السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ታላቅ ዳዕዋና ኮንፈረንስ በኢትዮጵያ እነሆ በአሏህ ፍቃድ ወሎ ኮምቦልቻ ከተማ አንሷር መስጅድ የፊታች እሁድ ቀን 18/03/ 2015 ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት በታላላቅ ከውጭ በመጡ አሊሞችና የሃገራችን አሊሞች መሻኢኾች እና ኡስታዞች ታላቅ የዳዕዋ ፣ የፈትዋ እና የኮርስ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ይጠብቃቹሃል... በዕለቱ ብዙ ታዳሚ ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል። በእለቱ ከሚገኙ ከውጭ ሀገር ታላላቅ ኡለማዎች መሃል 1) የተከበሩ ሸይኽ አቢ ዐማር ሙሐመድ ኢብኑ ዐብዲላሂ ባሙሳ - فضيلة الشيخ محمد بن عبد الله با موسى - حفظه الله تعالى 2) የተከበሩ ሸይኽ ረሻድ አል-ሑበይሺይ - فضيلة الشيخ رشاد الورد الحبيشي حفظه الله 3) የተከበሩት ሸይኽ ሙሳ አሕመድ አል ቀጧኒ فضيلة الشيخ موسى احمد القطاني እና ሌሎችም ውድ የሰለፊያ ኡስታዞች እና ወንድሞች ከ አፋር ከአዲስ አበባ ከደሴ ከኸሚሲይ እንዲሁም ከተለያዩ ቦታዎች በአለሠህ ፍቃድ ይዘምታሉ። በዕለቱ :- የኮርስ ፕሮግራም ይካሄዳል የደዕዋ ፕሮግራም ይካሄዳል በመሻኢኮቻችን ነሲሃ ይደረጋል የፈትዋ ፕሮግራም ይኖረናል ማሳሰቢያ :- ማንኛውም ስለማንኛውም ነገር ሹብሃ ያለበትም አካል ጥሪ ሳይደረግለትም መምጣት ይችላል በራችን ክፍት ነው ። በቂ ምግብ እና የመኝታ ቦታ ተዘጋጅቷል ... ከቅዳሜ ጀምሮ ኢትዮጵያውያን ይህንን ውድ ፕሮግራም ለመታደም ወደ ኮምቦልቻ አንሷር መስጅድ እብድታመሩ ስንል ጋብዘናቹሃል። ማሳሰቢያ የሌሊት ልብስ ይዛችሁ ብትመጡ የተመረጠ ነዉ። አድራሻ :- ኢትዮጵያ ኮምቦልቻ ከተማ ሀሰና ሀገር ክፍል ከተማ ቀበሌ ሁዳዴ በርበሬ ወንዝ አድሱ ድልድይ ተሻግሮ ደዌ ሰፈር በአንሷር መስጅድ t.me/Ye_kombolcha_Ansuar_Mesjid_Jemea t.me/Ye_kombolcha_Ansuar_Mesjid_Jemea 450 views05:00