት ዑመር (ረድየሏሁ አንሁ)
ጠየቁ
‌‌
አዎን ያ አሚረል ሙእሚኒን በማለት መለሰ።
‌‌
ይህ ሰው ካመለጠ ቅጣቱ አንተ ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን አታውቅም
እንዴ? ሲል ዑመር ተገርሞ ጠየቁ ግድ የለም ያአሚረል ሙእሚኒን እኔ
ዋስ እሆነዋለሁ …. ሲል አቡዘር መለሰ። ሰውየው ሄደ።
‌‌
አንድ ቀን አለፈ….ሁለተኛው ቀን ተከተለ…በሦስተኛው ቀን ሰውየው
ካልመጣ ቅጣቱ አቡዘር ላይ ስለሚፈፀም ሰዎች ተጨነቁ ……… ሆኖም
የዛን ቀን ከመግሪብ በፊት ያሰው እያለከለከ መጣ እንደደከመው
ገፅታው መስካሪ ነበር። ከዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ፊት ለፊት መጥቶ
በመቆም
‌‌
‹‹ከንዙን ለወንድሞቼ እና ለእናቴ ወንድሞች አስረክቤ መጣሁ አሁን
በቁጥጥርህ ስር ሆኛለሁ ቅጣቱን ፈፅምብኝ በማለት ተናገረ።
‌‌
ዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ተገረመ በዚያው ማምለጥ የምትችል ሆነህ
እንዴት ተመለስክ? ሲል ጠየቀው።
‌‌
‹‹ ሰዎች ዘንድ ቃል አክባሪነት/ጠባቂነት/ጠፋ እንዳይባል ፈርቼ ነው››
በማለት መለሰ።
‌‌
ዑመር ወደ አቡዘር ዞሮ ይህን ሰው እንዴት ዋስ ሆነከው? በማለት ጠየቀ
‌‌
‹‹እኔማ ዋስ የሆነኩት በሰዎች ዘንድ ኸይር (መልካም ስራ) ጠፋ
እንዳይባል ፈርቼ ነው›› ሲል አቡ ዘር መለሰ። በሁኔታው
የሟች ልጆች ልብ ተነካ በቃ አፉ ብለነዋል ቅጣቱ እንዳይፈፀምበት ሲሉ
ተናገሩ
‌‌‌
ዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ለምን? ሲል ጠየቃቸው…..‹‹እኛ ደግሞ
በሰዎች መሃል ይቅር መባባል ጠፋ እንዳይባል እንፈራለን›› አሉ
ሱብሃነላህ
‌‌
እኔ ደግሞ ሰዎች የሰሙትን አያደርሱም እንዳይባል ሰጋሁ እና
ነገርኳችሁ፡፡ @subhanela1
1.2K viewsሚ , 20:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-18 07:16:06 :መልካም ጎደኛ::::::::::

ኢማሙ አል ሻፊዒ እንዳሉት

የጀነት ሰዎች ጀነት በገቡ ጊዜ በዱንያ ላይ በመልካም ነገር ላይ የነበሩ ጎደኞቻቸውን ጀነት ውስጥ ሲያጧቸው አሏህን እንዲህ ሲሉ ይጠይቃሉ

" ጌታችን ሆይ ከኛ ጋር ሲሰግዱ እና ሲፆሙ የነበሩ ጎደኞች ነበሩ ጀነት ላይ አጣናቸው " ብለው ይጠይቃሉ ፡ አሏህም እንዲህ ይላቸዋል ፡ ወደ እሳት ሂዱና ከቀልቡ የዘር ፍሬ የምታክል ኢማን ያለውን ሰው አውጡ ይላቸዋል ,

ሀሰን አል በስሪ አሏህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ ፦

ሙእሚን የሆኑ ጎደኞችን አብዙ 、 የቂያም ቀን አሏህ በፈቃዱ መሸምገልን ይሰጣቸዋል እና,
ኢብኑ አል ጀውዚ አሏህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ ፡

☞በጀነት ውስጥ በመካከላችሁ ካጣችሁኝ , ስለኔ ጠይቁ ፡ ጌታችን ሆይ ያ ባሪያ በዱንያ ላይ ስላንተ ያስታውሰን ነበር የት አለ በሉ ከዛም አለቀሱ።

☞ ወዳጆቼ በጀነት ውስጥ ካጣችሁኝ ስለኔ ጠይቁ ምናልባትም በአሏህ መንገድ ላይ አንድ ጊዜም ቢሆን ስለሱ ታላቅነት ፣ ፈጣሪነት አስታውሻችሃለሁና።

አሏህ ሆይ ! ያንተን ትእዛዝ በመፈፀም ላይ የሚያበረታቱኝን መልካም ጎደኞች አብዛልኝ ወዳጆቼም ጋር በጀነት አል ፊርደውስ አንድ ላይ ሰብስበኝ ...አሚንንንንን
@subhanela1
956 viewsሚ , 04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-17 06:58:24 በጣም የምታምረዋ ልጅ በትዳር ፍለጋ

የምታምረዋ ልጅ ማግባት ትፈልጋለች ነገር ግን በጣም ፃዲቅ ሰው ነው ምትፈልገው፡፡በቀን ቀን ሙሉ ቁርዐን የሚቀራ፣ አመቱን ሙሉ የሚፆምና ለሊቱን ሙሉ በቁኑት የሚያሳልፍ ወንድ ነበር የፈለገችው፡፡በጣም ታምራለችና ወንድ የተባለ ሁሉ ሊያገባት ይፈልጋል ነገር ግን ያስቀመጠችው መስፈርት ከባድ ስለነበር ማንም ሊደፍር አልቻለም፡፡አንድ ልጅ በድፍረት እስኪመጣ ድረስ፤ ይህ ልጅ ያስቀመጠችውን መስፈርቶች ሁሉ እንደሚያሟላ ፈርሞ ኢማሙ ያጋቧቸዋል፡፡
በዛው በተጋቡ እለት ሚስቱ ሙሉ ቁርዐን ሲቀራም ይሁን ቀኑን ሲፆም አልያም ለሊቱን ሰላት ላይ ሲቆም አልተመለከተችም፡፡ ለውጥ ካለ ብላ ለአንድ ሳምንት ተከታተለችው ነገር ግን ምንም ለውጥ የለም፤ ስለዚህም ቅሬታዋን አቅርባ ከልጁ ጋር እንዲያፋቷት ጠየቀች፡፡ሁለቱንም ዳኛ ፊት አቆሟቸውና ዳኛው ጠየቀ “የጋብቻ ስምምነታችሁ ምን ነበረ?” አሉት፤

ልጁም “በየቀኑ ሙሉ ቁርዐን እንድቀራ፤ አመቱን ሙሉ እንድጶምና ለሊቱን በሰላት እንዳሳልፍ ነበር” ብሎ መለሰ፤

ዳኛው “ታዲያ የተጠየከውን አሟላህ?”

ልጁ “አዎ”

ዳኛው “ውሸታም! መች አሟላህ ? ሚስትህ ቅሬታ ያቀረበችው ከመስፈርቶቹ አንዱንም እንዳላሟላህ ነው፤ ለዛም ነው ፍቺ የጠየቀችው”

ልጁ አሟልቻለሁ ብሎ ድርቅ አለ፡፡

ዳኛው “በየቀኑ ሙሉ ቁርዐን ትቀራ ነበር?”

ልጁ “አዎ”

ዳኛው “ሚስትህ ግን አላየሁትም እያለች ነው፤ ታዲያ እንዴት አርገህ ነው ምትቀራው?”

ልጁ ረጋ ብሎ “በቀን ሶስት ጊዜ ሱረቱል ኢህላስ(ቁል ሁወላሁ አሃድ..) እቀራለሁ፤ መልዕክተኛው(ሰ.ዐ.ወ) ሶስት ጊዜ ሱረቱል ኢህላስን የቀራ ሙሉ ቁርዐን እንደቀራ ነው ብለዋልና” ብሎ መለሰ፤

ዳኛው በመገረም “ታዲያ አመቱን ሙሉ እንዴት ትጶማለህ?” አሉት

ልጁ “የረመዳንን ወር ሙሉ እፆማለሁ ከዛም ከሸዋሉ ስድስት ቀን ጨምሬ እፆማለሁ፤ መልዕክተኛው(ሰ.ዐ.ወ) ረመዳንን ሙሉ ወር የፆመ ከሸዋል ስድስት ቀን ያስከተለ አመቱን ሙሉ እንደፆመ ይቆጠራል ብለዋልና”

ዳኛው ተሳስተሀልም አላሉትም ለትንሽ ጊዜ ዝም አሉና ለዚህ መልስ አያገኝለትም ብለው “ሚስትህ ተኝተህ እንደምታድር ነው የነገረችን ታዲያ እንዴት ነው ለሊቱን ቆመህ አላህን እየተገዛህ ምታሳልፈው?” ብለው ጠየቁት

ልጁ እንደ ቅድሙ ረጋ ብሎ “ኢሻ ሰላትን በጀምዐ እሰግዳለሁ በቀጣዩ ቀን ሰላተ ሱብሂን በጀምዐ እሰግዳለሁ፤ መልዕክተኛው(ሰ.ዐ.ወ) ሰላተል ኢሻንና ሰላተ ሱብሂን በጀምዐ የሰገደ ለሊቱን ሙሉ አላህን ሲገዛ እንዳደረ ይቆጠርለታል ብለዋልና” ብሎ መለሰላቸው፡፡

ዳኛው በአግራሞት ተነስተው ልጁን አዩትና በሰላም እንዲለቁት ተናገሩ “ሂድ አንተ ሂድ በቃ!! በጋብቻህ ምንም ጥፋት አላየሁም” አሉት፡፡
@subhanela1
947 viewsሚ , 03:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ