Get Mystery Box with random crypto!

Awe

የቴሌግራም ቻናል አርማ roviben — Awe A
የቴሌግራም ቻናል አርማ roviben — Awe
የሰርጥ አድራሻ: @roviben
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1
የሰርጥ መግለጫ

Yidiyd

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-06 22:27:35
6.4K views19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 22:26:58 ታሪኩ የሚጀመረው በ 2002 ዓ.ም ከቤሩት ወደ አዲስአበባ የሚበረውና ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አይር መንገድ የሆነው ቦይንግ 787 አውሮፕላን ተከስክሶ ከ90 ሰዎች ጋር ባሏ የሞተባት ሎዛ የተባለች ትንታግ ገፀ-ባህሪ የአደጋውን መንስዔ በራሷ መንገድ ለማጣራት የምታደርገውን ውጣ ውረድ በመተረክ ነው።
የሎዛ ይህ ድርጊት በኢትዮጵያና በሊባኖስ አይር መንገዶች አልተወደደላትም። እንዲያውም በግዙፉ ቦይንግ ካምፓኒ እንደ ጭራቅ እንድትታይና እሷን ማስወገድ የመጨረሻ አማራጫቸው አድርገው እንዲወስዱ አነሳሳቸው።

ሳታውቀው እንዲህ አይነት አጣብቂኝ ውስጥ የገባችው ሎዛ ገለልተኛ የአደጋው መንስኤ አጣሪ ኮሚቴ ያወጣውን ድምዳሜ ስታይ ይብሱኑ እንድትበሳጭና ነገሩን ገፍታበት ትክክለኛውን የአደጋውን መንስዔ በራሷ መንገድ ማጣራት በአደጋው ለተቀጨው ባሏ ጥልቅ ፍቅሩን የምትገልጽበት አይነተኛ ማካካሻ አድርጋ ወሰደችው።

ግን ደግሞ የውርደት ካባ ላለመከናነብ በመላው ዓለም የዕዝ ሰንሰለቱን የዘረጋው የቦይንግ ካምፓኒና ስሙ ምስጢራዊ የሆነ ድርጅት ሎዛን ለማስወገድ የመጨረሻ ካርዳቸውን መዘዋል--ግብግቡ የሚጀምረው እዚህ ጋ ነው እንግዲህ !

መጽሐፉ ልቦለዳዊ ቢሆንም የተከሰቱ እውነተኛ ሁነቶች ላይ ተንተርሶ የተጻፈ ነው(በ2002 ዓ.ም ከቤሩት አዲስአበባ በረራውን ያደረገ ቦይንግ 787 አውሮፕላን ተከስክሶ 90 ያህል ሰዎች እንደተቀጠፉ ልብ ይሏል )።

በተያያዘና ተመጋጋቢ በሆነ ሁኔታ የተማሩ የኢትዮጵያ ምሁራን ከዚህ በፊት ባልተካሄደበት መንገድ ኢትዮጵያን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ቁጥር አንድ ሀገር ለማድረግ እንቅስቃሴውን ሲያጧጥፉ መጽሐፉ ይተርካል። እነዚህ ምሁራን ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አፍሪካን በቴክኖሎጂ ለማመንደግ የተነሳሱ ናቸው። ይህ ሁኔታ የእርዳታ ድርጓቸውን እየበተኑ ጥሬ እቃችንን በሚያጋብሱ ምዕራባውያን አልተወደደም--ሌላ ግብግብ!


በመጨረሻም ኢትዮጵያ በራሷ ባንዲራ ያጌጠች ሳታላይት ስታመነጥቅ የመጽሐፉ ሽፋን ላይ ይታያል።( ልብ በሉ! ይህን ሽፋን ይዞ መጽሐፉ የታተመው በ2008 ዓ.ም ነው)። ይህ ነገር መጽሐፉን ትንቢታዊ ያደርገዋል። ምክኒያቱም ከሁለት ዓመት በኋላ በቻይና ጀርባ አሳዝላም ቢሆን ኢትዮጵያ የራሷን ሳታላይት አመጥቃለች!


ሌላውን ከመጽሐፉ ......

መጽሐፉን በነጻ በ PDF ለማውረድ ከታች ያለውን link ተጠቀሙ!!!

ምርጥ :ልብ አንጠልጣይ
:ፍቅርን
:ስለላን
:ሳይንስን
:ትንቤትን
:መድሃኒቶችን አጠቃሎ የያዘ!!!!

*እመኑኝ.አንዴ ከከፈታችሁ ሳትጨርሱ አታቆሙም!

*ኢትዮጵያን የሚወድ ያንብበው!!!
ብርሃኑ በቀለ ሰንዶታል!!!
*NB..የፈጠራ ክህሎት ያላችሁ ምናባችሁን ስለሚያሰፋው ሳታነቡት አትለፉ!!

መልካም ንባብ
6.4K views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 21:54:26 ድሳካር.pdf
ድሳካር.pdf


ምርጥ :ልብ አንጠልጣይ
:ፍቅርን
:ስለላን
:ሳይንስን
:ትንቤትን
:መድሃኒቶችን አጠቃሎ የያዘ!!!!

*እመኑኝ.አንዴ ከከፈታችሁ ሳትጨርሱ አታቆሙም!

*ኢትዮጵያን የሚወድ ያንብበው!!!
ብርሃኑ በቀለ ሰንዶታል!!!
*NB..የፈጠራ ክህሎት ያላችሁ ምናባችሁን ስለሚያሰፋው ሳታነቡት አትለፉ!!

*NB..ኢትዮጵያዊነት የሚያንገሸግሻችሁ አታንብቡት!!
9.5K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-10 17:37:20
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሰራው ሃጢያት ነው::
ያዕ-4:17

በትንሳዔ ዋዜማ ለበጎ ስራ ተነስተናል::

ለማንኛውም እርዳታ 09-40-20-67-87
09-21-32-45-80
09-20-70-77-92
4.7K views14:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-27 23:38:07
AB PHOTOGRAPHY

#ትህትና

የአራቱም ደብር አስተዳዳሪዎች ለህዝቡ ሰላምታ ሲሰጡ

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
11.3K views20:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-27 22:23:53 ከመጻሕፍት ዓለም በ pinned «Watch "#Hakim Tube (ሐኪም ቲዩብ)" on YouTube https://youtube.com/channel/UCjBX6HQ06XOdev2OZ2X56EQ ስለጤናዎ ማወቅ ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ በሀኪሞች የተዘጋጀ የበሽታዎች መንስኤ፣መከላከያ መንገድና መድሀኒቶችን በቻናላችን በቀላሉ ያገኛሉ Do you want to know about your health condition?…»
19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-27 22:23:44 Watch "#Hakim Tube (ሐኪም ቲዩብ)" on YouTube
https://youtube.com/channel/UCjBX6HQ06XOdev2OZ2X56EQ

ስለጤናዎ ማወቅ ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ በሀኪሞች የተዘጋጀ የበሽታዎች መንስኤ፣መከላከያ መንገድና መድሀኒቶችን በቻናላችን በቀላሉ ያገኛሉ



Do you want to know about your health condition? Then subscribe this channel and you'll get disease descriptions ( cause, prevention) and treatment.
A channel prepared by Ethiopian Doctors in Amharic .
12.6K views19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 22:17:23 ክፍል 2

ኡኡኡኡኡኡኡኡኡ....ከወደውጪ ድምፅ ተሰማ፡፡ አስር አለቃ ጎረቤታቸውን በዱላ አናቱን ብለው በሩ ላይ ደፍተውት ነበር፡፡

ሰይጣን አጀንዳውን ይዞ አስር አለቃ ግቢ ሲደርስ ነገር ተደበላልቆ ጠበቀው፡፡ ጉዳዩን በጥንቃቄ አጣራና አጀንዳው ላይ እንዲህ ሲል ከተበ "የአስር አለቃው ጉዳይ ከእቅድ በላይ ተፈፅሟል፡፡"

ሦስት ፖሊሶች ኮሌታቸው ጨምድደው ወደያዟቸው አስር አለቃ ጆሮ ጠጋ አለና "አንተ ሸፋፋ! ስማ..! አሁን በግድያ ሙከራ ዘብጥያ ትወርዳለህ የተበደረው ጎረቤትህ ተሽሎት ወደ ቤቱ ይመለሳል..፡፡ ያች አንቋራሪ ልጅህም የትም ስታንቋር

ር ስለምትውል ቤትህ ሰው የለም፡፡ ሚስትህና ጎረቤትህ ብቻቸውን እዚህ ሰፊ ግቢ ራስህ አልጋ ላይ...ሂሂሂሂሂሂ ቂቂቂቂቂቂ አይ ሸፋፋው!!

ይልቅ ሚስትህን ዓይንህ እያየ ከምትወሰድ አንዱን ፖሊስ በካራቴ ድፋውና አምልጥ...ወታደር አይደለህ...? አስር አለቃ አይደለህ?.... ኮማንዶ ነኘ እያልክ በየጠላ ቤቱ ስታወራ አልነበር...? ወይስ ዝም ብለህ ስትወሽክ ነው...፡፡"

አስር አለቃ ቀስ ብለው ከጎናቸው የቆመውን ፖሊስ ተመለከቱት፡፡ክስት ያለ ነው...በዛ ላይ የያዘው መሳሪያ የከበደው ይመስላል፡፡ ሁለቱም ፖሊሶች ቢሆኑ ያን ያህል የሚስፈሩ አይደሉም ቀድረ ቀላል ነገር ናቸው፡፡ " ይሔኔንንስ መሣሪያውንም መንጠቅ አያቅተኘ " ሲሉ አሰቡ፡፡ ፖሊሶቹ አስር አለቃን እያጣደፉ ወደ ጣቢያ ወሰዷቸው፡፡

ዷ....! ዷ............መንደርተኛው ከሩቅ የተኩስ ድምፅ ሰማ

"ምንድነው....?"

"እስረኛ ሊያመልጥ ሞክሮ.....ፖሊሶቹ እግሩን ሰንክለው አቆሙት.....!

ሰይጣን በሳቅ ፍርስ አለ፡፡ እናም አጀንዳው ላይ እንዲህ ሲል ፃፈ "የእግሩ ጉዳይ አልቋል አሁን ነፍሱን ማንሻፈፍ ይቀረኛል!!"

ከዛም ሰይጣን ቀይ እስኪሪቢቶ አወጣና እየተፍነከነከ እንዲህ ሲል ፃፈ

"አስር አለቃ አምሳ አለቃ መቶ አለቃ ሻለቃ ጄነራል ሚኒስተር ...ጠቅላይ ሚኒስተር ሁሉም እግር አላቸው፡፡ እንኳን እነርሱ አገርም እግር አላት ስንፈልግ እናንሻፍፋታለን!!!"

ደራሲ #አሌክስ_አብርሃም
#ዙቤይዳ ከሚለው መፅሐፍ

#እግር_በእግር
ለንባብ እንዲመች ተደርጎ የተወሰደ

@jahABP ነኘ አስተያየታችሁን አድርሱኘ

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
26.2K views19:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 18:07:05
AB PHOTOGRAPHY


r.....for reflection

ምስሉን ተጭነው ይመልከቱ ቴክኖ ስፓርክ kb ወንድሜ ስልክህን እንዳነሳበት ስለሰጠኸኘ አመሰግናለሁ

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
16.1K views15:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 18:04:50 AB PHOTOGRAPHY & GRAPHIC DESIGN

#እግር_በእግር

አንድ ቀን ሰይጣን በመንደሩ ወደሚፈሩት እና ወደ ሚከበሩት አስር አለቃ ደባልቄ ግዛው ቤት ሔደና ቀዳሚሚ ተከታይም ሳያደርግ "ደባልቄ!!" ብሎ በስማቸው ጠራቸው፡፡

አስር አለቃ ፊታቸውን በቁጣና በግርምት አኮማትረው ድምፁን ወደሰሙበት ዞር ቢሉ በአካባቢው ሰው የሚባል የለም፡፡ እዚህ ሰፈር አንድም ሰው የአስር አለቅነትን ማዕረጋቸው ሳያስቀድም የአባቻቸውን ስም ሳያስከትል እንዲህ ንፋስ እንዳነሳው ፌስታል ስማቸውን ለብቻው አንጠልጥሎ የሚነሳ ሰው የለም፡፡

እንኳን ሰው የዚህ ሰፈር ሰይጣን ቢሆን ራሱ እንደዚህ አስር አለቃን አቃሎ እና አበሻቅጦ ይጠራቸዋል ተብሎ አይታሰብም፡፡ እንዴት ሆኖ! ምን ሲደረግ...!

እንግዲህ አስር አለቃ የተጣሉ ባልና ሚስት አስታርቀው ገና መመለሳቸው ነበር፡፡ ልክ በራቸው ላይ ሲደርሱ ነው ሰይጣን የጠራቸው፡፡ ምን ይጠራቸዋል ያዋረዳቸው እንጂ! ቢሆንም 'ጆሮዬ ነው' ብለው ወደ ቤታቸው ግቢ ሊገቡ ርምጃ ሲጀምሩ፣

"አንተ ደባልቄ ! የሚደባልቅ ይደባልቅህ! ሲጠሩ አትሰማም!? ደንቆሮ!!" ብሏቸው እርፍ፡፡ በዚህ ቢበቃማ ጥሩ ነበር "ምን ያራሩጥሃል? ያቺ መንሽ እግር ሚስትህ እንደሆነች የትም አትሔድብህ ተወዝፋ ነው የምትጠብቅህ" ሲል ዘለፋቸው፡፡

አስር አለቃ መጀመሪያ በተናጋሪው ድፍረት ግርርርርርርርርምምምምምም አላቸው ቀጥሎ የንግግሩ ትርጉም አዕምሮአቸው ውስጥ ሲተረጎም ደማቸው ፈላ፡፡ ላለፉት አርባ ዓመታት እንዲህ ተንቀውም እንዲህ ደማቸው ፈልቶም አያውቅም፡፡ ከዘራቸውን ጠበቅ አድርገው ጨበጡና ድምፁን ወደሰሙበት ፎክረው ዞሩ፡፡

"ያንበሳው ግልገል!" በአካባቢው የሰው ዘር የለም!!

"እንኳን ፊቴ ያላገኘሁት ደመ ከልብ አድርጌው ዘብጥያ መውረዴ ነበር፡፡" አሉና ከዘራቸውን ወደ ግራ እጃቸው አጋብቸው ከዘራ በያዙበት እጃቸው አማተቡ፡፡

"ሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂ..." የሰይጣን የሚያበሳጭ እና የሚሰቀጥጥ ሳቅ ጆሮአቸው ሥር ተቅለጨለጨ.......

" ድሮም ከእግዜራችሁ በፊት ዱላችሁ ነው ትዝ የሚላችሁ....ነውጠኛ ሁሉ.... #የምትዠልጠው_ስታጣ_ታማትባለህ? አይሸፋፋው አስር አለቃ....ሂሂሂሂሂ ሁሁሁሁ ቂቂቂቂቂ..." አለ ሰይጣን ግቢ ግቢያቸው ውስጥ ቀድሞ ገብቶ #ካሉበት_አርባ_ክንድ_ርቆ ከቆመ በኀላ፡፡

አስር አለቃ ግራ ተጋቡ፡፡ ንዴታቸውን ዋጥ አድርገው እየተጣደፉ በቁጣ ወደ ቤታቸው በር ገሰገሱ፡፡

አስር አለቃ አቋማቸው እንደሰምበሌጥ ቀጥ ያለ ስፖርተኛ አቋም ነው፡፡ ሰው ሁሉ "አቤት ቁመና!!" ይላቸው፡፡ ሰይጣን ግን ወደ ቤታቸው ሲጣደፉ የሚያበሽቅ ንግግር

"ሸፋፋ ..ሸፋፋ ትላለህ! ሲራመዱ አይተህ...ደግሞ ወታደር ነኘ ይላል እንዴ? ይሄን ደጋን የመሰለ እግር ይዞ ሂሂሂሂሂሂ...እንኳን አገር ልትጠብቅ በዚህ ሸፋፋ እግርህ ሚስትህንም አትጠብቅ ተመልከት የእግርህን ክፍተት በልጅነትህ ፀሐይ አላሞቀችልህም ያቺ ጨብራራ እናትህ!!! ኪኪኪኪኪ..."

አስር አለቃ ከሳቸው አልፎ እናታቸው ማዋረዱ ቢያንገበግባቸውም የተናጋሪው ማንነት ስለገባቸው እንደገና አማተቡና

"የማርያምን ብቅል ፈጭቻለሁ ቱ! ቱ! ቱ! አንተ ፖለቲከኛ ሰይጣን!" ብለው ወደ መሬት አንዴ ወደሰማይ ትፍ! ትፍ! ቀጠል አድርገውም " አንተ ክፋ አውቄኻለው እንዲ አቅልሎ የሚጠራኘ እንዳንተ ያለው ቀላል እንጂ ሌላ እንደማይሆን መች አጣሁት?" ካሉ በኀላ ቆይ ላግኘህ ሚመስል ዛቻ ከዘራቸውን ነቀነቁና ነጠቅ ነጠቅ ብለው በመራመድ ወደቤታቸው ገቡ፡፡

ሰይጣንም አጀንዳውን ከፍቶ "አስር አለቃ ደባልቄ" በሚለው ፊት ለፊት በቀይ እስኪሪቢቶ 'ራይት' አደረገ፡፡ መንገዱንም ቀጠለ! እየሳቀ እና እያፏጨ...! ይሄ ሸፋፋ ለዛሬ ይበቃዋል ሲበሳጭ ይደር፡፡ ነገ ደሞ በተመቸኘ ሰዓት ብቅ ብዬ ነጅሼው እሔዳለሁ፡፡ አለና እየሳቀ መንገዱን ቀጠለ፡፡

አስር አለቃ ቤት ግራና ቀኘ ባሉት ጫት ቤቶች ተኮልኩለው ጫት የሚቅሙትን ወጣቶች በኩራት እየተመለከተ
"ርስቴ እየተስፋፋ ነው!" ብሎ እየኮራ ቁልቁቅል ወደ ወንዙ!

በእርግጥም ሰይጣን እንዳሰበው አስር አለቃ ሌሊቱን እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደረው፡፡ እንደዛ ያበሻቀጣቸው ሰይጣን ነው ለማለት ጥርጣሬ ገባቸው "እኔ የትኛው ቅድስና ኖሮኘ ሊፈትነኘ ይመጣል?"
አሉ ለራሳቸው፡፡ እንደውም አንዱ ጎረቤታቸው ተደብቆ እንደሰደባቸው ጠረጠሩ፡፡ "ማን ሊሆን ይችላል? ሌሊቱን ሙሉ ተብሰለሰሉ ፡፡

"ይች ጎረቤቴ የትነበርሽ ትሆን እንዴ? የለም ድምፁ የወንድ ነው፡፡ ግንበኛው አሰፋ መሆን አለበት እሱ ለካ ለሥራ ክፍለሃገር ከሄደ ሁለት ወሩ... እና ማናባቱ ነው...፡፡" ወደ ንጋቱ ላይ አንድ ሃሳብ ብልጭ አለላቸው፡፡ አረጋ!! ድንበር እየገፋ የበጠበጣቸው ጎረቤታቸው!! አረጋ! እሱስ ሚስታቸውን በምኞት ዓይኑ የሚቃኘ ጥጋበኛ ነው ድምፁ መጣላቸው ራሱ ነው!

"አገኘሁት ብለው ዘለው ከአልጋቸው ተነሱ፡፡ ሚስታቸው እማማ የውብዳር በአስር አለቃ አነሳስ ደንግጠው

"በስማም ምን ሆኑ? ሲሉ ጠየቁ

"ዝም በይ ሸፋፋ!" ሲሉ ሚስታቸውን ሰደቧቸው ከሰይጣን በተዋሷት ያደረች ስድብ፡፡ አስር አለቃ ከዛ በፊት ሚስታቸው ሰድበው አያውቁም ነበር፡፡ ልብሳቸውን ለባብሰው እየተጣደፉ ሲወጡ ሚስታቸው አልጋው ላይ ሆነው አሰቡ

"ይሔን ሁሉ ዘመን ዓይቶት የማያውቀውን የእግሬን መንሻፈፍ ዛሬ እንዴት ታየው? ምናልባት ወጣት ሴት ዓይቶ ይሆን? ማን ያውቃል ...? ባላቸውን ካገቧቸው ጀምሮ ዛሬ ገና ተጠራጠሩ፡፡

ልጃቸው ስንቄ እንደ ሁልጊዜው ከመኘታዋ ተነስታ እያንጎራገረች ነበር፡፡ ለሙዚቃ ከፍተኛ ፍቅር ያላት ስንቄ በተለይ የአስቴርን አወቀን ዘፈኖች ስትዘፍን ታስደምማለች፡፡ ዛሬ ግን እናቷ ድንገት አንባረቁባት

"ወዲያ ዝም በይ! ምን በጧቱ ታንቋርሪብኛለሽ!"

ስንቄ በእናቷ ንግግር ክፉኛ ተበሳጨች፡፡ እስከዛሬ ሲያንቋርር ነበር "የኔ ልጅ ድምጿ ብቻ የወፍ ዘር የሚያረግፍ..." እያሉ ዛሬ ታዲያ ምን ነካቸው? ስታምሰለስል ድንገት ጓደኛዋ ሊበን ደወለ፡፡

ዛሬ "ሰርፕራይዝ" ሊያደርጋት ጓደኞቹን አዘጋጅቶ እየጠበቃት ነው፡፡ እንድታገባው ሊጠይቃት ወስኗል ጓደኞቹ ጋር ቤቱ ቅልብጭ ያለ ፕሮግራም አዘጋችቶ ድንገት ሊነግራት የቃል ኪዳን ቀለበቱን አዘጋጅቶ በጉጉት እየጠበቃት ነው፡፡

"ሄሎ!" አለች እንደከፋት

"ሄሎ...! ምነው ድምፅሽ?" አላት እንባ ተናንቋት ስለተናገረች ድምጿ በእርግጥም ድክም ብሎ ነበር፡፡

"ድምፄ ምን ሆነ? ስትል ጠየቀችው፡፡

"ተንቋረረ ልበል?" አላት ፈገግ ብሎ፡፡ ስልኩን ጆሮው ላይ ጠረቀመችበት፡፡

ዘፋኘነትም ከዚህ በኀላ ዋጋ እንደሌለው ገባት፡፡ አርፋ የፀሀፊነት ሥራዋን ለመስራት ወሰነች፡፡ "አንቋራሪ ድምፅ " ያውም በእናቷና በምቶደው ፍቅረኛዋ የተመሰከረበት...፡፡ እስከዛሬ ሰው ፊት 'ስታንቋርር' ሁሌም ሲታዘባት በሹክሹክታ ሲቀልድባት እነንደኖረች ተሰማትና አፈረች!!

###
ኡኡኡኡኡኡኡኡኡ....ከወደውጪ ድምፅ ተሰማ...........

ክፍል ሁለት ይቀጥላል

#ካሉበት_አርባ_ክንድ_ርቆ ከቆመ በኀላ፡፡ እኔ እንደጨመርኩበት ልብ ይሏል

@jahABP ነኘ አስተያየታችሁን አድርሱኘ
15.2K views15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ