Get Mystery Box with random crypto!

#መንፈስቅዱስ #ማነው ? (2) ~»>መንፈስ ቅዱስ አካል አለው ~»'መንፈስ' የሚለውን ቃል በእብ | መንፈስ ቅዱስ 𝐇𝐎𝐋𝐘 𝐒𝐏𝐈𝐑𝐈𝐓

#መንፈስቅዱስ #ማነው ? (2)

~»>መንፈስ ቅዱስ አካል አለው
~»"መንፈስ" የሚለውን ቃል በእብራይስጥ "ሩህ" በግሪክ "ኑማ" ከሚነፍስ ንፋስ ጋር ያገናኘዋል ከዚህ የተነሳ መንፈስቅዱስን አካል የሌለው የሚነፍስ ኃይል አርጎ የመረዳት አዝማሚያዎች አሉ
~»>መንፈስቅዱስ እንደ አብ እና ወልድ ሁሉ አካል ያለው መሆኑን በቅዱሳን መፅሀፍት ተፅፎአል::
~»በተደጋጋሚ "እኔ" አያለ በመናገሩ ምክንያት አካል ያለው መሆኑን ያሳያል
ዮሐንስ 14
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵-¹⁶ ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤
¹⁷ እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ።
“አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።”
— ዮሐንስ 14፥26
ዮሐንስ 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል።
¹⁴ እርሱ ያከብረኛል፥ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና።
~»>እየሱስ ክርስቶን በመተካት ሌላ አፅናኝ (ጳራቅሊጦስ) በመባሉ
“.....ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤”
— ዮሐንስ 14፥15-16
~»>መንፈስ ቅዱስ እውቅት ስሜት ፈቃድ ያለው አምላክ ነዉ::
“አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።”
— ዮሐንስ 14፥26
“ይህን ሁሉ ግን ያ አንዱ መንፈስ እንደሚፈቅድ ለእያንዳንዱ ለብቻው እያካፈለ ያደርጋል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥11
“ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ።”
— ኤፌሶን 4፥30
(እብ 3:7-9 ሐዋ 16:6)

ተባርካችሁአል!