የጤና ሚኒስቴር ከተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቁ የጤና ባለሙያዎች ከግንቦት 01 እስከ 04/2014 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና እንደሚሰጥ አሳውቋል። ሚኒስቴሩ ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የገለጸ ሲሆን የተፈታኝ ባለሙያዎች የጊዜ ሰሌዳን ይፋ አድርጓል። ፋርማሲ፣ አንስቴዥያ እና ሜዲካል ራዲዮሎጂ ባለሙያዎች ~ ግንቦት 01/2014 ዓ.ም ነርሲንግ ~ ግንቦት 02/2014 ዓ.ም ሕክምና፣ ጤና መኮንን እና ዴንታል ሜድስን ባለሙያዎች ~ ግንቦት 03/2014 ዓ.ም ሚድዋይፍሪ እና ሜዲካል ላቦራቶሪ ባለሙያዎች ~ ግንቦት 04/2014 ዓ.ም 2.3K views07:49