Get Mystery Box with random crypto!

ሰበር ዜና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመንግስት የተለያዩ ተቋማትና በተወገዙት | የኦርቶዶክስ መንፈሳዊ ገፅ

ሰበር ዜና

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመንግስት የተለያዩ ተቋማትና በተወገዙት የቀድሞ ሶስት "ጳጳሳትና የተሾሙት 25 ጳጳሳትን" ከሰሰች

ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው
√ የቤትክርስቲያንን ክብርና ስም በመንካት
√ በሕይወት የመኖር፣ የመዘዋወር እና የማምለክ መብትን በመንካት
√ መንግሥት ሁሉን ሰው በእኩል ሕጋዊ ጥበቃ እና በእኩልነት የማየት ሕገመንግሥታዊ ኀላፊነትን ባለመወጣት

√ የቤተክህነት ንብረት ሲዘረፍ እርምጃ ባለመውሰድ

√ ጳጳሳትን እና የቤተክህነት ሕጋዊ መዋቅር ውስጥ ያሉትን በማፈን፣ በማሰርና በማስፈራራት

√ የመንግሥት ሚዲያ በሕዝብ ሀብት እየተዳደረ የቤተክርስቲያኗን መግለጫ እና የደረሰባትን የሕግ ጥሰት ባለመዘገብ ህገመንግሥታዊ ኀላፊነትን ባለመወጣት

√ አቶ ኀይለ ሚካኤል ታደሰ የተባሉ የሕገ ወጦቹ  ቃል አቀባይ ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጭ ፀብ አጫሪ ቅስቀሳ በማድረጋቸው ተከሰዋል።

ክሱ ሰኞ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በስምንት ሰዓት ይሰማል።