ፍራ ሰምቶ እንዳልሰማ ፣ ቢሆን ኖሮት ጆሮ አይቶ እንዳላየ ፣ ቢደበቅ ከ ጓሮ አፍ ኖሮት ፀጥ ቢል ፣ መናገር ባይሻ ፈርቶህ እንዳይመስልህ ፣ ይህን ጊዜ ሀበሻ ጀግና የጀግና ልጅ ፣ የሰው ዘር መነሻ ሲሸሽ ሊያሳጣህ ነው ፣መነሻ መድረሻ ። ዝም ሲል ሊያደምጥህ ፣ ስተትክን ሊረዳ እያየ እንዳላየ ፣ ሲደበቅ ከ ጓዳ አንድ እየሆነ ነው ፣ ዘመድና ባዳ ። ጆሮው እየሰማ ፣ ቢመስልህ ደንቆሮ ፀጥታው ካየለ ፣ አንድ ሁለት ቀን ቆጥሮ ሊያጠፋህ ነው ፣ ቀብሮ ። ስለዚህ ፍራ #ኪሩቤልዮናስ @yegtm_hywet @amharic_poet 14 viewsblessing_crown, 20:25