Get Mystery Box with random crypto!

Islamic Education

የቴሌግራም ቻናል አርማ romedanm — Islamic Education I
የቴሌግራም ቻናል አርማ romedanm — Islamic Education
የሰርጥ አድራሻ: @romedanm
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 316
የሰርጥ መግለጫ

አላህ(ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡-
ﻓَﺎﺳْﺘَﺒِﻘُﻮﺍ ﺍﻟْﺨَﻴْﺮَﺍﺕ
“ #ወደ_መልካም_ሥራዎችም_ተሽቀዳደሙ።” (አል-በቀራ2፤148)
ሁሉም የአላህ #ምህረትና_እዝነት ለማግኘት ይሽቀዳደማል።
#ሙስሊም ሆይ! ስለሆነም ወደዚህ መለኮታዊ #ስጦታና_የኢማን_ምጥቀት ፈጠን ብለህ ጉዞ ጀምር ተሽቀዳደም። #በአላህ ፈቃድ ታሸንፋለህ።
ለማንኛዉም አስተያየት
📩📮👇
@Ramadanetbot

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-02-15 18:31:01 Turkiye Burslari Scholarship ይባላል፤ በቱርክ መንግስት ስፖንሰርነት በየአመቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ከመላው አለም ተቀብሎ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተምራል።

ይህ ስኮላርሽፕ በ ባችለርስ (የመጀሪያ ዲግሪ)፣ ማስተርስ እና ፒኤችዲ ደረጃዎች የተዘጋጀ ሲሆን የዘንድሮ 12ተኛ ክፍል ተማሪዎች በ 11 Transcript ባችለርስ አፕላይ ማድረግ ትችላላችሁ።

የስኮላርሺፑ ጥቅሞች
1. ነፃ የ ፕሌን ትኬት ወደ ቱርክ
2. ነፃ ትምህርት
3. የጤና ኢንሹራንስ
4. Accommodation (መኖሪያ)
5. stipend money (የወጪ ገንዘብ)። በየወሩ ለ ባችለር 1000 T.Lira ማስተርስ 1400 T.Lira ፒኤችዲ 1800 T.Lira

አፕላይ ለማድረግ የሚያስፈልጉ ዶክመንቶች

የቀበሌ መታወቂያ/ ፓስፖርት /የልደት ካርድ

የአራት አመት ከ 9-12 ትራንስክሪፕት። ዘንድሮ 12 ተማሪ የሆናችሁ ከ 9-11 ማስገባት ትችላላችሁ።
ትራንስክሪፕታችሁ የአራቱን/ሶስቱን አመት ጠቅላላ ውጤት Average 70% እና ከዛ በላይ የሚፈለግ ሲሆን Medicine, Dentistry እና Pharmacy መማር ለምትፈልጉ 90% እና ከዛ በላይ መሆን አለበት።

የብሄራዊ ፈተና ሰርቲፊኬት የ 10 ካላቹ አስገቡ የ 12 ካለ ወዲያው ማስገባት ከሌለ ግን ኢንተርቪው ላይ ማስገባት ይቻላል።

Letter of Recomendation ከ አስተማሪያቹ ወይም ዳይሬክተር ስለእናንት የሚፃፍ ደብዳቤ ነው። ማሳሰቢያ:- አስተማሪዎች ብዙ ጊዜ ከልምድ ማነስም ሆነ ጊዜ ካለመስጠት አሪፍ የሚባል Recommendation ስለማይፅፉላችሁ ራሳችሁ ወይም ሌላ ሰው በደንብ ፅፎላችሁ ለአስተማሪዎቻችሁ ብትወስዱላቸው የተሻለ ነው። ጥሩ Recommendation ለአፕልኬሽናቹ በጣም ጠቃሚ ነው።
ከዚህ ባለፈ

Letter of intent ይኖረዋል። ይህ ደግሞ ለምን ቱርክ መማር እንደፈለጋችሁ፣ ፊልዳቹን እንዴት በምን ምክንያት እንደመረጣችሁ እና ተምራቹ ስትጨርሱ አላማቹ ምን እንደሆነ የሚጠይቁ ጥያቄዎች መልስ ምትሰጠቡት ነው።
ይህ በጣም ወሳኝ የሆነ ፓርት ሲሆን ትራንስክሪፕታቹ እንኳን ትንሽ ዝቅ ቢልባቹ እነዚህን ጥያቄዎች ጥሩ በሆነ መንገድ ከመለሳቹ ያን የመሸፈን ዕድል አላችሁ። በ አጠቃላይ ዝቅ ያለ ትራንስክሪፕት ሆነም አልሆነ በጣም በጣም አስፈላጊ ክፍል ስለሆነ ጊዜ ሰታችሁ፣ ስለአፃፃፉ ሰርች አድርጋቹ እና ተጠንቅቃችሁ ፃፉ።

ጉርድ ፎቶ

ከዚህ ውጭ Extracurricular certificate ካለን ሁሉንም ብናስገባ በጣም ጠቃሚ ነው። ምሳሌ:- የት/ቤት ክለብ ተሳትፎ፣ በጎ አድራጎት ማህበር፣ ማንኛውም ከማህበር ከግል ወይም ከመንግስት ተቋም ያገኘናቸውን ሠርቲፊኬቶች።

በተጨማሪም አለምአቀፍ የቋንቋ ፈተናዎችን(TOEFL,GRE,SAT...) ሠርቲፊኬት ካላቹ በጣም ጠቃሚ ስለሆኑ በፍፁም ማስገባት እንዳትረሱ።

አፕሊኬሽኑ ኦንላይን እና ነፃ ሲሆን በየአመቱ ከ January 10 - February 20 አፕላይ ማድረግ ይቻላል። ስለዚህ አንድ ሳምንት አካባቢ የሚሆን ጊዜ ስለቀረው ጊዜው ሳያልቅ በ ሊንኩ ገብታችሁ አፕላይ አድርጉ።



መዓሰላማ

ተቅዋ ጀመዓ


||
t.me/MuradTadesse
466 views , 15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-09 09:58:40 ➩ማስታወሻ
=========
«እናታችን አዒሻ የረመዳን ወር ሲገባ ከፈጅር ሶላት ቡሀላ ፀሀይ እስክትወጣ ድረስ ቁርአን ትቀራ ነበር ከዚያም ልክ ፀሀይዋ ስትወጣ ትተኛለች»።

ምንጭ:- ((لطائف المعارف171/1))

https://t.me/ramadanlov
367 views , 06:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-09 09:58:40 ➩ማስታወሻ
========
ረሱል (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሲያፈጥሩ ይህንን ዱዓ ይሉ ነበር «ዘሃበ ዘመዑ ወብተለቲል ዑሩቁ ወሰበተል አጅሩ ኢንሻ አሏህ»
ምንጭ:- ሶሒሁል ጃሚዕ (4678)
https://t.me/ramadanlov
324 views , 06:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-09 09:58:40 ➩ማስታወሻ
==============
«እጁ አመድ አፋሸ ይሁን ረመዳንን አግኝቶ ወንጀሉ ሳይማርለት ያለፈው ሰው»።
ረሱል (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም
ምንጭ:- ቲርሚዚ (3445)
https://t.me/ramadanlov
305 views , 06:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-29 20:32:40 ወላሂ ልሰሙት የሚገባ ሙሀደራ ነው

https://t.me/ramadanlov
https://t.me/ramadanlov
315 views , 17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-29 20:31:15 እዉነተኛ ታሪክ
#የቅዠት_ህልም
ክፍል


     አንድ ሸህ ወደ ሌላ ሀገር እየሄደ መንገድ ላይ ይመሽበታል፡፡ ከዛም የሆነ ቤት ሲደርስ እዚህ ቤት አሳድሩኝ ይላቸዋል፡፡ የቤቱ ባለቤት እሺ ብለዉ ወደ ቤት እንዲገባ ፈቀዱለት..... እራታቸዉን እየበሉ ደአዋ ያረጋሉ እንግዳዉ ሸህ አትስረቁ አትዋሹ  የሚያምር ሀዲሶች ምክር ሲመክሯቸዉ አመሹ ጠዋት ቁርስ አብልተዋቸዉ ተስናብተዉ ከቤት ሄዱ ......
    ከዛ ሌላ ሰዉ ቁርስ ሊበላ ሲፈለግ ሸህየዉ ቁርስ የበሉበት ሰሀን ይጠፋል፡፡ ቢፈለግ ቢፈለግ ጠፋ
እስኪ ሸሆቹ ወስደዉት እንደሆነ ተከትለን እንያቸዉ ብለዉ ተከተሏቸዉ
እንደደረሱም ሸህየዉ ሰሀኑን ይዘዉታል፡፡
..... ማታ ደአዋዉን ካዳመጠዉ የአሳደሯቸዉ ልጅ እንዴ
.....ሸሁ ማታ አትስረቁ አትዋሹ እያልኩ መክረሁን እንዴት አንቱ ትሰርቃለሁ??? አላቸዉ፡፡
.....ሸህየዉም እኔ የነገርኳችሁ ሀዲስ እና ቁርአኑን ነዉ እንጂ የራሴን ባህሪ እና ፀባይ አልነገርኳችሁም፡፡ ........አሏቸዉ ይባላል፡፡

ይህ  የቅዠት ህልም በሚል የተዘጋጀ ታሪክ በእዉነተኛ ታሪክ ሲሆን ከላይ እንደነገርኳችሁ ከላይ ከነገርኳችሁ ቀልድ ጋር ይያያዛል
  
       ስሜ ኢክራም ሁሴን ሲሆን ተወልጄ ያደኩት በአባ ጅፋር ሀገር .... ጅማ ከተማ ነዉ፡፡ እናት እና አባቴ በሂወት ያሉ ሲሆን ደሀም ሀብታም ባንባል መካከለኛ ኑሮ ነዋሪዎች ነን፡፡
ሶስት እህት አንድ ወንድም አለኝ፡፡ እኔ ሶስተኛ ልጅ ነኝ ከእኔ በላይ አንድ እህት አንድ ወንድም ሲሆን እህቴ አግብታለች ወንድሜ ግን ገና ነዉ ፡፡

   ከእኔ በታች ያሉትን የመንከባከብ ሀላፊነት አለብኝ፡፡ አጫዉታቸዋለሁ እንከባከባቸዋለሁ.... አባቴ ቀልድ አያቅም በጣም ቁጥጥሩ ከባድ ነበር፡፡ ከልጅነቴ ጀምሮ በጣም ተቆጣጥሮ የአሳደገኝ ሲሆን ትምህርቴን ስማር .......ትምህርት ቤት ድረስ ይቆጣጠረኝ ነበር፡፡ ትምህርቴን እየተማሪኩ ከትምህርት ስመለስ ቁርአን እንድቀራ ከሰፈራችን ካሉ ቁርአን ከሚያቀሩ ሸህ ጋር ከትምህርት ሰአት ዉጭ እቀራለሁ ፡፡ ትምህርቴን 9 እና 10 የተማርኩት ጅማ በሚገኘዉ ጂረን የሚባል ትምህርት ቤት ሲሆን 11 እና 12 ክፍል ደግሞ ጂማ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነበር፡፡
  ግን እስከ 12 ክፍል ስማር አይነ አፋር ከማንም ወንድ ጋር አልቀርብም ነበር  ......ብቻ ለትምህርቴ ትኩረት ሰጥቼ የምማር... ከክፉ የሴት ጓደኞች የራኩኝ ነበርኩ፡፡ ከትምህርት ወደ ቤት ከቤት ወደ ትምህርት ሲሆን በትርፍ ሰአቴ ቁርአን ቀርቼ እናቴን በስራ ማገዝ ታናሾቼን መንከባከብ የዘወትር ስራየ ነበር፡፡

ቁርአን አከተምኩ ቤተሰቦቼ በጣም ተደሰቱ፡፡ ግን ኪታብ ለመቅራት ጊዜ አላገኘሁም......
 አስራ ሁለተኛ ክፍል ስለሆንኩ ለማትሪክ ፈተና  ጥሩ ዉጤት ለማምጣት ብየ  ትኩረት ሰጥቼ  እያጠናሁ  ነዉ፡፡
....,የመተፈተኛ ቀናችን ደረሰ ተፈተንኩ ፡፡ የዩኒቨርስቲ  ዉጤት እስከ ሚመጣ ድረስ ዱአ ማድረግ እና እናቴን በስራ ማገዝ እና ቁርአኑ እንዳይጠፋኝ  ምላሽ መቅራት ላይ አተኮርኩ፡፡

ቁርአን የሚያቀሩኝ ኡስታዜ ስለዲን ስለ ሴት ልጅ ስነ ስርዓት ይመክሩኝ ነበር፡፡  እናቴ ለእኔ እናቴም ጓደኛየም ነበረች ሁሌ የሆነ ነገር ሲገጥመኝ መጀመሪያ ለእናቴ ነበር የማማክራት፡፡

    እናቴም የተለያዩ ሴቶች የገቡበትን ችግር ከወንድ ጋር ከትዳር በፊት ምንም መቀራረብ እንደሌለብኝ ሁሌ ትመክረኛለች ፡፡ ለወደፊት ትምህርትሽን ተምረሽ ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሰሽ አስደስችን ትለኝ ነበር ፡፡
.....እኔም  እሺ እናቴ አንቺንማ አስደስትሻለሁ ቃል ገብቻለሁ እላታለሁ ፡፡ በቀኝ ጆሮየ አዳምጨ በግራ ጆሮዋ የማፈስ ልጅ  አይደለሁም፡፡

   ግን የዩኒቨርስቲ ዉጤት ከመጣልኝ ኢንሻ አላህ ዩኒቨርስቲ ኪታብ እቀራለሁ ብየ ለራሴ ቃል ገባሁ፡፡
   ህልም አለኝ  ተምሬ  ቤተሰቦቼን ማስደሰት ነዉ የሚታየኝ የወደፊቱ ነዉ፡፡

 የዩኒቨርስቲ ማለፊያ  ዉጤት መጣ ፡፡ ዉጤቴም ያላሰብኩት  ነበር፡፡  ዉጤትም ዩኒቨርስቲ ለመግባት.......

#part
#ይ
       #ቀ
             #ጥ
                    #ላ
                         #ል
ለጓጀኛው ለወዳጅዎ ሼር ለማድረግ ይሄን ይጫኑ

JOIN

´´´´´´´ :¨·.·¨: ❀ share
           `·. https://t.me/ramadanlov
305 views , 17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-28 09:09:21


እኛ የዚያ ከረሃብ የተነሳ ሆዳቸው ላይ ድንጋይ
ያሰሩት ነብይ ህዝቦች ነን...
የዛ የመልካም ስነምግባር ቁንጮ መልክተኛ ህዝቦች
የዚያ ህዝቦቹ ናፍቀውት ያነባው ረሱል ህዝቦች
ያ በመለየቱ የቴምር ዛፍ የተንሰቀሰቀለት የታላቅ ሰው ህዝቦች ነን...

ከቀናት ሁሉ አውራና ምርጥ በሆነው ጁመአ ቀን በታላቁ ሰው ላይ ሰለዋት ማለት በቀጥታ ነቢ ጆሮ ነው ሚደርሰው።

የእከሌ ልጅ ባንቱ ላይ ሰለዋት አውርድዋል
ተብሎ ስምህ የዓለማት ነቢይﷺ ፊት
መነሳቱ ምን ያማረ ነው

صلى عليك الله يا نورًا سرى في المشرقين ففرت الظلمات ، صلوا عليه ﷺ.

መልካም ጁመዐ
265 views , 06:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-05 09:24:45
ኢና ሊላሂ ወዒና ኢለይሂ ራጂዑን
ሼይኽ መሐመድ ቢን ሷሊህ አል ሉሄይዳን ወደ አኼራ ሄዱ

የሳኡዲ አረቢያ የታላላቅ ኡለሞች ምክር ቤት አባል የነበሩት ታላቁ የሃገርቱ
አሊም ሼይኽ መሐመድ ቢን ሷሊህ አል ሉሄይዳን ወደ አኼራ ሄደዋል:: ሊላሂ
ወዒና ኢለይሂ ራጂዑን
ትምህርቶቻቸው ለሃገራቸው ብቻ ሳይሆን ለመላው አለም ተደራሽ ሆኖ ብዙዎች
ከሳቸው እውቀት ተጠቃሚ ይሆኑ ነበር::
በመስጂደል ሀረም ትምህርት ሲሰጡም ከፍተኛ ህዝብ ዙሪያቸው ተቀምጦ
የሚሰጡትን ትምህርት ይከታተል ነበር::
ሼይኽ መሐመድ ቢን ሷሊህ አል ሉሄይዳን በሳዑዲ አረቢያ በቡኻይሪያ ከተማ
ቃሲም በተባለ አካባቢ በ 1350 አመተ ሒጅሪያ ነበር የተወለዱት::

እኚህ ታላቅ የእድሜ ባለፀጋ እና የእውቀት ቀንዲል በ93 አመታቸው የዚህን
ምድር ቆይታቸውን አጠናቀው ወደ ጌታቸው አልፈዋል!
ምድራችን ትልቅ አሊም በሞት ተነጥቃለች::
አላህ ይዘንላቸው! መልካም ስራቸውን ሁሉ ይቀበላቸው! ማረፊያቸውንም በጀነት
ያድርግላቸው
https://t.me/ramadanlov
https://t.me/ramadanlov
337 views , 06:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-04 11:36:15
አላህ ሆይ!

ደካማ በሆነው ትዕግስታችን ችላ አትበለን። እዝነትህ ሁሉንም ያካበበ ጌታ ነህና ይቅር በለን።
https://t.me/ramadanlov
267 views , 08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-02 17:43:33 "ሀፍሲ"
ክፍል አስራ ሁለት
ፀሐፊ፦ ኑዕማን ኢድሪስ

እሁድ ጧት
3:00 ሰአት
ሻሸመኔ

... መስጅዱ አከባቢ ወላጆቻቸዉን በሞት ያጡ ህጻናቶች ተሰብስበዋል። ረጂና አስታማሚ ያጡ እድሜያቸዉ የገፉ አዛዉንቶችም ምርኩዛቸዉን ተደግፈዉ በመስጅዱ አጥር ስር ተደርድረዉ ተቀምጠዋል። የሻሸመኔ ወጣቶች ጀመዓ እነ ኡስማን ከመምጣታቸዉ በፊት በከተማዉ እየተዘዋወሩ በያዙት መረጃ መሰረት በሀገሪቱ ብዙ ረጂ ያጡ አረጋዉያን ቢኖሩም የተዘጋጀላቸዉን ስጦታ ለመቀበል የመጡት ግን የተወሰኑት ነበሩ። በህመምናና በተለያዩ ምክንያቶች ያልመጡት ብዙ ናቸዉ።
ሙባረክ ስም እየጠራ ሸኽ አጃኢቡና ኡስማን ለአረጋዉያኖቹ የተዘጋጀዉን እያከፋፈሉ ነበር።
ዴቭ፤ ሀያትና ሳራ ደግሞ በሀፍሲ እየተመሩ ወላጆቻቸዉን ላጡ ህጻናት አልባሳትና የምግብ ዉጤቶችን ይሰጣሉ።

... "ሰዉን መርዳት ለየት የሚያደርገዉ ነገር ከተቀባዩ በላይ ሰጪዉ ነዉ የሚደሰተዉ። ስትሰጡ ፤ ለጋሽ ስትሆኑ የሰጣችሁት ሰዉ በናንተ ምክንያት ፈገግ ብሎ ስታዩት ከየትኛዉም ሰዉ በላይ ደስተኛ የምትሆኑት እናንተ ናችሁ!...." ስራቸዉን አጠናቀዉ ከሻሸመኔ ሙስሊም ወጣቶች ጀመዓ ጋር የምሳ ግበዣ ላይ ሸኽ አጃኢቡ ንግግር እያደረጉ ነዉ። "... ልጆቼ በእርጅና ጊዜያችሁም ይሁን ለአኼራዉ ቤታችሁ ሚጠቅማችሁ በወጣትነት የምትሰሩት ኸይር ስራ ነዉ። ብዙ የተቸገሩ አረጋዉያኖች አሉ፤ የእናንተ የእድሜ እኩዮች አልባሌ ቦታ ነዉ የሚዉሉት። አረጋዉያኖችን ተንከባከቡ፤ ወጣቶችንም ከመጥፎ ነገር ታደጓቸዉ።...." አሉ።
.
.
.
... ከምሳዉ በኃላ ጉዞዉ ተጀምሯል። ሳሪና ሙባረክ ከዴቭ ጋር አብረዉ ሲሄዱ፤ ኡስማን ደግሞ ከሀያት ጋር አብረዉ እየሄዱ ነዉ።

ሀፍሲ ሸኽ አጃኢቡ ለምን እንደፈለጓት ብዙም አላሳሰባትም። ከትናንት ምሽት ጀምሮ ዉስጧ በዴቭ ፍቅር ተንጧል። ለወራቶች ያክል የኔ ይሆናል ብላ እርግጠኛ የነበረችበት ነገር በትናንትዉ ምሽት ንፍስ ላይ እንደተሰጣ የስንዴ ገለባ ላይያዝ ላይሰበሰብ ተበታትኗል። አማላይ የሆነዉ ዉበቷ፤ ብዙ ወንዶች የሚቋምጡለት ቁንጅናዋ ዴቭን ማንበርከክ አልቻለም። በቤተሰቦቿና በጓደኞቿ በኩል የመጡት ወንዶች ሁሉ ተጨምቀዉ አንድ ዴቭን ሆነዉ በጠየቀኝ። "በጣም የምወዳት እሷም ከኔ በላይ የምትወደኝ ሴት አለች!"። ተስፋዋ እንደተሟጠጠ ተሰማት። ልጅ እንዳለዉ ስታስብ ደግሞ ይበልጥ ትሸበራለች። ሸህ አጃኢቡ ዘወር ብለዉ ከተመለከቷት በኃላ ንግግር ለመጀመር ያክል "ምን እያሰብሽ ነዉ ልጄ?" አሏት። እንደመደንገጥ ብላ አይኗን እያርገበገበች "ምን አላሰብኩም ኡስታዝ... ይልቅ ትናንት እፈልግሻለሁ ያሉኝ ለምን ነበር?" ብላ እሳቸዉን መልሳ ጠየቀቻቸዉ። ለማወቅ አልጓጓችም። ማዉራታቸዉ ዴቭን ለደቂቃዎች ቢያስረሳኝ ብላ አስባ ነዉ።

... "ሃዩ" አላት።
"ወይዬ ኡስሚ" ብላ መለሰችለት። ሀያት በተፈጥሮዋ ዝምተኛ ናት። ዝምታዋ ግን ብዙ ነገር አሳጥቷታል። አሁን ላይ ግን በዝምታዋ ምክንያት ኡስማንን ማጣት አልፈለገችም። ለማንም ሳትነግር፤ ለጓደኞቿ ሳታማር በዉስጧ ፍቅሯን አፍና ይዛ ኡስማንን ከአንድ አመት በላይ ወደዋለች። ስሜቷን አዉጥቷ ባትነግረዉም በአይኗቿና በሰዉነት እንቅስቃሴ ገልጻለት ነበር። ነገር ግን ኡስማን ልቡ ከሀፍሲ ጋር ስለሄደ ሀያትን ሊያስተዉላት አልቻለም።
"ትናንት የሆነ ነገር ልትነግሪኝ ፈልገሽ ነበር..." ብሏት እጁን ከመኪያዉ መሪ ላይ ሳያነሳ መልከት አላት። እጆቿን እርስ በርስ እያፋተገቻቸዉ ነበር። አሁንም እንደፈራች ያስታዉቅባል።
"ኡስሚ...." አለች። ድምጸን ዝቅ አድርጋ ብትጠራዉም መልሷን እየተጠባበቀ ስለነበር ሰምቷታል።
"ሃዩቲ ንገሪኝ አትፍሪ!" ብሎ ድፍረት እንዲኖራት አደረገ።
"ኡስሚ .. ከነገርኩህ በኃላ ብትርቀኝስ ብዬ ፈራሁ!" ስትለዉ ኡስማን ልቡ እንደመደንገጥ አለ። መጀመሪያም ከሷ እስኪመጣ እንጅ ከትናንት ምሽት ጀምሮ ጠርጥሯል። ምን እንደሚመልስላት ተጨነቀ። ኡስማን ለሰዎች መጎዳት ምክንያት መሆን አይፈልጎም። ሰዎችን ከመጉትና ከማሳዘን ይልቅ ለራሱ ቢጎዳ ይመርጣል። ቤተሰቦቹም ብዙ ጊዜ ሚወቅሱት በዚ ባህሪዉ ነዉ።
"ሃዩ አንቺንኮ ዛሬ አይደለም ማዉቅሽ እንዴት እርቅሻለሁ?" አላት።
"ኡስሚ እንደ ድፍረት አትቁጠርብኝ"
"ችግር የለም ንገሪኝ!"
"ኡስሚ ዉስጤ ያለዉን ስሜት ቃላት አይገልጹኝም። እነግረሀለሁ እያልኩኝ ስለምፈራህ ብቻ ሳልነግርህ አመት አለፈኝ።..." ኡስማን ይበልጥ ተገረመ። "እኔ ሀፍሲን በስድስት ወር ተስፋ እየቆረጥኩ ነዉ አንቺ አመት ሙሉ ሳትነግሪኝ ብቻሽን አፈቀርሽኝ!" በጣም ደነቀዉ።
"... አፈቅራሀለሁ ኡስሚ" አለችዉ። ስሙን እየደጋገመች ስትጠራዉ እሱም በተደጋጋሚ እየዞረ ሲመለከታት ነበር። ለተወሰኑ ደቂቃዎች ምንም ነገር ሳይመልስላት ዝምታን መረጠ። ሃዩ ደግሞ ስሜቷን አዉጥታ ከነገረችዉ በኃላ ወደሱ ዞራ መልሱን መጠባበቅ ያዘች።
.
.
.
..."ሀፍሲ የኔ ልጅ አንቺ በጣም ቆንጅዬ ነሽ። አላህ (ሱ.ወ) አስዉቦ ፈጥሮሻል። እድሜሽም ቢሆን ሃያን እያለፍሽ ነዉ።...." እያሉ ለመግቢያ ያክል በምክር ቢጤ ጎንተል እያደረጉት ነዉ። ሀፍሲም መኪናዋን እያሽከረከረች ጆሮዋን ጣል አድርጋ እያዳመጠቻቸዉ ነዉ። "... ዉበት እንደሆነ ጠፊ፤ እድሜም ገፊ ነዉ። አሁን የሚጠይቁሽ፤ የሚያባብሉሽ ወንዶች ሁሉ እድሚሽ ሲገፍ፤ ቁንጅናሽ ሲጠፋ አጠገብሽ አይገኙም። እና ልጄ..." ብለዉ ወደ ዋናዉ ጉዳያቸዉ ሊገቡ ነዉ። "...እና ልጄ ኡስማን ወዳንቺ ዘንድ ልኮኝ ነበር።" ሲሏት ሀፍሲ በድንጋጤ የመኪናዋን ፍጥነት መቆጣጠሪያ ፍሬኑን ተረገጠችዉ። መኪናዋ ቀጥ ብላ ነበር የቆመችዉ። ኡስማን እዚ ደረጃ ይደርሳል፤ ሸህ አጃኢቡን ይልክብኛል ብላ አስባ አታዉቅም። "እንደ ወንድሜ ነዉ የማይህ" ካለችዉ በኃላ ተስፋ ቆርጧል። ትቶኛል ብላ ታስብ ነበር።
"ምን ሁነሽ መኪናዉን አቆምሽ?" ብለዉ ጠየቋት። ተረጋግታ ለማሽከርከር እየሞከረች "አይ ምንም!" አለቻቸዉ።

"ነቢ ሰላም አላ
ረሱል ሰላም አላ
ሙሀመድ ነብዬ ሶለላህ አላ
ሙሀመድ ነብዬ ሶለላህ አላ...." ዴቭ የመኪናዉን ቴፕ ድምጽ ለቆታል። በሸህ ሙሀመድ አወል መንዙማ ሙባረክና ሳሪ ከመኪናዉ የኃላ ወንበር ሁነዉ በህብረት እያጨበጨቡ ይቀበላሉ። የሰሩት ስራ አስደስቷቸዋል። ምክንያቱም ከአዲስ አበባ ዉጭ ወደ ክፍለ ሀገር ተጉዘዉ አረጋዉያንንና ወላጆቻቸዉን ያጡ ህጻናት ሲረዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ነዉ። ዴቭ የመኪናዉን መሪ በመሀል እየለቀቀ እንደነሱ ጋር አብሮ ያጨበጭባል።

"ሀዩቲ ይሄን ያክል ጊዜ ሳትነግሪኝ መጎዳት አልነበረብሽም..." አላት። አንድ አመት ሙሉ ሳትነግረዉ ከምትቆይ መጀመሪያ አከባቢ ሀፍሲ ልቡ ዉስጥ ሳትገባ፤ ሳያፈቅር ብትነግረዉ የተሻለ እንደነበር እያሰበ አሁን ምን ብሏት እንደሚለያዩ ማሰላሰል ጀመረ።
"ልነግርህ አስቤ ነበር ግን ፈራሁህ" አለችዉ። ኡስማን ማግባት እንዳለበት ያምናል። ነገር ግን ሸኽ አጃኢቡን ወደ ሀፍሲ ልኳቸዋል። የሀፍሲን መልስ ማወቅ ስላልቻለ ሀያትን ምን ብሎ ይመልስላት፤ ጨነቀዉ። "በድጋሜ ሀፍሲ አልፈልግም ካለች ሀያትን አገባታለሁ!። ፍቃደኛ ከሆነች ግን ሀፍሲን አገባታለሁ።" ብሎ ለራሱ ወሰነ።

https://t.me/ramadanlov
ክፍል አስራ ሶስት ይቀጥላል.........
282 views , 14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ