አዘነች ድንግል አለቀሰች አዘነች ድንግል አለቀሰች ፍጹም አምርራ በአንድ ልጇ ምክንያት ደርሶባት መከራ በአንድ ልጇ ምክንያት ደርሶባት መከራ/፪/ #አዝ በመንጻቱ ወር በዓርባኛው ቀን ሥምዖን አረጋዊ ታቀፈ እና ጌታን ትንቢት ተናገረ ተገልጾለት ሞቱ በነፍስሽ ሠይፍ ያልፋል አንቺም እናቲቱ ይኽንን መከራ ሲሠማ ጆሮዋ አምርራ አለቀሰች አልቆም አለ ዕንባዋ #አዝ በአሥራ ሁለት ዓመቱ ለማክበር በዓል በኢየሩሳሌም ቢገኝ አማኑኤል ሲጠይቅ ሲሠማ በቤተ መቅደሱ የኦሪት ካኅናት ሲደነቁ በእርሱ እስከ ሦስት ቀን ድረስ ብትልጣው ፈልጋ ልቧ ተሠበረ በሐዘን አለንጋ #አዝ ጠዋት በማለዳ በጲላጦስ ደጅ ሲጸናበት አይታ የጨካኞች እጅ ርቃኑን አድርገው ያለ አንዳች ጥፋት ከግንድ ጋር አስረው ጀርባውን ሲገርፉት እንዴትስ አታለቅስ እንዴት አታነባ ሲገርፉት ሲያዳፉት ልጇን እንደ ሌባ #አዝ የዓለሙን ፈጣሪ የዓለሙን ዳኛ ንጹሑን ጌታ መሥሏቸው ቀማኛ እጁን እና እግሮቹን በችንካር ወጥረው በወንበዴ መሐል ሠቅለውን ብታየው ድንግል አለቀሰች አልቻለች መጽናናት ዕንባዋ ወረደ እንደ ክረምት ጅረት #አዝ ዮሴፍ ኒቆዲሞስ በአንድ ሲማከሩ ቅዱሥ ሐያል ብለድ ገንዘው ሊቀብሩ በአዲስ መቃብር በአሥራ አንደኛው ሠዓት ሥጋውን አኑረው በድንጋይ ቢዘጉት እያለች ዐነባች አንድ ልጄ እኮ ነው ከእርሱ የሚቀድም ተከታይ የሌለው። @ortodoxmezmur @ortodoxmezmur @ortodoxmezmur 15.3K views11:01