2022-05-20 21:21:53
ያልተባልናቸው ነገሮች!!
1. እንደህፃናት ሁኑ (child-like) እንጂ ህፃናት ሁኑ (childish) አልተባልንም!
ማቴ 18:2-3, 1ኛ ቆሮ 11:13
2. በአምሮአችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ አዕምሮአችሁን ቆልፉ አልተባልንም!
ሮሜ 12:2
3. አገልግሎታችሁ ለሰው ህሊና እና አዕምሮ የሚመች ይሁን እንጂ ለራሳችሁ የሚመች ይሁን አልተባልንም!
ሮሜ 12:1, 1ቆሮ8: 9-13
4. ዝለፍ ገስፅ ምከር ( 2ጢሞ 4:2) ስንባል ውስጠ መነሻው(motive) ሰዎችንከተያዙበት ቀንበር በእግዚአብሔር መንፈስ ሃይል ማላቀቅ ከሚሄዱበት የተሳሳተ መንገድ መመለስ እንጂ የሰዎችን ቅስም መስበር ይሁን አልተባልንም!
5. የጨለማን ስራ ግለጡ እንጂ የደከመውን ሰው ገመና አጋልጡ አልተባልንም!
ኤፌ 5:11-13
6. እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ እንጂ እርስ በርሳችሁ ተሽነጋገሉ አልተባልንም!
ሮሜ 12:10
7. እንደ ርግብ የዋሆች (innocent) ሁኑ እንጂ ምንም የማታመዛዝኑ ሞኞች ሁኑ አልተባልንም!
ማቴ 10:16
8. ክፉውን በክፉ ፈንታ አትመልሱ እንጂ ክፉውን አትቃወሙ አልተባልንም!
1ጴጥ 4:9
9. ሁሉን ፈትኑ እንጂ ሁሉን በጭፍን ተቃወሙም ተቀበሉም አልተባልንም!
1ኛ5:20-21
10. የሚላችሁን ሁሉ (ጌታ/ኢየሱስ/ ቃሉ/መንፈሱ) አድርጉ እንጂ የሚሉአችሁን ሁሉ (ሰዎች/የሰው ፈቃድ/ስጋና ደም) አድርጉ አልተባልንም!
ዮሐ 2:5
ተባረኩልኝ!
ለዓለም ጥላሁን (ዶ/ር)
05/17/22 ተፃፈ
@KALTUBE
@KALTUBE
@KALTUBE
@shekayinah
264 viewsYabinasa, edited 18:21