Get Mystery Box with random crypto!

ይህች ማን ናት??? ፡- 1.ፀጋን የተሞላች ከሴቶች ተለይታ የተባረከችና እግዚአብሔር ከእርሷ ጋር | ፅርሀ አርያም ቅድስት ስላሴ ቤተክርስትያን

ይህች ማን ናት??? ፡-
1.ፀጋን የተሞላች ከሴቶች ተለይታ የተባረከችና እግዚአብሔር
ከእርሷ ጋር የሆነ።
* መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ። ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ
ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ
ነሽ አላት።
የሉቃስ ወንጌል 1 : 28
2.በእግዚአብሔር ፊት ፀጋን ሞገስን ያገኘች።
* መልአኩም እንዲህ አላት። ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር
ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ።
የሉቃስ ወንጌል 1 : 30
3.የሰላምታዋ ድምፅ ፅንስ በደስታ ያዘለለ።
* ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ
በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ
ሞላባት፥
የሉቃስ ወንጌል 1 : 41
4.ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚሏት ።
* የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ
ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤
የሉቃስ ወንጌል 1 : 48
5.ፍፁም ትሁት። * የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና።
እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤
የሉቃስ ወንጌል 1 : 48
6.ቅዱሳን ያከበሯት።* የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ
እንዴት ይሆንልኛል?
የሉቃስ ወንጌል 1 : 43
7.ሰዎች በተጨነቁ ሰአት የምትማልድ።
* የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት። የወይን ጠጅ እኮ
የላቸውም አለችው።
የዮሐንስ ወንጌል 2 : 3
8.ምልክት ፀሐይን የተጎናፀፈች አህዛብን ሁሉ በብረት በትር
ይገዛ ዘንድ ያለውን ወንድ ልጅ የወለደች።* ታላቅ ምልክትም
በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት
በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት
አንዲት ሴት ነበረች።
የዮሐንስ ራእይ 12 : 1 * አሕዛብንም ሁሉ በብረት በትር
ይገዛቸው ዘንድ ያለውን ልጅ ወንድ ልጅ ወለደች፤ ልጅዋም ወደ
እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ።
የዮሐንስ ራእይ 12 : 5
9.ዘንዶው ያሳደዳት። * ዘንዶውም ወደ ምድር እንደ ተጣለ ባየ
ጊዜ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሳደዳት።
የዮሐንስ ራእይ 12 : 13
10.ዘንዶው በዘሯየተቆጣና ዘሯን ሊዋጋ የሄደ።
* ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት
የሚጠብቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን ከዘርዋ የቀሩትን
ሊዋጋ ሄደ፤
የዮሐንስ ራእይ 12 : 17
11.ውብ የሆነች።* ወዳጄ ሆይ፥ እንደ ቴርሳ ውብ ነሽ፥እንደ
ኢየሩሳሌምም ያማርሽ ነሽ፤ዓላማ ይዞ እንደ ተሰለፈ ሠራዊት
ታስፈሪያለሽ።
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 6 : 4
* ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።
መዝሙረ ዳዊት 45 : 11
12.የወርቅ ልብስ ተጎናፅፋ በእግዚአብሔር ቀኝ የምትቆም።
የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ
ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።
መዝሙረ ዳዊት 45 : 9
13.ንጉስ ዳዊት ልጄ ያላት።* ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም
አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤
መዝሙረ ዳዊት 45 : 10
14.ልጆቿን ገዥ አድርጋ የምትሾም።* በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች
ተወለዱልሽ፥ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ
ትሾሚያቸዋለሽ።
መዝሙረ ዳዊት 45 : 16
15.ተዘግቶ የሚኖረው የምስራቁ በር።* እግዚአብሔርም። ይህ
በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፥ ሰውም አይገባበትም፤
የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል።
ትንቢተ ሕዝቅኤል 44 : 2
16.የናቋት ሁሉ የሚሰግዱላት አማናዊት ፅዮን።*
የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ
ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ፤
የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን
ይሉሻል።
ትንቢተ ኢሳይያስ 60 : 14
17.በድንግልና ፈጣሪዋን የወለደች ምልክት
* ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል
ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ
ትጠራዋለች።
ትንቢተ ኢሳይያስ 7 : 14
18.እግዚአብሔር ያስቀረልን ዘር።* የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር
ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም
በመሰልነ ነበር።
ትንቢተ ኢሳይያስ 1 : 9
19.ቅዱስ ጳውሎስ ንፅህት ድንግል ያላት።
* በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት
ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ
አጭቻችኋለሁና፤
2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 11 : 2
20.ንገስታት የሚያመሰግንዋት።* ርግቤ መደምደሚያዬም
አንዲት ናት፤ለእናትዋ አንዲት ናት ለወለደቻትም የተመረጠች
ናት። ቈነጃጅትም አይተው አሞገሱአት፥ንግሥታትና ቍባቶችም
አመሰገኑአት።
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 6 : 9
21.ማን ናት???* ይህች እንደ ማለዳ ብርሃን የምትጐበኝ፥እንደ
ጨረቃ የተዋበች እንደ ፀሐይም የጠራች፥ዓላማ ይዞ እንደ
ተሰለፈ ሠራዊት የምታስፈራ ማን ናት?
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 6 : 10።
በአንቺ የሚኖሩ ሁሉ ደስ እንደሚላቸው ይነግራቸዋል።
መዝሙረ ዳዊት 87 : 7።