የሀገር መከላከያ ሰራዊት የአቅመ ደካሞችን ቤት ሰራ::
የሀገር መካላከያ ሰራዊት የሀገር ሉአላዊነትን ከማስከበር ባሻገር የአቅመ ደካሞችን ቤት እየሰሩ መሆኑን በራያ ቆቦ ወረዳ 010 ቦረን/ዞብል/ ቀበሌ ያሉ የ8ኛ ዕዝ 1ኛ ኮር 45ኛ ክፍለ ጦር 2ኛ ሬጅመንት አዛዥ ሌ/ኮሎኔል ማቲዎስ ማርቆስ ገልፀዋል::
ሌ/ኮሎኔል ማቲዎስ ማርቆስ አክለው ሰራዊቱ በኪሱ ከ150 ብር ጀምሮ በማዋጣት አናጺና ግንበኛ በመሆን ጭምር የ3 አቅመ ደካማ ሴቶችን ቤት ሰርተው ማስረከባቸውንና ይህ ተግባር ወደፊት ተጠናክሮ እንደሚቀ ተናግረዋል::
በመጨረሻም በተደረገው የበጎ ስራ ተግባር በመላው የራያ ህዝብ ስም ምስጋና ያቀረቡት ይወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ዱሱ ናቸው::
ራቆኮ